Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 247.50K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-03-16 20:20:10
ለውድ የባንካችን ደንበኞች የዲጂታል ባንክ አግልግሎት ሙሉ በሙሉ መጀመሩን እንገልፃለን

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

በሲስተም ችግር ምክንያት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፥ በኢንተርኔት ባንኪንግ፥ በሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ አጋጥሞ እንደነበር መግለፃችን ይታወቃል።

በቅርንጫፍ እና በኤቲኤም የሚሰጡ አገልግሎቶች ቀደም ብለው መጀመራቸውን ያሳወቅን ሲሆን አሁን ደግሞ በዲጂታል የሚሰጡ የባንክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መጀመራቸውን እናሳውቃለን።

ውድ ደንበኞቻችን በትእግስት ስለጠበቃችሁን እያመሰገንን ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል  በድጋሚ ይቅርታ እንጠይቃለን።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
21.0K views17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 16:46:44 የኢትዮጲያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በመስቀል አደባባይ የሚያከናውኑት የፀሎት ፕሮግራም ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የተወሰኑ መንገዶችን ለተሸከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ

አሽከርካሪዎች እንደተለመደው ለትራፊክ ፖሊሶች ትዕዛዝ ተባባሪ እንዲሆኑ ተጠይቋል፡፡

ዕሁድ መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ ከሰዓት በሗላ ከቀኑ 7፡30 እስከ 12፡00 ሰዓት ድረስ የኢትዮጲያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የፀሎት መርሐ-ግብር ስለሚያከናውኑ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

አሽከርካሪዎች መረጃው አስቀድሞ ኖሯቸው ሌሎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ ተባባሪ እንዲሆኑ ፖሊስ ጥሪውን እያስተላለፈ፡-

• ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ኡራኤል አደባባይ ላይ

• ከቦሌ ጌቱ ኮሜርሻል አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ አደባባይ በታች እና በላይ እንዲሁም ግራና ቀኝ

.የቀድሞው አራተኛ ክፍለጦር (ጥላሁን አደባባይ ላይ )

• ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለሚጓዙ ለገሀር መብራት ላይ

• ከሀራምቤ መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት ላይ

• ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ
ዕሁድ መጋቢት 8 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡ 00 ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ድረስ መንገዶቹ ለጊዜው ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ፡፡

ፕሮግራሙ በሚከበርበት ዙሪያ እና በአካባቢው በግራና በቀኝ ለረጅምም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
29.6K views13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 15:36:40 የኤቲኤም(ATM) አገልግሎት ጀምሯል

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

• ሀሰተኛ መረጃን ስለማሳወቅ

ለክቡራን ደንበኞቻችን በቅርንጫፎች አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን ቀደም ብለን ያሳወቅን ሲሆን አሁን ደግሞ ተቋርጦ የነበረው የኤቲኤም(ATM) አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ስራ የጀመረ መሆኑን ለክቡራን ደንበኞቻችን እንገልጻለን። በቀጣይም ሁሉንም ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች ሥራ የምናስጀምር ይሆናል፡፡

በሌላ በኩል በሲስተም ችግር ምክንያት በባንካችን በጊዜያዊነት የተከሰተውን የአገልግሎት መስተጓጎልን ምክንያት በማድረግ ሀሰተኛ መረጃዎች በማህበራዊ ትስሥር ገፆች በመዘዋወር ላይ እንደሚገኙ ለመረዳት ችለናል፡፡

በባንካችን የተከሰተው የአገልግሎት መቋረጥ በባንካችን የውስጥ የሲስተም ችግር እንጂ ፣ በሀሰት እንደሚሰራጨው ከባንኩ ውጭ በደረሰ የሳይበር ወይም ሌላ ተመሳሳይ ጥቃት አለመሆኑን እየገለፅን፣ ባንካችን አስተማማኝ የሳይበር ደህንነት ጥበቃ ያለው መሆኑን በድጋሚ እናረጋግጣለን፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምንም አይነት ስጋት እንዳይገባቸው እያሳሰብን፣ ችግሩን በሰዓታት ልዩነት ሙሉ በሙሉ ለማስተካከል አየሠራን መሆኑን እንገልፃለን፡፡


@Esat_tv1
@Esat_tv1
31.4K views12:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 13:35:27
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲስተም ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የቅርንጫፎች አገልግሎት መጀመሩን አሳውቋል

የባንኩ ቅርንጫፎች ዛሬ እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት አገልግሎት እንደሚሰጡም አሳውቋል።

በተመሳሳይ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶች ፦
- ኢንተርኔት ባንኪንግ፥
- ሞባይል ባንኪንግ፥
- ሲቢኢ ብር ለማስጀመር እየሠራ መሆኑን ገልጾ ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል በድጋሚ ይቅርታ ጠይቋል።

ባንኩ በምን ምክንያት የሲስተም ችግር እንደተፈጠረ የሰጠው ማብራሪያ የለም።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
33.4K views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 11:29:33
በሲስተም ችግር ምክንያት የተቋረጠውን አገልግሎት መልሶ ለማስጀመር በከፍተኛ ርብርብ እየተሰራ ነው

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

በሲስተም ችግር ምክንያት የተቋረጠውን አገልግሎት መልሶ ለማስጀመር በከፍተኛ ርብርብ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲስተም ችግር ምክንያት በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ማለትም በቅርንጫፎች፣ በኢንተርኔት ባንኪንግ፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ እንዲሁም በሲቢኢ ብር የአገልግሎት መቋረጥ እንዳጋጠመው አስታውቋል።

አገልግሎቱን መልሶ ለማስጀመር በከፍተኛ እርብርብ እየተሰራ መሆኑን የገለፀው ባንኩ፤ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጠይቋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
35.1K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 11:29:33
በኢትዬጵያ ለመጀመርያ ግዜ ያስገባነው(water proof)ከ እርጥበት የሚከላከል የፍራሽ ሽፋን....
100% water proof] ምንም አይነት ውሃ ፣ ፈሳሽ ፣እርጥበት የማይልሳልፍ
ሲተኙ እንደ ላስቲክ ሰውነትን የማያቃጥል
የመንኮሻኮሽ ድምፅ ፤የማንሸራተት ፀባይ የሌለው
ሲፈልጉ አውልቀው የሚያጥቡት
ፍራሽዎን በንጽሕና ይጠብቃል
ለማጽዳት ቀላል ነው
የፍራሽዎን የማገልገል ዋስትናዎ ረዘም ላለ ጊዜ እንዲቆይ ያግዛል።
አልጋህን የበለጠ ምቹ ያደርገዋል
አለርጂዎችን ወይም ሳንካዎችን ያግዳል።
የፍራሽ ጥራትን ይጠብቃል
ይደውሉ ያሉበት እንልካለን
Mattres size
1.20mx2m.....3500birr                         1.50mx2m ....3700birr
1.80mx2m ..... .4000birr                       2m×2.2m......4,200birr
0910647273  0936115487

Join telegram  https://t.me/trutruekawoch
32.7K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-16 11:29:24
Do You Want To Buy Or Sell Cars Without Hustle? Welcome to the Best Online Car Market .. Please Join And Contact Us You Will Be Thankfull.. Join @

https://t.me/Poppycarmarket

+251911407105
+251911248768

Let's Make Life Easy
30.2K views08:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 21:57:42 ታግተው የነበሩ አምስት የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መገደላቸው ተነገረ

ለሁለት ሳምንት ያህል ታግተው የነበሩ አምስት የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች ተገድለው መገኘታቸውን የፋብሪካውን አንድ ኃላፊ ለቢቢሲ ገለጹ።ስማቸውን እንዳይጠቀስ የጠየቁት የስኳር ፋብሪካው ኃላፊ የአምስቱ ሠራተኞች አስከሬን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 6/2016 ዓ.ም. መገኘቱን ገልጸዋል።

አስከሬናቸው ከፋብሪካው ማሳ ወጣ ብሎ ጨካ በሚባል የገጠር አካባቢ ነው የተገኘው።ከተገደሉት መካከለ ሦስቱ ሠራተኞች ከወንጂ አካባቢ ሲሆኑ፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም በዛሬው ዕለት መፈጸሙ ተገልጿል።ሌሎቹ ሁለቱ ሠራተኞች አንደኛው ከአዳማ የመጣው ሲሆን ቀብሩ ዛሬ የሚፈጽም ሲሆን፣ እንዲሁም ሌላኛው ከደሴ የመጣው ግለሰብ አስከሬን ወደ ስፍራው ተልኳል ተብሏል።

አራቱ ሠራተኞች በፋብሪካው ውስጥ በትራክተር ኦፕሬተርነት ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ እና ዕድሜያቸው ከፍ ያለ እንደሆኑም እኚሁ የፋብሪካው ኃላፊ ለቢቢሲ ተናግረዋል።ሌላኛው የኤሌክትሪክ ሠራተኛ (ፎርማን) ወጣት ሲሆን በቅርብ የተቀጠረ እና ለአንድ ዓመት ያህል በፋብሪካው አገልግሏል።

አንደ ኃላፊው ከሆነ ግለሰቦቹ ከሁለት ሳምንታት በፊት የአዳር ስር ላይ ምሽቱን አሳልፈው ጥዋት ላይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ዶዶታ ከሚባለው ፋብሪካው ከሚገኝበት ስፍራ በታጣቂዎች ታግተው ተወስደዋል።ኃላፊው፣ ሠራተኞቹን ያገቷቸው ሰዎች ገንዘብ ጠይቀው እንደነበር? ወይም የጠየቋቸው ጉዳዮች እንዳሉ ዝርዝሩን እንደማያውቁ አስረድተዋል።

ነገር ግን ፋብሪካው ከአጋቾቹ በኩል ምንም እንዳልተጠየቀ ገልጸው፣ ወዲያውኑ ለመንግሥት አካል ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።ፓሊስም ሠራተኞቹን ለማስለቀቅ እየተከታታለ እንደነበር የገለጹት ኃላፊው፤ ነገር ግን አስከሬናቸው ዛሬ ጥዋት 2 ሰዓት አካባቢ ተገኝቷል ብለዋል።ስለ ግድያው እንዴት? እና ስንት ሰዓት? ተፈጸመ የሚለውን ባያውቁም ምናልባትም ትናንት ምሽት ተገድለዋል ብለው እንደሚጠረጥሩ የተናገሩት ኃላፊው ሰራተኞቹ መገደላቸውን ሰምተው ወደ አካበቢው ሲሄዱ አስከሬናቸውን አግኝተናል ብለዋል።

በፋብሪካው እገታ ሲያጋጥም የመጀመሪያ መሆኑን እና እስካሁን ባለው ሁኔታ ሰላማዊ እንደነበርም ኃላፊው አስረድተዋል።በእገታው ዙሪያ ቢቢሲ የተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎችን እና ቤተሰቦቻቸውን ለማናገር እየሞከረ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃዎችን ስናገኝ እናካትታለን።በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አቅራቢያ ከአዲስ አበባ 110 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የወንጂ ስኳር ፋብሪካ በ1946 ዓ.ም. ኤች.ቪ.ኤ በተባለ የኔዘርላንድስ ተቋም እና በኢትዮጵያ መንግሥት የጋራ ባለቤትነት የተቋቋሙ በአገሪቱ ቀዳሚ የስኳር ፋብሪካ ነው።

ወታደራዊው መንግሥት ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ ፋብሪካው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት ባለቤትነት ስር መግባቱ ይታወሳል።ወንጂ ስኳር ፋብሪካ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 496/2014 ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ከተደረጉት አምስት ስኳር ፋብሪካዎች መካከከል አንደኛው ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
39.3K views18:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 17:30:47
430 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለመምህራን በዕጣ ተላለፉ

በዛሬው ዕለት 430 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለመምህራን በዕጣ እንዲተላለፉ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

ከዚህ በፊት ለመምህራን ተላልፈው ከነበሩ 5 ሺህ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ውል ሳይፈጸምባቸው የቆዩ 435 ቤቶች ናቸው ዛሬ በዕጣ እንዲተላለፉ የተደረጉት።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት መረጃ፤ ውል ሳይፈጸምባቸው የቆዩት 435 ቤቶችን በማጣራት ከተለዩ በኋላ ዛሬ በዕጣ ለቤት ዕድለኞቹ መተላለፋቸውን ገልጸዋል።

"ያለንን ውስን ሃብት በግልፀኝነትና በፍትዊነት በተገቢ ሁኔታ ለህዝባችን እንዲደርስ እያደረግን መስራታችንን እንቀጥላለን" ብለዋል ከንቲባዋ በመልዕክታቸው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
43.0K views14:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 12:10:16
የቲክ ቶክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ተጠቃሚዎች የአሜሪካ እገዳን እንዲታገሉ ጥሪ አቀረቡ

የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት ቲክ ቶክ እንዲታገድ በድምጽ ብልጫ የወሰነ ሲሆን፣ ሴኔቱም ድምጽ ሊሰጥበት ዝግጅት ላይ እንደሆነ ታውቋል።

የቲክ ቶክ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሹ ቼው ቲክ ቶክን ማገድ በሺዎች የሚቆጠሩ አሜሪካውያንን ህይወት አደጋ ላይ ይጥላል ብለዋል።

ዋና ሥራ አስፈጻሚው አስተያየቱን የሰጡት የአሜሪካ የታችኛው ምክር ቤት ቻይናዊ የቲክቶክ ባለቤት ባይትዳንስ ቲክ ቶክን ለአሜሪካ እንዲሸጡ ወይም ካልሆነ እገዳ እንዲጣል የሚያስገድድ ረቂቅ ካፀደቀ በኋላ ነው።

ህጉ በሴኔቱ ከፀደቀ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ወደ ተግባር እንዲገባ እፈርማለሁ ማለታቸው ይታወሳል።

ቼው ለምክር ቤቱ ድምጽ ምላሽ ሲሰጡም ውሳኔውን “አሳዛኝ” እና ከባድ መዘዝ ሊያከትል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።

ውሳኔው መተግበሪያውን በመጠቀም በትንንሽ ንግዶች ውስጥ በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እያገኙ ያሉ ሰዎችን ባዶ ኪስ ማስቀረት እንደሆና የበርካታ አሜሪካውያንን ሥራ አደጋ ላይ መጣል ነው ብለዋል።

ከ170 ሚሊዮን በላይ አሜሪካውያን የቲክ ቶክ ተጠቃሚዎች መሆናቸውን አርቲ በዘገባው አስታውሷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
43.6K views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ