Get Mystery Box with random crypto!

480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ ተያዙ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 480 ስደተኞች በሊቢያ | ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ ተያዙ

ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ መያዛቸው ተነግሯል።

የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት/IOM ሰኞ'ለት ባወጣው መግለጫ 480 ስደተኞች በባህር ላይ ጠባቂዎች መያዛቸውን አስታውቋል።

ድርጅቱ "ከመጋቢት 24 እስከ 30,2024 ውስጥ 480 ስደተኞች ተይዘው ወደ ሊቢያ ተመልሰዋል " ነው ያለው።

ከተያዙት ስደተኞች ውስጥ 26 ሴቶች እንዲሁም 5 ህፃናት እንደሚገኙበትም ተነግሯል።

የስደተኞች 2 አስክሬንም ተገኝቷል።

በዚህ ዓመት በጠቅላላ 3,791 ስደተኞች የተያዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 120ዎቹ ሲሞቱ ፣ ሌሎች 250 የሚሆኑት ጠፍተዋል መባሉን MDN ዘግቧል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1