2022-08-31 08:01:16
በህዝባችን ላይ እየደረሰ የሚገኘውን የጠላት ትህነግና መሰሎቹ ወረራ ለመቀልበስ በየትኛውም ግንባር ለመሰለፍ ዝግጁ ነን
የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር
በወቅታዊ የጠላት ወረራ ሲመክር የቆየው የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር በህዝባችንና በሀገራችን የህልውና ዕጣ ፈንታ ላይ ያነጣጠረውን የጠላት ወረራ እንደተለመደው ከህዝባችንና ከፀጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ማንኛውንም መስዕዋትነት በመክፈል ጠላትን ለመፋለምና ዕኩይ ምኞቱን ለማክሸፍ ዝግጁ መሆናችንን እናሳውቃለን።
ህዝባችን የተለመደው አጋርነትህ እንዳይለየን እያልን ከዘመቻ ዝግጅታችን መሳ ለመሳ የሚከተሉት ትብብርና ድጋፎች የሚመለከተው አካል እንዲያደርግልን እናሳስባለን።
1ኛ-አላግባብ በእስር የሚገኙ የፋኖ ዓባሎቻችን በአስቸኳይ እንዲፈቱ፣
2ኛ-በከፋፋይ ሴረኞችና በተራ አሉባልታ እየተሳደዱና ያልተገባ ጫና እየደረሰባቸው የሚገኙ በየትኛውም አካባቢ የሚገኙ የፋኖ ዓባላት ነፃነት ተሰቷቸው ትግሉን እንዲቀላቀሉ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጥ፣
3ኛ-በዘመቻችን ቀና ትብብርና መደጋገፍ የሚመለከተው ሁሉ እንዲያደርግልን ስንል ከዘመቻ ዝግጅታችን መሳ ለመሳ ትብብርና ድጋፍ እንጠይቃለን።
ለቀናት እየተደረገ በሚገኘው ጦርነት የሚጠበቅባችሁን እየፈፀማችሁ ለምትገኙ የህዝባችን ታማኝ ጀግና ልጆች ሁሉ ያለንን ክብር እያረጋገጥን በትንሽ ቀናት ውስጥ ከጎናችሁ ተሰልፈን የጠላትን ግፍና ዕኩይ ምኞት አክሽፈን ጦርነቱን በድል እንደምንቋጨው ጥርጥር የለንም።
በክቡር መስዕዋትነት የተከበረ ሀገርና ህዝብ እናፀናለን!
በምክክር ላይ የቆየው የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር መልዕክት ነው።
አንድነት ሀይል ነው!
@ET_SEBER_ZENA
@ET_SEBER_ZENA
2.1K views05:01