Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.97K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2024-04-09 13:34:40
38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ህይወታቸው አልፏል

በጅቡቲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ

በጅቡቲ የባህር ዳርቻ ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ የመን በመጓዝ ላይ በነበረች ጀልባ ላይ በደረሰ የመስጠም አደጋ 38 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞች ሕይወታቸውን እንዳጡ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቋል።

ትላንት ሰኞ በጅቡቲ ሰሜን ምስራቅ " ጎዶሪያ " በሚባል የባህር ዳርቻ አቅራቢያ 60 ኢትዮጵያውያን ፍልሰተኞችን አሳፍራ ወደ የመን ትጓዝ የነበረች ጀልባ ላይ በደረሰው የመገልበጥ አደጋ የ38 ፍልሰተኞች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

በጅቡቲ የኢፌዴሪ ሚሲዮንም አደጋው ከደረሰ በኋላ ወደ ስፍራው በመጓዝ የአደጋውን መንስኤ በማጣራት ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ኤምባሲው ፥ በየዓመቱ ከ200 ሺ የሚበልጡ ፍልሰተኞች ከጅቡቲ ባህር ዳርቻ የኤደን ባህረ ሰላጤ በመነሳት መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመድረስ በየብስ እና በባህር አደገኛ ጉዞ ያደርጋሉ ብሏል።

ባለፉት አምስት ዓመታት በጀልባ መስመጥ አደጋ ብቻ የ189 ዜጎቻችን ሕይወት እንዳለፈ ጠቁሟል።

በየጊዜው የሚደርሰው አደጋ እንዳለ ቢሆንም የፍልሰተኞቹ ቁጥር ግን አሁንም እየጨመረ እንደሆነ ገልጿል።

ዜጎች በህገ ወጥ ደላሎች የሀሰት ስብከት በመታለል ውድ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለው በዚህ አደገኛ የጉዞ መስመር ከመንቀሳቀስ እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።

የፍትህ አካላት ሕገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን ከገጠራማ የአገራችን አካባቢዎች ዜጎቻችን በመመልመል ለስደት በሚዳርጓቸው ግለሰቦች ላይ ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳስቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
48.3K views10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 12:44:13 በአማራ ክልል እየተፈፀሙ የሚገኙ ሙስሊሞችን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችን በማስመልከት ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሠጠ መግለጫ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በታጣቂዎች እየተፈፀሙ የሚገኙትን፣ በተለይ ሙስሊሞችን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶች፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ ከአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በሚያደርገው የመረጃ ልውውጥ በቅርበት ሲከታተላቸው ቆይቷል። ጠቅላይ ምክር ቤታችን፣ ሁኔታዎች ከዛሬ ነገ ይሻሻላሉ በሚል ነገሩን በትዕግሥት ለመያዝ ቢሞክርም፣ ሁኔታዎቹ ከመሻሻል ይልቅ እየተባባሱ በመሄድ ላይ መኾናቸውን ለማወቅ ችለናል።

መጋቢት 29/2016 ምሽት የአማራ ክልላዊ መንግሥት መቀመጫ በሆነችው ባህር ዳር ከተማ፣ ከቀበሌ 14 መስጂድ የመግሪብ ሰላታቸውን ሰግደው እየወጡ በነበሩ አራት የአንድ ቤተሰብ አባላት (አንድ አባትና ሦስት ልጆቻቸው) እንዲሁም ጎረቤታቸው የኾነ ሌላ አንድ ግለሰብ፣ በታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸውን በከባድ ሐዘን ነው የሰማነው:: በተመሳሳይም በሞጣ ከተማ በአንድ ምዕመን ላይ ግድያ መፈፀሙንና በጎንደር ከተማ ተመሳሳይ ድርጊት መፈፀሙን፤ መስጅድን በጥይት መምታት ቦምብ መወርወር በተደጋጋሚ ጊዜ እየተፈፀመ በመሆኑ የአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት መጋቢት 30/2016 ባወጣው መግለጫ አሳውቆናል።

የግፍ ግድያው የተፈጸመባቸው የእነዚህ ምዕመናን ሥርዐተ-ቀብር በትናንትናው ዕለት ተፈጽሟል። አላህይዘንላቸው፤ ቤተሰቦቻቸውን መጽናናትን ይስጣቸው፡፡

በአማራ ክልል ሞጣ ከተማ ታጣቂዎች አንድን ወጣት ካገቱ በኋላ፣ ቤተሰቦቹን በማስፈራራት 300 ሺህ ተቀብለው ሲያበቁ ታጋቹን በጭካኔ መግደላቸውንም ከክልሉ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተገኘው መረጃ ይጠቁማል::

በሁለቱ ከተሞች ከተፈጸሙት የግፍ ግድያዎች በተጨማሪ መጋቢት 26/2016 እንዲሁም ቅዳሜ መጋቢት 28/2016 በብቸና ከተማ ባል እና ሚስት በጥይትና በስለት እጅግ ዘግናኝ በሆነ መንገድ ግድያ የተፈፀመባቸው እና በጎንደር ከተሞች ስላማዊ ምዕመናን መገደላቸውንም ምክር ቤታችን በሐዘን ሰምቷል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ባለፉት ስምንት ወራት፣ በተለይ ሙስሊሞችን ዒላማ በማድረግ ግድያዎች፤ እገታዎች፤ ዘረፋዎች እና የማፈናቀል ተግባራት ሲፈፀሙ መቆየታቸውን ተረድተናል፡፡

በአጠቃላይ መጠነ ሰፊ በሆነ ሁኔታ ምዕመናን የተገደሉ፣ የታገቱ እና በሺዎች የሚቆጠሩ የተፈናቀሉ ሲሆን፤ ከፍተኛ ዝርፊያዎች ተፈጽመዋል።

የተለያዩ ሃይማኖትና እምነት ተከታዮች ለአያሌ ዘመናት አብረው በሰላም በኖሩባት ሀገራችን፣ ዜጎችን በሃይማኖታቸው ሳቢያ ልዩነት በመፍጠር የጥቃት ዒላማ ማድረግ፣ የሀገርን ሰላም እናየሕዝብን አብሮነት በእጅጉ የሚጎዳ፣ አስከፊ ማኅበራዊ ጠባሳ የሚያስከትል፣ ኃላፊነት የጎደለውና በፍፁም ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው::

ሰዎች የተለያየ ጥያቄ ሊኖራቸው ይችላል:: ነገር ግን ሰላማዊ ዜጎችን በግፍ በመግደልና በማሸበር ሊያሳኩ የሚችሉት ምንም ዓይነት ግብ ይኖራል ብለን አናምንም::

ሰላማዊ ዜጎችን በሃይማኖት ለይቶ የማጥቃት እርምጃ፣ በማንም ይፈፀም በማን የሽብር ተግባር እንጂ፣ የትኛውንም ሃይማኖት ወይም ብሔር የሚወክል ተግባር ነው ብለንም አናምንም። በመኾነ-ም፣ በአማራ ክልል በተደጋጋሚ እየተፈፀሙ ያሉትን ሙስሊሞችን ዒላማ ያደረጉ የግድያ፣ የእገታ እና የዘረፋ ጥቃቶች በጽኑ እናወግዛቸዋለን፡፡

ይህ የጥፋት ክብሪት ዉሎ አድሮ ሁላችንንም ሊያነደን የሚችል በመኾኑ፣ ሁሉም የሃይማኖት ተቋማት ዛሬውኑ በጥብቅ ሊያወግዙት ይገባል ብለንም እናምናለን።

ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
13.1K views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 11:19:03 ከዒድ አልፈጥር ክብረ በዓል ጋር ተያይዞ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ

ከለሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ የኢድ አልፈጥር በዓል ጋር ተያይዞ የበዓሉ የኢድ ሶላት ተጀምሮ እሰከሚጠናቀቅ በአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ይዘጋሉ።

በዚህም መሰረት ፦

- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ

- ከጎተራ ማሳለጫ ወደ ስታዲዮም የሚወስደው  አጎና ሲኒማ ላይ

- ከሜክሲኮ ወደ ለገሃር የሚወስደው መንገድ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

- ከብሔራዊ ቤ/መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት ላይ

- ከኦሎሚፒያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ

- ከመገናኛ ወደ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ  22 መስቀለኛ መንገዱ አካባቢ

- ከጥቁር አንበሳ ሼል ወደ ለገሀር የሚወስደው መንገድ ጥቁር አንበሳ ሼል  አጠገብ

- ከሲግናል እና ከአቧሬ ወደ ካዛንቺስ የሚመጣው መንገድ  አቧሬ ሴቶች አደባባይ  ላይ

- ከመስቀል ፍላወር ወደ መስቀል አደባባይ የሚመጣው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ

- ከቄራ በአዲሱ መንገድ ወደ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን የሚወስደው መንገድ ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን መገንጠያ ላይ

- ከጌጃ ሰፈር በሰንጋተራ ወደ ለገሐር ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ሰንጋ ተራ 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት አካባቢ

- ከአብነት በጌጃ ሰፈር ወደ ብሔራዊ ቴአትር የሚወስደው መንገድ ጎባ ቁጠባ አጠገብ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቴአትር ሜትሮሎጂ መ/ቤት ላይ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የኋላ በር  ወደ ብሔራዊ ቴአትር  ለሚሄዱ ጥቁር አንበሳ ሼል ድሬንስ አካባቢ

- ከተክለ ሐይማኖት አካባቢ በጎላ ሚካኤል ውስጥ ለውስጥ ወደ ለገሐር ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች ጎላ ሚካኤል መስቀለኛው ላይ

... ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከለሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ይሆናሉ።

መላው ህብረተሰቡ / አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
16.7K viewsedited  08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 11:18:44
15.3K views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 10:33:24
የኢድ አል ፈጥር በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር ዝግጅት ተጠናቅቋል

የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል

ሕዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል ፈጥር በዓልን ያለምን የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲያከብር በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም ከተማ አስተዳደሮች የጋራ ግብረ ኃይሉ ከወዲሁ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር በመግባት ተልዕኮውን በተገቢው እየተወጣ እንደሚገኝ አስታወቀ።

የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ-ኃይል የኢድ አል ፈጥር በዓልን አስመልክቶ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፏል፡፡

በመልእክቱም፤ ሕዝበ ሙስሊሙ በዓሉን ያለምን የፀጥታ ችግር በሰላም እንዲያከብር የጋራ ግብረ ኃይሉ ከወዲሁ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ተግባር መግባቱን አስታውቋል፡፡

ሰላም ወዳዱ የሀገራችን ሕዝብም ለሰላምና ደኅንነት እንቅፋት የሆኑ ነገሮችን ለማስወገድ በሚካሄደው የፀጥታ ማስከበር ሥራ ውስጥ በባለቤትነት እያደረገ ያለውን ተሳትፎ የበለጠ አጠናክሮ እንዲቀጥል የጋራ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል፡፡

ማህበረሰቡ የአካባቢውን ሰላምና ደኅንነት የሚያደፈርሱ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠትና አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ ከጋራ ግብረ-ኃይሉ ጎን በመሆን የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣውም ግብረ-ኃይሉ ጥሪውን አቅርቧል።

ለመላው የዕምነቱ ተከታዮች እንኳን ለ1445ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ያለው የፀጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረ ኃይል፤ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር እና የአብሮነት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
17.6K views07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 09:55:14
ከ1 ነጥብ 8 ሚሊየን በላይ የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በኦንላይን ተሠጠ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ 1 ሚሊየን 816 ሺህ 41 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎቶች በኦንላይን መሠጠታቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ለዘርፉ የተሻለ አፈፃፀም መገኘትም በእድሳት ወቅት ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ በእረፍት ቀናት አገልግሎት መሠጠቱ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡

በሀገር አቀፍ ደረጃ በአጠቃላይ በኦንላይን እና በባክ ኦፊስ 2 ሚሊየን 34 ሺህ 787 የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት መሠጠቱን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

ከተሠጡት አገልግሎቶች መካከልም÷ አዲስ የንግድ ምዝገባና የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ፈቃድ እድሳት፣ ማሻሻያ፣ የንግድ ስም እንዲሁም መሠል 19 የተለያዩ አገልግሎቶች እንደሚገኙበት ተጠቅሷል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት በሀገር አቀፍ ደረጃ 2 ነጥብ 8 ሚሊየን የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት በኦንላይን ለመስጠት ታቅዶ እየተሠራ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
17.9K views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 09:55:12
በጾም ወቅት ምን ልጠቀም ብለዉ እያሰቡ ከሆነ በአንድ ማንኪያ ከ23 ግራም በላይ ፕሮቲን ሊያገኙበት የሚችሉትን 100% የቪጋን ፕሮቲን አመጣንልዎ።

በከፍተኛ ጥራት የተመረተ

አሁኑኑ ለማዘዝ 9369 ላይ ይደውሉልን፣ የዘርፉ ባለሟያዎች ትክክለኛዎቹን ምርቶች ለመምረጥ እና ፈጣን አቅርቦትን ለማዘጋጀት ይረዳዎታል።

የሚያስፈልገው ጓደኛ ካለዎት share ማድረግዎን አይዘንጉ!


አዳማ - ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ 9369


+251966113766

Join  https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5
16.1K views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 09:52:03
ከዘመኑ ጋር ይዘምኑ!

      ራሰዎን በአንድ ቋንቋ አይገድቡ! የተለያዩ ቋንቋዎችን ይማሩ! የስራ ፣ የትምህርት እና የህይወት አማራጭዎን ያስፉ !
    ስልክዎን ተጠቅመው የፈለጉትን ቋንቋ በታላላቅ ዩንቨርቲዎች እና ኮሌጆች በሚያስተምሩ  ብቁ መምህራኖቻችን ተምረው በራስ መተማመንዎን ያዳብሩ!
   
እንግሊዘኛ
አረብኛ
አፋን ኦሮሞ
አማርኛ  ቋንቋዎችን የትም ሀገር ቢሆን አያሳስበዎት  በኦንላይን እናስተምረዎታለን!

ብራይት የስልጠና ማዕከል
    ለብርሀናማ ሕይወት ትክክለኛ ቦታ
0932878889
0970828287
https://t.me/brighttraining90
17.9K views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-09 09:51:59
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

0911248768   ይደውሉልን
17.9K views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 23:10:35
የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን ማጨለሙ ተነገረ

የፀሐይ ግርዶሹ በርካታ የአሜሪካ ከተሞችን በእኩለ ቀን ሙሉ በሙሉ እንዳጨለማቸው ተገልጿል፡፡

ሙሉ የጸሐይ ግርዶሹ ማዛትላን የተባለችውን የሜክሲኮ ከተማ ጨለማ አልብሷት ከለፈ በኃላ ወደ ዳላስ፣ ቴክሳስ እና ሌሎች የአሜሪካ ግዛቶች ተሸጋግሯል፡፡

በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች የጸሐይ ግርዶሹ እስከ 4 ደቂቃ መቆየቱም ተጠቁሟል፡፡

የጸሐይ ግርዶሹ በሚቀጥሉት ሰዓታት ወደ ሰሜን አሜሪካ ሰሜናዊ እና ምስራቃዊ ክፍሎች እንደሚዞርም ተመላክቷል፡፡

በሰሜን አሜሪካ ክስተቱን ለማየት በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ መውጣታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ክስተቱን በልዩ ሁኔታ እየተከታተለ የሚገኘው የአሜሪካ የጠፈር ምርምር ተቋም (ናሳ) ያለ ጸሐይ መነጽር ግርዶሹን ለማየት መሞከር እጅግ የዓይን ብርሃንን እስከማሳጣት የሚደርስ ችግር ሊያመጣ እንደሚችል በማስገንዘብ ላይ መሆኑም ተነግሯል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
31.2K views20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ