Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.97K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2024-04-05 14:36:44
በካፋ ዞን በጊምቦ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ

በካፋ ዞን በጊምቦ ወረዳ ቢጣ ጨጋ ቀበሌ ልዩ ስፍራው ዳራ ተብሉ በሚጠራ አከባቢ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ኦባማ የጭነት ተሸከርካሪ ከባጃጅ ጋር በመጋጨታቸው በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድሩሱን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

በአደጋው ባጃጅ ውስጥ የነበሩ ሾፌሩን ጨምሮ 2 ወንዶችና 2 ሴቶች ወዲያውኑ ህይወታቸው ሲልፍ 1 ሰው ለተጨማሪ ህክምና ወደ ጅማ በመጓዝ ላይ እያለች ህይወቷ ማለፉን ተነግሯል። የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነውም ተብሏል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
36.0K views11:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 09:51:00
በትናንትናው እለት በፍኖተሰላም ከተማ በሚገኝ ት/ት ዉስጥ በደረሰ የቦንብ ፍንዳታ በ 25 ተማሪዎች ላይ ጉዳት ደረሰ አራት ተማሪዎችም በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ተብሏል

በትናንትናው እለት በዳሞት መሰናዶ ቁጥር 1 ትምህርት ቤት ላይ በፈነዳ ቦንብ 25 ተማሪዎች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን አራቱ ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተሰምቷል። ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው ተማሪዎች ውስጥም ሁለቱ ተማሪዎች ሪፈር ተብለዋል ሲል የክልሉ መንግስት አስታውቋል፡፡

ዮሃንስ ተስፋየ ሹመት የተባለ ተማሪ ፍንዳታውን ያደረሰ መሆኑን ፖሊስ አረጋግጧል ያለዉ የአማራ ክልላዊ መንግስት ፤ ተማሪዉ እጁ እና እግሩ ላይ ቆስሎ ተይዟል ማለቱንም ተሰምቷል። የክልሉ መንግስት "ጽንፈኛ" ሲል የጠራዉን የፋኖ ሀይል ለዚህ ፍንዳታ ተጠያቂ አድርጎታል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
37.8K views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 14:46:59
480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ ተያዙ

ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ መያዛቸው ተነግሯል።

የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት/IOM ሰኞ'ለት ባወጣው መግለጫ 480 ስደተኞች በባህር ላይ ጠባቂዎች መያዛቸውን አስታውቋል።

ድርጅቱ "ከመጋቢት 24 እስከ 30,2024 ውስጥ 480 ስደተኞች ተይዘው ወደ ሊቢያ ተመልሰዋል " ነው ያለው።

ከተያዙት ስደተኞች ውስጥ 26 ሴቶች እንዲሁም 5 ህፃናት እንደሚገኙበትም ተነግሯል።

የስደተኞች 2 አስክሬንም ተገኝቷል።

በዚህ ዓመት በጠቅላላ 3,791 ስደተኞች የተያዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 120ዎቹ ሲሞቱ ፣ ሌሎች 250 የሚሆኑት ጠፍተዋል መባሉን MDN ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
24.9K views11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 13:06:46
በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት አያገኙም ተባለ

በሚቀጥለው ዓመት የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ለማግኘት ብሔራዊ መታወቂያ ያስፈልጋል በማለት በቀጣይ ዓመት ብሔራዊ መታወቂያ የሌላቸው ነጋዴዎች አገልግሎት ማግኘት እንደማይችሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

የንግድ ፈቃድና ምዝገባ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ደንበኞች በአካል መገኘት ሳይጠበቅባቸው በኦንላይን አገልግሎት እያገኙ ነው ሲባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚሰጣቸው አገልግሎቶች ከሌሎች ተቋማት ጋር የሚያገናኘው በመሆኑ ከተቋማቱ ጋር ሲስተም የማናበብ ስራ በፋይዳ መለያ የሚሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።

ስለዚህ የንግዱ ማህበረሰብ ከ2017 በፊት ብሔራዊ መታወቂያ በማውጣት ራሱን ለነገሮች ዝግጁ ማድረግ ይጠበቅበታል ሲሉ በንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የላይሰንሲንግ እና ሬጉላቶሪ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጅራታ ነመራ ተናግረዋል።

Credit : EPA

@Esat_tv1
@Esat_tv1
28.5K views10:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 11:22:42
ጠንካራ የግል ዳታ ጥበቃ ስርዓት ለመፍጠር ያስችላል የተባለ አዋጅ ፀደቀ

በምክር ቤቱ የሰው ሀብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አዋጁን አስመልክቶ እንደገለጸው÷ አዋጁ የግል ዳታ ጥበቃ ተቆጣጣሪ ተቋምን በመሰየም ጠንካራ የግል ዳታ ጥበቃ ስርዓት እንዲፈጠር ለማድረግ ወሳኝ ነው፡፡

የግል ዳታን ማሰባሰብ አስፈላጊ እየሆነ መምጣቱ እና በዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ውስጥ የተሰበሰቡ የግል ዳታዎችን ማቀናበር ለማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እድገት ያለው ሚና እያደገ በመምጣቱ አዋጁ እንደተዘጋጀ ተጠቁሟል፡፡

እንዲሁም ዳታ በሚሰበሰብበት እና በሚቀናበርበት ወቅት የግል ዳታ መብት ጥሰት እንዳይፈጠር ለመቆጣጥር የሚያስችል የግል ዳታ ጥበቃ አዋጅ ማውጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱም አዋጁ እንደተዘጋጀ ቋሚ ኮሚቴው ገልጿል፡፡

በተጨማሪም አዋጁ ከግል ዳታ ጋር የተያያዙ የመብት ጥሰቶች ሲከሰቱ ውጤታማ መፍትሔ ለመስጠት እንዲሁም ከዳታ ማቀናበር ስራ ጋር የተያያዘ አደጋን ለመቀነስ እና ሀላፊነት የሚሰማው ዳታ የማቀናበር ባህልን ለማሳደግ ወሳኝ እንደሆነ ተጠቅሷል፡፡

በኢትዮጵያ የግል ዳታ ላይ መብትን ዝርዝር የሚደነግግ ሕግ ባለመኖሩ እና የግል ዳታ ጥበቃ ተቆጣጣሪ ተቋም ባለመሰየሙ ጠንካራ የግል ዳታ ጥበቃ ስርዓት እንዳይፈጠር ማድረጉ ተነስቷል፡፡

በዚህም ዳታ በሚሰበሰብበት እና በሚቀናበርበት ወቅት የግል ዳታ መብት ጥሰት እንዳይፈጠር ለመቆጣጠር የሚያስችል አዋጅ ማውጣት አስፈልጓልም ነው የተባለው፡፡

በረቂቅ አዋጁ ላይ ከህዝብ ጋር እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት መካሄዱንም ቋሚ ኮሚቴው አስታውሷል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
28.6K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 11:22:40
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

0911248768   ይደውሉልን
25.1K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-04 11:22:28
እንዲህም አለ?

ኢትዮጲያን ጨምሮ በተለያዮ የአለም ሀገራት እየኖሩ ቋንቋን በ online (ኦንላይን) መማር

ብራይት የስልጠና ማዕከል ባሉበት ቦታ ሆነው በ online (ኦንላይን) አማራጭ ብቻ  የበርካታ አመታት ልምድ ባላቸው መምህራኖቹ  አማርኛ ፣ አፋን ኦሮሞ ፣ እንግሊዘኛ እና ዓረበኛ ቋንቋን ከመፃፍና ማንበብ ጀምሮ በሚያስደስት መልኩ  እያስተማረ ይገኛል።

በነዚህ ስልኮች በዋሳፕ፣በቴሌግራም፣በኢሞ ያገኝናል።
0932878889
0933666662
@brighttraining90
ብራይት የስልጠና መአከል
ለብርሀናማ ሂወት ትክክለኛ ቦታ።
26.7K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 17:36:50
ጁምዓና ከተራን ጨምሮ አራት ቀናት ሥራ ዝግ ሆኖ እንዲከበሩ ጥያቄ ቀረበ

ጁምዓ፣ ከተራና ቃና ዘገሊላ የአደባባይ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች፣ እንዲሁም የካቲት 12 የሰማዕታት መታሰቢያ በዓላት ሥራ ዝግ ሆነው እንዲከበሩ በፓርላማ ጥያቄ መቅረቡን ሪፖርተር አስነብቧል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለጤና፣ የሕዝብ በዓላትንና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የሕዝብ ውይይት የተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች፣ ምሁራንና ሌሎች ተቋማት ተሳትፈዋል።

ተሳታፊዎቹ ምን ጥያቄ አቀረቡ?

- የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን በመወከል የተገኙት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል፣ በእስልምና አንድ ሰው 3 ተከታታይ ጁምዓ ካልተገኘ በመናፍቅነት የሚያስፈርጅ ከባድ ጉዳይ በመሆኑ፣ ዓርብ (ጁምዓ) ቀን ሥራ ዝግ እንዲሆን፣ ወይም ደግሞ አሁን በሥራ ላይ ያለውን ከአምስት ሰዓት ተኩል እስከ ሰባት ሰዓት ተኩል በአዋጁ መካተት አለበት ብለዋል።

- ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትሪያሪክ የሕግ መምርያ ኃላፊ መምህር አባ ገብረ ሥላሴ ጌትነት፣ እየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ባህረ ዮርዳኖስ ሄዶ መጠመቁን የሚያሳየው የቃል ኪዳኑን ታቦት በመያዝ ጥር 10 ቀን የሚከበረው ከተራና ከጥምቀት በኋላ ጥር 12 ቀን የሚከበረው ቃና ዘገሊላ ክብረ በዓላት ከሥራ ዝግ መሆን አለባቸው ብለዋል፡፡

- በተጨማሪም የካቲት 12 የሰማዕታት ቀን ታስቦ ከመዋል ይልቅ ከሥራ ዝግ ሆኖ መከበር ይገባዋል ያሉት ደግሞ፣ የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረዳት ፕሮፌሰር) ናቸው፡፡

የተሰጡ አስተያየቶች ረቂቅ አዋጁን ለማጎልበት እንደሚያግዝ ሲገለፅ፣ አዋጁ ኢትዮጵያውያንን እንዲመስል ዘላቂነት ያለው ውይይት እንደሚደረግም ተጠቁሟል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
39.6K views14:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 15:07:38
በመሬት አገልግሎት ላይ ተጥሎ የነበረው  እግድ ተነሳ

ላለፉት ሦስት ወራት እግድ ተጥሎበት የነበረው የመሬት አገልግሎት ካለፈው ሰኞ መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ መነሳቱ ተገለጸ።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ በተጠናው የመዋቅር ጥናት መሠረት የሰራተኞች ድልድል ተካሂዶ ምደባ እስከሚካሄድ ድረስ ከጥር  21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት ሦስት ወራት ታግዶ የቆየው የመሬት አገልግሎት፣ የዜጎችን መብት የጣሰ እንደነበር በመናገር  ተገልጋዮች ሲያማርሩ ቆይተዋል።

አስተዳደሩ   እንደገለጸው አጠቃላይ የሰራተኛ ድልድሉ በመጠናቀቁ ከቀን ከመጋቢት 23 ቀን2016 ዓ.ም ጀምሮ የመሬት አገልግሎት የተጀመረ  መሆኑን አስታውቋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
39.4K views12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-03 11:46:23
28ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 28ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን 2017-2021 የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊሲካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የማክሮ ኢኮኖሚና ፊሲካል ማዕቀፉ የመንግስት በጀት ከማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታው እና የፊሲካል አቅም ጋር ተጣጥሞ እንዲዘጋጅ ለማድረግ፤ ከመንግስት ገቢ አሰባሰብ እና ሀብት አመዳደብ አኳያ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን በማመላከት ለቀጣይ በጀት አመት የበጀት ዝግጅት ለማድረግ፤ የመካከለኛ ዘመን የመንግስት ገቢና ወጪ እንዲሁም የፊሲካል ሚዛን የፖሊሲ አቅጣጫዎችን ለመለየት እና ለማመላከት የሚያገለግል ማዕቀፍ በመሆኑ ምክር ቤቱ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው የተጨማሪ እሴት ታክስ ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የተጨማሪ እሴት ታክስ ስራ ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ በሀገሪቱ የእኮኖሚ እንቅስቃሴ ውስጥ የተደረጉ ለውጦችን በህግ ማእቀፉ ውስጥ ማስገባት በማስፈለጉ፣ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የተጨማሪ እሴት ታክስ ጫና እንዳያርፍባቸው ለማድረግ የሚያስችል ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
40.3K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ