Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)

የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC) E
የቴሌግራም ቻናል አርማ etbcinfo — Ethiopian Trading Businesses Corporation (ETBC)
የሰርጥ አድራሻ: @etbcinfo
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.13K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-08 14:40:07
289 viewsedited  11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-07 16:21:01 https://www.etbc-ethiopia.com/index.php/media-am/news-am/316-2023-06-07-13-18-25
368 views13:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-01 15:13:47 የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 2,877,560 ኩንታል ምርትና አገልግሎት ለገበያ አቀረበ

ኮርፖሬሽኑ በ2015 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገር ውስጥ እና በውጭ ገበያ ብር 9,046,004,247 ዋጋ ያለው 2,877,560 ኩንታል ምርትና አገልግሎት በማሰራጨት ዕቅዱን በመጠን 90 በመቶ በዋጋ ደግሞ 79 በመቶ አከናውኗል፡፡ የኮርፖሬሽኑ የሽያጭ መጠን ከ2014 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ40 በመቶ ብልጫ አለው፡፡ ከተገኘው ጠቅላላ ሽያጭ ገቢ 99.14 በመቶ ከሀገር ውስጥ ሽያጭ ገቢ የተገኘ ሲሆን ቀሪው 0.86 በመቶ ከኤክስፖርት የተገኘ ገቢ ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለሃገር ውስጥ ገበያ ብር 8,713,617,305 ዋጋ ያለው 2,832,037 ኩንታል ምርት እና አገልግሎት በማሰራጨት የዕቅዱን በመጠን 92 በመቶ በዋጋ ደግሞ 81 በመቶ አከናውኗል፡፡ የሀገር ውስጥ የፍጆታ ምርቶች በገቢ ድርሻ ሲታይ፡- እህልና ቡና 69.1%፣ የምግብ ዘይት 14.7%፣ ፍጆታ ዕቃዎች 6.7%፣ የኮንስትራክሽን ግብአቶች 5.27%፣ አትክልትና ፍራፍሬ 4.1 እና የግዥ አገልግሎት ሽያጭ 0.1 በመቶ ድርሻ ነበራቸው፡፡

የውጭ ሀገር ሽያጭን በተመለከተ በዘጠኝ ወራት 6,577 ኩንታል የተለያዩ የብርዕ፣ ጥራጥሬ፣ የቅባት እህሎች፣ ቡና እና ፍራፍሬ ሽያጭ በማድረግ 1,484,488 የአሜሪካን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ከአምራቾች የገዛውን ምርት በቀጥታ ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአቅርቦት ዕጥረት ለመከላከል ከሚያደርገው ጥረት ባሻገር በበጀት ዓመቱ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በሀገር ውስጥ ግብይት ለህብረተሰቡ ያቀረባቸው ምርቶች ከነፃ ገበያ ዋጋው ጋር ሲነጻጸር ቅናሽ ነበረው፡፡ ኮርፖሬሽኑ ለህብረተሰቡ የሸጠውን ብር 7.57 በሊዮን ዋጋ ያለው ምርት በወቅቱ በነበረው የገበያ ዋጋ ቢሽጥ ሊያወጣ ይችል የነበረው ዋጋ ብር 12.24 ቢሊዮን እንደሆነ ይገመታል፡፡ በዚህም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ኮርፖሬሽኑ የሸጠው አጠቃላይ ምርት ዋጋ ከገበያው ዋጋ በብር 4.67 ቢሊዮን የቀነሰ መሆኑ ተመልከቷል፡፡
790 views12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-25 09:43:35 ኮርፖሬሽኑን ተሸላሚ ያደረጉ አመራርና ሠራተኞች የምስጋና መርኃ ግብር በፎቶ
https://www.etbc-ethiopia.com/index.php/media-am/news-am/313-2023-05-25-06-20-40
https://www.etbc-ethiopia.com/index.php/media-am/2022-03-29-11-57-28/event/KaizenAbyssinia

የማኅበራዊ ትስስር ገጾቻችችን በመቀላቀልና ድረገጻችንን በመጎብኘት የምርትና አገልግሎት መረጃዎችን በቀላሉና በፍጥነት ያግኙ!
ድረገጽ፡- https://www.etbc-ethiopia.com
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/etbcofficial
ቴሌግራም፡- https://t.me/etbcinfo
ዜና ኢንሥኮ አንድሮይድ መተግበሪያ፡- https://t.ly/DiXR
ዩትዩብ ቻነል፡- https://www.youtube.com/@etbcinfocom4858
አስተያየትዎን በኢሜይል አድራሻችን etbcinfo@etbc-ethiopia.com ያድርሱን፡፡
ኮርፖሬት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
978 viewsedited  06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 15:55:21
228 views12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-16 15:53:41 የምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ

የጃፓን መንግስት ለኢትዮጵያ የ 57ሺ ኩንታል የጃፓን ሩዝ ድጋፍ አደረገ፡፡ የምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ግንቦት 08/ 2015 ዓ.ም በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ እቃዎች ንግድ ሥራ ዘርፍ ቃሊቲ ሽያጭ ማእከል የተካሄደ ሲሆን የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው፣ በገንዘብ ሚኒስቴር የመንግስታት ትብብር ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ግርማ፣ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ኢቶ ታካኮ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አቻ ደምሴ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

ሰመሪታ ሰዋሰው የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በድጋፍ ርክክቡ ወቅት ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያና ጃፓን የቆየ የኢኮኖሚ ትብብር እንዳላቸው ጠቅሰው በጃፓን መንግስት የተደረገው የምግብ ድጋፍ የሀገራቱን ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክር እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ አያይዘውም የተደረገው የ57 ሺ ኩንታል የሩዝ ምግብ ድጋፍ 300 ሚሊየን ብር እንደሚገመት ጠቁመዋል፡፡

ኢቶ ታካኮ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ባስተላለፉት መልእክት የርክክብ ሥነ-ሥርዓቱን ላስተባበሩት የገንዘብ ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ንግድ ስራዎች ኮርፖሬሽን ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን መንግስታቸው የኢትዮጵያን ህዝብ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ የሚያግዝ ተከታታይነት ያለው ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ አክለውም ድጋፉ በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን በኩል ለኅብረተሰቡ በተቻለ ፍጥነት እንደሚሰራጭ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡

አቶ ቶውፊቅ ይመር በኮርፖሬሽኑ የፍጆታ እቃዎች ን/ስ/ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ በምግብ ድጋፍ ርክክብ ሥነ-ስርዓቱ ላይ ለተገኙት እንግዶችና የሚዲያ አካላት በፍጆታ እቃዎች ን/ስ/ ዘርፍ የቃሊቲ ሽያጭ ማእከልን ያስጎበኙና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ኮርፖሬሽኑ የምግብ ድጋፉን በአግባቡ ለህብረተሰቡ ለማሰራጨት የሚያስችል አቅምና ልምድ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መጠነኛ የሆነ የመሸጫ ተመን እንደሚወጣለት ገልጸው፣ በሸማች ህብረት ስራ ማኅበራት በኩል ለኅብረተሰቡ እንደሚደርስ ጠቁመዋል፡፡
231 views12:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 15:21:39
564 viewsedited  12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-11 13:42:12 የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
88 views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 09:49:09
219 viewsedited  06:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-04 16:19:25
334 views13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ