Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.97K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2024-04-03 08:14:46
በአዲስ አበባ የቤት ሽያጭ ዋጋ ተመን ላይ በድጋሚ ማሻሻያ ተደረ

◉በአዲሱ መመሪያ መመሪያ 34 በመቶ የዋጋ ቅናሽ ተደርጓል 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፈው ዓመት ሰኔ 8 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው የቤት ሽያጭ ዋጋ ማሻሻያ ላይ ከሕብረተሰቡ በርካታ ቅሬታዎች በመቅረባቸው፣ መመሪያው በድጋሚ እንዲከለስ ተደርጓል። 

መጋቢት 23 ቀን 2016 ዓ.ም  በተሠራጨው አዲስ መመሪያ በኮንዶሚኒየም ቤቶች እና በአፓርታማዎች ሽያጭ የካሬ ሜትር ዋጋ ላይ በአማካኝ 34 በመቶ ቅናሽ ተደርጓል።

የከተማው መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ እና የመሬት ይዞታ ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ በጋራ ባካሄዱት ጥናት የተዘጋጀው ማኑዋል በቤት ሽያጭ ገቢ ላይ የዋጋ ቅናሽ እንዲያመጣ ተደርጓል።

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ይዞታ ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ግፋወሰን ደሲሳ ፊርማ ለሁሉም ክፍለ ከተሞች በተሰራጨው መመሪያ  እንደተመለከተው፣ ከዚህ በፊት በነበረው አሠራር ለአብነት ደረጃ አንድ በተባሉ አካባቢዎች የሚሸጥ የአንድ አፓርታማ ቤት  ዋጋ በካሬ ሜትር 132,200 ብር፣ በተመሳሳይ በዚሁ ደረጃ አንድ አካባቢ የኮንዶሚንየም ቤቶች ሽያጭ ዋጋ ደግሞ በካሬ ሜትር  72,300 ብር በሚል ቁርጥ ዋጋ ወጥቶላቸው የነበረ ሲሆን፣ በአዲሱ ማኑዋል ይህ ቁርጥ ዋጋ በ34 በመቶ እንዲቀንስ ተደርጓል።

የከተማው አስተዳደር የቤት ሽያጭ ግብይት ላይ አዲስ ማንዋል ለማውጣት የተገደደው፣  በግብይት ወቅት መሬት ላይ ያለው ዕውነታና የሚቀርበው የሽያጭ ውል እጅግ የተራራቀ በመሆኑ ነው ተብሏል። በቤት ግብይት ዙሪያ አሳንሶ መዋዋል፣ አሳንሶ መገመት፣ የስም ዝውውር ማዘግየትና ሌሎችም ተጠቃሽ ችግሮች መሆናቸው ተመልክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
39.0K views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 22:16:53
አዲሱ አዋጅ “ስለ መኖሪያ ቤት ኪራይ ውል” ዘመን ዝርዝር

ዛሬ በፓርላማ በጸደቀው “የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ” ከተዘረዘሩ ድንጋጌዎች ውስጥ፤ “የመኖሪያ ቤት የኪራይ ውል ዘመንን” የሚመለከቱት የሚጠቀሱ ናቸው። “የመኖሪያ ቤት ኪራይ የውል ዘመን ከሁለት ዓመት ሊያንስ አይችልም” ሲል የደነገገው አዋጁ፤ ይህ የተደረገበትን ዋነኛ ምክንያት በማብራሪያው ላይ አስፍሯል።

“የአዋጁ ዓላማ የመኖሪያ ቤት ኪራይ የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ በመሆኑ፤ ውሉ ከሁለት ዓመት ያነሰ ቢሆን አከራዩ ውሉን ለማደስ ፍቃደኛ ላይሆን ስለሚችል፤ ተከራይ በየጊዜው በቀጣይ ስለሚከራየው ቤት በመጨነቅ የተረጋጋ ህይወት እንዳይመራ ያደርገዋል” ሲል የአዋጁ ማብራሪያ አትቷል።

“ከሁለት ዓመት ያለፈ ዘመን ይኑረው ቢባል ደግሞ የአከራይን መብት እንዳይጫን፤ ሚዛናዊ በሆነ መልኩ የውል ዘመኑ ከሁለት ዓመት ያላነሰ ጊዜ እንዲሆን” መደረጉን የአዋጁ ማብራሪያ አስገንዝቧል።

“አዋጁ ከመውጣቱ በፊት ከሁለት ዓመት በታች የተደረጉ የቤት ኪራይ ውሎች ላይ ይህንን አዋጅ ተግባራዊ ማድረግ ፍትሐዊ ስለማይሆን፤ በውላቸው ላይ ያጸደቁት ቤት ኪራይ የውል ዘመን ተቀባይነት እንዲያገኝ ተደርጓል” ሲል ማብራሪያው አክሏል። ዝርዝሩን ከላይ ከተያያዘው ምስላዊ መረጃ ይመልከቱ።

Via Ethiopia Insider

@Esat_tv1
@Esat_tv1
41.0K views19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 21:31:57
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ121 ሺህ እስከ 95 ሺህ ገንዘብ ያለአግባብ የወሰዱና እስካሁን ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ አሰራጨ

በትላንትናው ዕለት 108 ሺህ እስከ 305 ሺህ ገንዘብ ወስደው ያልመለሱ ግለሰቦችን ፎቶግራፍ ማሰራጨቱ ይታወሳል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
41.3K views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 14:26:59
የተፈጠረው የነዳጅ እጥርት እስከ ነገ ጠዋት ድረስ ይቀረፋል

የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት

ከሰሞኑ በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች ማስተዋል የተለመደ ሆኗል።ይሄንንም ተከትሎ የረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች ምክንያት ምን እንደሆነ ለማወቅ ኢቢሲ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅትን አነጋግሯል፡፡የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ይስማ አለም ምህረቱ የነዳጅ እጥረት የተፈጠረው ጅቡቲ ላይ የዘነበውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ድልድይ በመሰበሩ ነው ብለዋል።

በተጨማሪም ነዳጅ የጫነ አንድ የነዳጅ ቦቴ ተገልብጦ መንገድ መዘጋጋት በማስከተሉ የነዳጅ እጥረት መከሰቱን አስረድተዋል፡፡ችግሩን ለመቅረፍ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች በድሬደዋ በኩል እንዲገቡ ተደርጓል ያሉት ስራ አስፈጻሚው ይሄንኑ ተከትሎ ትናንት ከሰአት ጀምሮ ነዳጅ የጫኑ ቦቴዎች መግባት መጀመራቸውን አረጋግጠዋል፡፡አክለውም ዛሬ እና ነገ ነዳጅ የጫኑ ተጨማሪ ቦቴዎች እንደሚገቡ እና ችግሩ እስከ ነገ ጠዋት ድረስ እንደሚቀረፍ ገልጸዋል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
44.3K views11:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 09:44:12
በፒያሳና አካባቢው እየተከናወነ ባለው ግንባታ ምክንያት መንገዱ ስለተዘጋ አሽከርካሪዎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ፖሊስ አሳሰበ

ቀደም ሲል የመንገዱን መዘጋት በተመለከተ መረጃ ቢሰጥም አሁንም አሽከርካሪ ዎች ወደ ግንባታ ቦታው እየመጡ በግንባታ ስራው ላይ ጫና እየፈጠሩ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በመሆኑም በፒያሳና አካባቢው የመንገድ ግንባታ እየተከናወነ በመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ መንገዱ ስለተዘጋ አሽከርካሪዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

በዚህም መሰረት፡-

• ከጊዮርጊስ አደባባይ በእሳት አደጋ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከቅድስተ ማርያም ወደ አራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር

• ከአራት ኪሎ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

• ከባሻ ወልዴ ችሎት ወደ ቱሪስት እና ወደ ቅድስተ ማርያም

• ከእሪ በከንቱ (ቀይ ባህር ኮንዶሚኒየም) ወደ ደጎል አደባባይ እንዲሁም

• ከደጎል አደባባይ ወደ ራስ መኮንን ድልድይ በሚወስዱት መንገዶች መግባት እና መንገዶቹን ለጊዜው መጠቀምም ሆነ በመንገዶቹ ላይ መኪና ማቆም እንደማይቻል ተገልጿል፡፡

ይህን በመገንዘብ አሽከርካሪዎች ከእነዚህ ውጪ ያሉ ሌሎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ ተባባሪ እንዲሆኑ ፖሊስ አሳስቧል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
20.7K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 09:44:10
[CREATINE MONOHYADRATE ]

ጡንቻን ለመገንባት እና ጉልበት ለማግኘት፤ ለሰውነትዎ የሚያስፈልገውን ይስጡት!

በፆም ወቅት የሚወሰድ!

ጥንካሬ፣ብርታት እና ፈጣን የሰዉነት ጥገና ያስፈልገኛል ብለዉ ካሰቡ ክሬቲን ይገባዎታል
የዘርፉ ባለሙያዎች ጥናት እንደሚያሳየዉ ክሬቲን የሚጠቀሙ አትሌቶች እና ስፓርተኞች 23 % የተሻለ አፈጻጸም እና ጥገና ያሳያሉ!

ለነፃ የምክር አገልግሎት እና የተሟላ መረጃ ወደ ጥሪ ማእከላችን ይደውሉልን
9369

አድራሻ አዳማ - ፖስታ ቤት ሶሬቲ ህንፃ ፊትለፊት ጀርመን ሲቲ ሞል 1ኛ ፎቅ ሱቅ ቁጥር 110

+251966113766

Join https://t.me/+RCaZ_Ka6SOrlz0u5
19.0K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 09:44:02
ነጋዴ ነዎት?
ቀጥታ ከውጭ ሀገር እቃ ማስመጣት ይፈልጋሉ?
ቋንቋ ባለመቻልዎ ምክንያት የደላላ ጣልቃ ገብነትስ መሮዎታል?
ወይስ ውጭ ሀገር ሔደው መስራት ይፈልጋሉ?

ሀሳብዎ ይህ ከሆነ የኛም ፍላጎት እርሶዎን ማስደሰት ነው። እንግሊዘኛ፣አማርኛ፣አፋን ኦሮሞ እና አረብኛ ቋንቋን ባሉበት ሆነው በኦንላይን ልናስትምርዎ እጅግ የላቀ ልምድ ያላቸውን መምህራን አዘጋጅተን እየጠበቅነዎት ነው።


@brighttraining90

ለመመዝገብ በእነዚህ ስልኮች በዋት ሳፕ፣ በኢሞ፣በቴሌግራም ያገኙናል
0933666662
0932878889
17.4K views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-02 09:43:48
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

0911248768   ይደውሉልን
17.1K views06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 22:01:23
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ108ሺ እስከ 305ሺ ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን ምስል ይፋ አደረገ

በባንኩ የሲስተም ማዘመኛ ሥራ ላይ የተፈጠረውን ክፍተት በመጠቀም መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ያለአግባብ ከባንካችን የወሰዱትን ገንዘብ እንዲመልሱ እስከ መጋቢት 21 ቀን 2016 ዓ.ም በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ መሠረት 10,857 የሚሆኑ ግለሰቦች ያለባቸውን ገንዘብ አጠናቀው መመለሳቸውን ባንኩ ገልጿል፡፡

ባንኩ "የተሰጠውን ተደጋጋሚ እድል ተጠቅመው ያላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦች አሉ ያለ ሲሆን ባንካችን ገንዘቡን ለማስመለስ በተከታታይ ስለሚወስዳቸው እርምጃዎች በተደጋጋሚ ባሳወቀው መሠረት እስካሁን ያላግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን የመጀመሪያ ዙር ፎቶግራፍ በባንካችን ድረ-ገጽ እና የማህበራዊ ትስስር ገፆች ለማውጣት ተገደናል ብሏል፡፡

በዚህ አጋጣሚ ባንካችን የተለያዩ ምክንያቶችን ግምት ውስጥ በማስገባት የገንዘብ መመለሻ ጊዜውን ለመጨረሻ ጊዜ እስከ መጋቢት 25 ቀን 2016 ዓ.ም ያራዘመ በመሆኑ፣ ይህን የመጭረሻ እድል ተጠቅማችሁ ገንዘቡን እድትመልሱ እያሳሰብን፣ በተሰጠው የጊዜ ገደብ የማይመልሱትን ወደ ህግ የምናቀርብ መሆኑን በድጋሚ እናሳስባለን ብሏል፡፡

ከ108ሺ እስከ 305ሺ ያለአግባብ የወሰዱትን ገንዘብ ያልመለሱ ግለሰቦችን ምስል ከዚህ በታች ባለው ሊንክ ይፋ አድርጓል።
https://combanketh.et/list-of-customers

@Esat_tv1
@Esat_tv1
29.1K views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-01 19:59:47
የኢትዮጵያ ነዳጅ አዳዮች ማህበር ፥ በአዲስ አበባ ከተማ የነዳጅ ዕጥረት መከሰቱንና ምክንያቱ ደግሞ ጅቡቲ ላይ የዘነበ ከባድ ዝናብን ተከትሎ የመንገድ መቆራረጥ በመፈጠሩ መሆኑን ገልጿል

በተጨማሪም አስቀድሞም ከቦታዉ በበቂ ሁኔታ ነዳጅ እየተጫነ ባለመሆኑ መሆኑን አመልክቷል።

የማህበሩ የቦርድ አባል አቶ ደሳለኝ አበባየሁ ፥ እነዚህ ምክንያቶች ከነዳጅ አቅራቢ ኩባንያዎች የተነገራቸዉ እንደሆነ ጠቁመዋል።

ችግሩ ለመስተካከል ጊዜ ይወስድ እንደሆን የተጠየቁት አቶ ደሳለኝ " ጉዳዩ ትልቅ ነዉ፤ እንደ ቀላል የሚታይ አይደለም ያሉን ሲሆን፤ በእርግጠኝነት መንግስትም ሌት ተቀን ርብርብ አድርጎ ነገሮችን ያስተካክላል ብለን ተስፋ እናደርጋለን " ብለዋል።

ከጅቡቲ ከሚመጣዉ በተጨማሪ ክምችት ውስጥ ነዳጅ አልነበረም ወይ ? የተባሉት አቶ ደሳለኝ፤ " ቤንዚን ከአዋሽ ፣ ከሱሉልታ ዲፖዎች ነው እየተጫነ ያለዉ ፤ አሁን ላይ ግን ከክምችት ለመጫን ያልፈለጉበት የራሳቸዉ ምክንያት ይኖራቸዋል ፤ መንግስትም ይህንን አይቶ መፍትሄ ይሰጣል ብለን እንጠብቃለን " ብለዋል።

" አንድ ያለን መንገድ የጅቡቲ ብቻ ነዉ " ብለው " መንገዱ የተበላሸ በመሆኑ ደግሞ የመቆራረጥ ችግር ያጋጥማል ከባድ ዝናብ ሲዘንብ ደግሞ ችግሩን ከፍ ያደርገዋል " ሲሉ ገልጸዋል።

" እንደዚህ ዓይነት ችግሮች የሚያግጥሙ በመሆኑ ለተወሰነ ጊዜ በትዕግስት ማለፍ አስፈላጊ ነው " ብለዋል።

ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ ረጃጅም የነዳጅ ሰልፎች እየተስተዋሉ ይገኛል።

ይህ መረጃ የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
32.1K views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ