Get Mystery Box with random crypto!

ESAT (ኢሳት🇪🇹)®

የሰርጥ አድራሻ: @esat_tv1
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 246.97K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2024-04-16 15:19:03
በኮሪደር ልማት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት ሆኑ

በአዲስ አበባ ከተማ በተወሰኑ አካባቢዎች እየተከናወኑ በሚገኙ የኮሪደር ልማት ሥራዎች ምክንያት ዝግ ሆነው የቆዩ መንገዶች ለተሽከርካሪ ክፍት መደረጋቸውን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በዚህም መሰረት፡-

ከደጃች ውቤ በአፍንጮ በር ወደ ራስ መኮንን ድልድይ

ከባሻወልዴ ችሎት በቱሪስት ሆቴል ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከዳኑ ሆስፒታል እስከ ቱሪስት ሆቴል በመውጣት ወደ ራስ መኮንን ድልድይ አፍንጮ በር

ከአራዳ መስተዳደር ወደ ዳኑ ሆስፒታል መውረጃ በአንድ አቅጣጫ ብቻ አሽከርካሪዎች መጠቀም እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ እየተከናወኑ ባሉ የልማት ሥራዎች ምክንያት ለአጭር ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ በጥብቅ መከልከሉንም ነው ፖሊስ ያሳሰበው፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1
45.8K views12:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-16 04:59:08 ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አብን የተሰጠ መግለጫ

ከትናንት ታሪካዊ ስህተቱ የማይማረው ህወሐት ለአራተኛ ዙር በህዝባችን ላይ ወረራ ፈፅሟል። የፌዴራልና የአማራ ክልል ክልሉ መንግስታትም በህዝብ ላይ የተቃጣውን የጥፋት ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

የኢትዮጵያ ህዝብ ዘላለማዊ ጠላት የሆነው ወያኔ ህወሐት በህዝብ ትግል ተገፍትሮ ወደ ትግራይ ከተሰበሰበ በኋላ በተደጋጋሚ ወረራ በመፈፀም በህዝባችን ላይ ለጆሮ የሚከብድ ዘግናኝ ግፍ ፈፅሟል። ምንም እንኳን ህወሐት በተደጋጋሚ ጊዜ በቆሰቆሰው ጦርነት የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቀጥታ የገፈቱ ቀማሽ ይሁኑ እንጅ ዋና ዓላማው ኢትዮጵያ ሐገራችንን መበታተን እና የፈራረሰች ሐገር መፍጠር መሆኑን በአፈ ቀላጤው በኩል በተደጋጋሚ ተናግሯል።

ይህ የእናት ጡት ነካሽ ቡድን የሐገራችን ደጀን የሆነውን የሰሜን እዝ የመከለከያ ሰራዊት በማጥቃቱ ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ያጋጠመውን ቁጣ መቋቋም ተስኖት ለሶስተኛ ጊዜ እየተመላለሰ ያደረገው የሐገር ማፍረስ ሙከራ ባይሳካለትም እንኳን አድፍጦ ለጦርነት ከመዘጋጀት ግን ቦዝኖ አያውቅም።

ህወሐት ከጦርነት ውጭ መኖር የማይችል፣ በጦርነት አድጎ በጦርነት ያረጀ ቡድን በመሆኑ በመላው የኢትዮጵያ ክልሎች የሚገኙ አማፂያንን ከማስታጠቅ አልፎ ከታሪካዊ ጠላቶቻችን ጋር በመወገን ሐገራችንን የጦር ቀጠና ለማድረግ ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ነበር የከረመው። በቀጥታ ከሚደግፋቸው የጥፋት ኃይሎች በተጨማሪ የራሱን ኃይል በማደራጀት የሰርጎ ገብ ኃይል እየላከ ህዝባችንን ሲረብሽ መክረሙ ሳያንሰው በአሁኑ ሰዓት በራያ በኩል ቀጥተኛ የሆነ ጥቃት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ ወረራ ከፍቶ ይገኛል።

ኋላ ቀርነት እና ግትርናት ዋና መገለጫው የሆነው የጥፋት ቡድን የሚሊዮኖችን ህይዎት በቀጠፈውና ከተደጋጋሚ ስህተቱ ባለመማር ዛሬም ለሌላ ዙር እልቂት ተዘጋጅቶ በህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል።

በህዝቦች እኩልነት እና በብሔረሰቦች መብት ፈፅሞ የማያምነው ህወሐት እኔ የማልገዛት ኢትዮጵያ ተረጋግታ መኖር የለባትም የሚል ያልተገራ ክፉ አመሉን በተደጋጋሚ አሳይቷል። በዚህም እንደ ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እኩልነትን ፈፅሞ እንደማይሻ አረጋግጧል።

ለህዝባችን የሚከተሉትን መልዕክቶች እናስተላልፋለን

1. ምንም እንኳን አሸባሪው እና ተስፋፊው ወያኔ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጠላት ቢሆንም ፣ በተለይ የአማራ ህዝብ የቡድኑ ወረራ ቀጥተኛ ሰለባ እና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ ጦርነቱን የመመከት ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በሁሉም አካባቢዎች የሚገኘው ሕዝባችን ካለፈው የጥፋት ግዜ በመማር ከታሪካዊ ጠላቱ የሚሰነዘርበትን ወረራ ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር በመቀናጀት እንዲመክት፣

2. ህዝባችን ከወያኔ ትጥቅ አስፈች ፕሮፖጋንዳ ራሱን እንዲጠብቅ እና ከዚህ ታሪካዊ ጠላት የሚመጣን ማንኛውንም ውዥንብር ጆሮ እንዳይሰጥ፣ ከዚህ ጋር በተያያዘ አንዳንድ የወገን ኃይሎች ለወያኔ የሚያሳዩትን የተለሳለሰ የባንዳነት መንገድ ህዝባችን ፈፅሞ እንዳያዳምጥ እና እንዲህ ያሉትን ቡድኖች አጥብቆ እንዲታገል፣

3. የአማራ እና የአፋር ህዝብ የጦርነቱ ዋና ገፈት ቀማሽ በመሆኑ የኢትዮጵያ ኃይሎች የሚፈልጉትን ሁሉ በማቅረብ ከሐገሩ ጎን እንዲቆም

4. ህዝባችን ይህን ታሪካዊ ጠላት በመቅጣት የተለመደ ጀግንነቱን እንዲወጣ ስንል ጥሪ እያቀረብን፤ በተለይ መንግስት በህዝባችን ላይ ለአራተኛ ጊዜ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በዝምታ የሚመለከት ከሆነ፤ ህዝባችን ስርአትን አምኖ ችግሮች ሁሉ በህግ አግባብ ይፈታሉ የሚል ቀናኢነቱ ማታለያ ሆኖ ከዋለ፤ ይህ በራያ ብቻ የማይቆም ይልቁንም የሁሉ ነገር መፍረሻና ማፍረሻ እንዲሆን መንግስት የፈቀደ መሆኑን ታሪክ የሚመዘግበው ሀቅ ይሆናል።

5. በህወሐት ችግር የአማራና የትግራይ ህዝቦች እንዲሁም መላ ሀገሪቱና ቀጠናው ችግር ውስጥ እየወደቀ በመሆኑ ይህ በአስቸኳይ እንዲቆም እያሳሰብን በተለይ የፌዴራሉ መንግስትና የአማራ ክልል መንግስት በህዝባችን ላይ እየተፈጸመ የሚገኘውን ወረራ በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አበክረን እንጠይቃለን!

ሚያዝያ 07/2016 ዓ.ም አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ

@Esat_tv1
@Eaat_tv1
21.3K views01:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 10:51:11
እስራኤል “ትክክለኛው ሰዓት ላይ” ለኢራን ጥቃት የአጸፋ ምላሽ እሰጣለሁ አለች

እስራኤል ልክ እንደ ኢራን ሁሉ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎችን በመተኮስ ‘ትክክለኛው ሰዓት ላይ’ የበቀል እርምጃ እውስዳለሁ አለች።ዓለም አቀፉ ማሕብረሰብ በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ውጥረት ከሚያባብስ እርምጃ እንዲቆጠቡ አገራት ቢያሳስቡም እስራኤል ግን ትክክል ሆኖ ሳገኘው የአጸፋ እርምጃ እውስዳለሁ ብላለች።

ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ በእስራኤል ላይ በፈጸመችው ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት ከ300 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ወደ እስራኤል ማስወንጨፏ ይታወሳል።ከ300 በላይ የሚሆኑት ሚሳኤሎች እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ እና ከየመን ወደ እስራኤል የተተኮሱ ቢሆንም አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ በእስራኤል፣ በአሜሪካ እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ ተደርገዋል።

ከኢራን የተወነጨፉ ሚሳኤሎችን በማምከን ድጋፍ ስታደርግ የነበረችው አሜሪካ እስራኤል የበቀል እርምጃ ብትወስድ ተሳታፊ አልሆንም ስትል አስታውቃለች።አምስት አባላት ያሉት የእስራኤል የጦር ካቢኔ እና የአገሪቱ ፓርላማ አባል ቤኒ ጋንትዝ ትክክለኛው ሰዓት ላይ ኢራን ለፈጸመችው ተግባር እስራኤል ዋጋ ታስከፍላታለች ብለዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
40.3K views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 10:51:10
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

0911248768   ይደውሉልን
37.8K views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-15 10:51:06
Niya Online payment

የተለያዩ እንደ SAT እና USMLE ያሉ የውጭ ፈተናዎችን ክፍያ ለመፈጸም ለ Scholarship application fee ለመክፈል ከ Alibaba, Amazon እና የመሳሰሉ የኦንላይን ገበያዎች ላይ ክፍያ ለመፈጸም እንዲሁም ለሌሎች ማንኛውንም በ online የሚከፈሉ ክፍያዎች ለመክፈል ፈልገው ተቸግረዋል

እንግዲያውስ እኛ ጋር መፍትሄ አለ!

በVisa card, Mastercard ወይም በ Payoneer እንደራስዎ ሆነን ክፍያዎን እንፈጽምሎታለን!

- በ ቴሌግራም  አድራሻችን @StraightouttaNazreth
-በ ስልክ ቁጥራችን +251934729413 ይደውሉ

Niya online payment
36.5K views07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 13:12:54 እስራኤል ከኢራን የተወነጨፉባትን 300 ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ሚሳኤሎች ማክሸፏን ገለጸች

እስራኤል በራሷና አጋሮቿ በኢራን ከተወነጨፉባት ከ300 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖች እና ሚሳኤሎች ውስጥ 99 በመቶውን ማክሸፍ መቻሏን አስታውቃለች።

ይሁንና በግዛቷ ላይ አነስተኛ መጠን ያለው ድብደባ እንደተፈፀመና በዚህም በደቡባዊ እስራኤል የሚገኘው የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት ካምፕ መመታቱን አንዲት ሕፃንም መቁሰሏን ገልፃለች።

ኢራን በእሥራኤል ላይ ጥቃት መሠንዘር መጀመሯን ተከትሎም መረጃዎች ተከታትለው በመውጣት ላይ ይገኛሉ።
እሥራኤል እየተሰነዘረባት ካለው ጥቃት የተነሳ አየር ክልሏን መሉ በሙሉ ዝግ ማድረጓ ተሰምቷል።

የመካከለኛው ምሥራቅ ሀገራት ላልተወሰነ ጊዜ የአየር ወሰናቸውን ዝግ ያደረጉ ሲሆን፤ ሶሪያ ፣ ኢራቅ ፣ ዮርዳኖስ እና ግብፅ የአየር ክልሎቻቸውን በጊዜያዊነት በመዝጋትም ከፍተኛ ተጠንቀቅ አውጀዋል።
ኢራን በእሥራኤል ላይ ከድሮንና የሚሳዔል ጥቃቶች በተጓዳኝ፤ የሳይበር ጥቃት መፈፀሟም ተነግሯል።

ከቴህራን የሚወጡ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት፤ በእሥራኤል የመከላከያ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሳይበር ጥቃት ተፈፅሟል።
ይሁንና ይህን የሳይበር ጥቃት ትክክለኝነት እስካሁን ከገለልተኛ አካል ማረጋገጥ አለመቻሉ ተመላክቷል።

መዳረሻቸውን ወደ እሥራኤል ያደረጉ የኢራን ድሮኖች እንደ ግሪሣ ወፍ ምሽቱን በኢራቅ ሰማይ ላይ በብዛት የታዩ ሲሆን፤ ከዋክብት እንጂ ድሮኖች የማይመስሉበትን ምስል የኢራኑ ታዝኒም የዜና አውታር ይዞ ወጥቷል።

የአየር እና የባሕር ኃይል ምድብ ጣብያዎች እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ መኖሪያ የኢራን ጥቃት ዒላማ ተብለው ከተገመቱት መካከል እንደሚጠቀሱም ተመላክቷል።
ኢርና የዜና ምንጭ እንደዘገበው ከሆነ፤ ኢራን ወደ እሥራኤል ባላስቲክ ሚሳዔሎችን ማስወንጨፍ ጀምራለች።

ከኢራን እየተሠነዘረ ባለው ጥቃት ቅድሚያ ተጠቂ ሊሆኑ ከሚችሉ አካባቢዎች ዜጎች እንዲርቁና ፡ ጥቃትን በሚቀንሱ መከለያዎች ውስጥ እንዲቆዩ ሲል የእሥራኤል መከላከያ ሠራዊት ለዜጎች ትዕዛዝ መስጠቱም ተነግሯል።

ለኢራን ጥቃት ተጋላጭ ናቸው ከተባሉት የእሥራኤል ይዞታዎችና ግዛቶች መካከል የጎላን ኮረብታዎች ፣ ኔቫቲም ፣ ዲሞና ፣ ኤይላትና በዙሪያቸው ያሉ ነዋሪዎች መሽገው እንዲቆዩ የእሥራኤል ጦር ለሀገሪቱ ዜጎች አሳስቧል።

ትናንት ምሽቱን ጥቃት የጀመረችው ኢራን ከ300 በላይ ሰው አልባ አውሮፕላኖችና ሚሳኤሎችን ወደ እሥራኤል አስወንጭፋለች።

ይሁንና ሰው አልባ አውሮፕላኖቹና ሚሳኤሎቹ የእሥራኤልን የአየር ክልል ከመጣሳቸው በፊት በእስራኤል በራሷና በአጋሮቿ በአሜሪካ፣ በብሪታንያ፣ በፈረንሳይ እና በዮርዳኖስ የአየር መከላከያ ኃይሎች እንዳከሸፏቸው አንድ የእሥራኤል መከላከያ ከፍተኛ ሹም ለ ዘ ታይምስ ኦቭ እሥራኤል ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
47.6K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 08:34:55
ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች

ከሰምኑ ውጥረት ውስጥ በከረሙት  ኢራንና እስራኤል መካከል ጦርነቱ ስድስት ሰአት ተኩል ላይ በይፋ ጀምሯል።

ኢራን ወደ እስራኤል በሺወች የሚቆጠሩ  ሮኬት እና ሚሳኤሎችን ተኩሳለች።

የሊባኖሱ ሄዝቦላህ በእስራኤል ቁጥጥር ስር ወደሚገኙት  የጎላን ተራሮች በደርዘን የሚቆጠሩ  ሮኬቶችን እየስወነጨፈ ነው።

አሜሪካ ተጨማሪ ሃይሏን ወደ መካከለኛው ምስራቅ አስጠግታለች።

ኢራቅና ዮርዳኖስ   የአየር ክልላቸውን  በጊዜያዊነት ዘግተዋል።

የእስራኤል የአየር ክልልም ከደቂቃዎች በኋላ ሙሉ ለሙሉ ይዘጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ድሮኖች ወይም ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወደ እስራኤል ለመድረስ 1 ሺህ 800 ኪ.ሜ. ርቀት ያህል መጓዝ የሚኖርባቸው ሲሆን ፥ ይህም ሰዓታት ሊወስድ እንደሚችልም ነው የተገለፀው።

አልጀዚራ እያንዳንዱን ክስተት በቀጥታ ስርጭት እያስመለከተ ነው።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
48.1K viewsedited  05:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 16:00:11
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ

ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረዉን ደንብ በመሻር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ለሚሰጣቸው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታዉቋል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አዲሱ ደንብ ከመዉጣቱ በፊት ሲሰራበት የነበረዉን የሰነዶች ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያን በመሻር ማሻሻያዉ ከሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለሚሰጣቸው የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያ ለመወሰን ባወጣዉ በዚህ ደንብ በተቀመጠው አዲሱ የክፍያ መጠን የሰነድ አይነቶቹ ቢለያይም ለሁሉም አገልግሎቶች ከ 200 ብር ጀምሮ እስከ 500 ብር ድረስ ክፍያን ይጠይቃል።

ካፒታል በተመለከተዉ በዚህ ደንብ ላይ ለሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዉል ሰነድ ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ሽያጭ ፣ ለመመስረቻ ፅሁፍ ሰነድ እና በስጦታ መልክ ለሚሰጡ ንብረቶች ዉል ሰነድ የክፍያ አገልግሎት ተመን ከወጣላቸው መካከል ዉስጥ ተካተዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1
27.4K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 16:00:08
Niya Online payment

የተለያዩ እንደ SAT እና USMLE ያሉ የውጭ ፈተናዎችን ክፍያ ለመፈጸም ለ Scholarship application fee ለመክፈል ከ Alibaba, Amazon እና የመሳሰሉ የኦንላይን ገበያዎች ላይ ክፍያ ለመፈጸም እንዲሁም ለሌሎች ማንኛውንም በ online የሚከፈሉ ክፍያዎች ለመክፈል ፈልገው ተቸግረዋል

እንግዲያውስ እኛ ጋር መፍትሄ አለ!

በVisa card, Mastercard ወይም በ Payoneer እንደራስዎ ሆነን ክፍያዎን እንፈጽምሎታለን!

- በ ቴሌግራም  አድራሻችን @StraightouttaNazreth
-በ ስልክ ቁጥራችን +251934729413 ይደውሉ

Niya online payment
26.4K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 16:00:02
መኪና ለመግዛት ወይም ለመሸጥ ከፈለጉ ያለምንም ክፍያ
ይህንን የቴሌግራም መተግበሪያ ይቀላቀላሉ።

https://t.me/Poppycarmarket

0911248768   ይደውሉልን
25.1K views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ