Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-04-28 07:16:54
2 views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 16:08:43 ትንሽ ለግንዛቤ
የ15 ቱ አበው ነብያት ስም
1-ቅዱስ አዳም አባታችን
2- ቅዱስ ሴት
3- ቅዱስ ሔኖስ
4- ቅዱስ ቃይናን
5-ቅዱስ መላልኤል
6- ቅዱስ ያሬድ
7- ቅዱስ ኄኖክ
8- ቅዱስ ማቱሳላ
9- ቅዱስ ላሜሕ
10- ቅዱስ ኖህ
11- ቅዱስ አብርሃም
12- ቅዱስ ይሳሐቅ
13- ቅዱስ ያዕቆብ
14- ቅዱስ ሙሴ
15- ቅዱስሳሙኤል ናቸው : :

የ4 ቱ ዐብይት ነብያት
1- ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃለ
2- ቅዱስ ኤርሚያስ
3- ቅዱስ ሕዝቅኤል
4- ቅዱስ ዳንኤል ናቸው : :

12 ደቂቀ ነብያት
1- ቅዱስ ሆሴይ
2- ቅዱስ አሞጽ
3- ቅዱስ ሚክያስ
4- ቅዱስ ዮናስ
5- ቅዱስ ናሆም
6- ቅዱስ አብድዩ
7- ቅዱስ ሶፎንያስ
8- ቅደስ ሐጌ
9- ቅዱስ ኢዮኤል
10- ቀዱስ ዕንባቆም
11- ቅዱስ ዘካርያስ
12- ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው : :

የ8 ቱ ካልአን ነብያት
1- ቅዱስ ኢያሱ
2- ቀዱስ ሶምሶን
3- ቀዱስ ዮፍታሔ
4- ቅዱስ ጌዴዎን
5- ቅዱስ ዳዊት
6- ቅዱስ ሰለሞን
7- ቅዱስ ኤልያስ
8- ቅዱስ ኤልሳዕ ናቸው : :
በረከታቸው ይደርብን !
3 views13:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 11:04:40
“በኡባልም ወንዝ መካከል። “ገብርኤል ሆይ”፥ ራእዩን ለዚህ ሰው አስታውቀው ብሎ የሚጮኸውን የሰውን ድምፅ ሰማሁ። እኔም ወደ ቆምሁበት ቀረበ፤ በመጣም ጊዜ ፈርቼ በግምባሬ ተደፋሁ፤ እርሱም። የሰው ልጅ ሆይ፥ ራእዩ ለፍጻሜ ዘመን እንደ ሆነ አስተውል አለኝ። ሲናገረኝም ደንግጬ በምድር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ፤ እርሱም ዳሰሰኝ ቀጥ አድርጎም አቆመኝ። እንዲህም አለኝ። እነሆ፥ በመቅሠፍቱ በመጨረሻ ዘመን የሚሆነውን አስታውቅሃለሁ፤ ይህ ለተወሰነው ለፍጻሜ ዘመን ነውና።”
ት/ዳን.፰፡፲፮-፲፱ (8፡16-19)
4 views08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 09:45:22
እዉነቱ ይሄ እና ይሄ ብቻ ነዉ
4 views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 07:03:16 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ✞✞✞

አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)

ልዩ ስሟ አምዓዳ በምትባል ሀገር በሉፊ አውራጃ በሮም አገር አንድ ጽኑ ክርስቲያን ነበር፡፡

ይህ ክርስቲያን ስሙ አብርሃም ይሰኛል፡፡ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከአንዱ አገር ወደ ሌላ አገር ሲሰደድ የኖረ እግዚአብሔርን የሚፈራ ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ ለነዳይና ለምስኪን ባልቴቶች እናት አባት ለሞቱባቸዉ ልጆች ምጽዋትን የሚሰጥ ነበር፡፡

እንዲሁም እንደርሱ ደግ የሆነች ስሟ ሐሪክ የምትባል ደግ ሚስት ነበረችው የስሟ ትርጉምም  በክርስቶስ የታመነች ማለት ነው፡፡ 

እነዚህ ሁለት ደግ ክርስቲያኖች ታዲያ ልጅ አልነበራቸውም ነገር ግን
ልጅ ባይኖራቸውም እለት እለት እግዚአብሔርን ከማመስገን በቀር አማረው አያውቁም ነገር ግን ለቤተ እግዚአብሔር  አገልጋይ የሚሆን አንድ ልጅ ይሰጣቸው ዘንድ በአንቃዕድዎ ወደ እግዚአብሔር ይለምኑ ነበር፡፡

አንድ ቀን መልዐከ እግዚአብሔር ለዚህ   ደግ ሰው ተገልፆ ይኽ ፍሬ የአንተ ነው እርሱም ወደ እኔ የሚቀርብ እግዚአብሔርን የሚያስደስት ፈቃዱንም የሚፈፅም ያማረ መባዕ ነው ብሎ እጅግ መልካም ፍሬን በእጁ ሰጠው፡፡

ይኽ ደግ ሰው አብርሃምም ከእንቅልፉ ተነስቶ ይህንን  በህልሙ የሰማውንና የአየውን ነገር ኹሉ ለሚስቱ ሐሪክ ነገራት እርሷም ታላቅ ደስታ ተደሰተች ልዑል እግዚአብሔርን በአንድነት አመሰገኑ፡፡ሚስቱ ሐሪክም ፀነሰች፡፡

ይኽቺ ሚስቱ ሐሪክ በፀነሰች ጊዜም በቤታቸው መካከል ሁለንተናው መልካምና ታላቅ ዛፍ በቀለ በቅጠሉ ላይ በዕብራይስጥ ቋንቋ የተጻፈ ጽሕፈትን አዩ ጽሕፈቱም በጽዮን አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ቅዱስ የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላ የሚል ነው፡፡

ከዚህም በኀላ ሐሪክ መልከ መልካምና ከብርሃናት ይልቅ ፊቱ የሚያበራ ወንድ ልጅን ወለዱ፡፡እናቱና አባቱ ይህንን በአዩ ጊዜ ታላቅ ደስታ ተደስተው ለነዳያን ምጽዋትን ለአብያተ ክርስቲያናት የሚገባውን በወርቅና በብር ያጌጡ የነዋየ ቅድሳት አልባሳትን ሰጡ ስሙንም ቡላ ብለው ሰየሙት፡፡ትርጓሜውም ለእግዚአብሔር የተለየ ማለት ነው፡፡

እናትና አባቱም በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት አሥር አመት በሆነው ጊዜም በመጀመሪያ አባቱ አብርሃም አረፈ ከትንሽ ቀናት በኀላ እናቱ ሐሪክ አረፈች፡፡

በዚያን ዘመን ታዲያ ንጉሡ ቤተ ክርስቲያንን እንዲዘጉ እና ቤተ ጣዖት እንዲከፍቱ ክርስቲያን ሁላቸው የምስጋና ባለቤት ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን (ሎቱ ስብሐት) እንዲክዱ የሚል ወደዚያች አገር ደረሰ፡፡

ይህ የተባረከ ብላቴና ቡላም ይህንን በሰማ ደጋጎች ክርስቲያንም ሲሰቃዩ ባየ ጊዜ ስለ ክርስቶስ በሰማዕትነት ይሞት ዘንድ ጨክኖ ሕዝብን ሰማዕትነት ለመቀበል በወዲህም በወዲያም ያሉትን ሕዝቡን እየገፋ ሄዶ ንጉሥ አቅሮጵስ ካለበት ቀርቦ ያፈርክና የተዋረድክ የረከስክ የጽድቅ ሁሉ ጠላት የዲያቢሎስ መልእክተኛ አንተና ንጉስክ የተነቀፋችሁ የምታመልኳቸው ጣዖታትም የተዋረዱና በምድር የረከሱ ናቸው አለው፡፡

ንጉሡም ሰምቶ ይህንን ወጣቱ ቡላን አስረው ከፊቱ ያቆሙት ዘንድ አዝዞ ተመልከቱ የእሊክ ክርስቲያን ልቦናቸው የጸና ነው ትንሽ ብላቴና ሆኖ ሳለ ምንም አልፈራም ይልቁኑም እንድቀጣው ይቃወመኛል እንጂ አለ፡፡

ይህንንም ብሎ በሚቆራርጥ ብረት ሠንሰለት አሰሩት ጀርባውን በአለንጋ እንዲገርፉት ሰውነቱም እየለያዩ እየቆራረጡ የውስጥ አንጀቱን በተቆለፈ ብረትና በስለታማ መጋዝ እጆቹንና እግሮቹን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ፡፡

በእንዲህ ባለ መከራ ቢያሰቃዩትም ተመልሶ በእግሩ ይቆማል እንጂ አልሞተም ንጉሡ እሊህ ክርስቲያን መተታቸውን ተመልከቱ አለ፡፡

እንዲሁም አባ ቡላ በአሥራ አምስት አመቱ ከሌላ ንጉሥ ጋር እንደ ቀድሞ ለረከሱ ጣዖቶች አልሰግድም በማለቱ ብዙ ስቃይ አሰቃየው በመጨረሻም አንገቱን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ብጹዕ ጻድቅ ቡላም ራሱን ከመቁረጣቸው አስቀድሞ ከመዝሙረ ዳዊት ሳምኬት ዐማፅያንን ጠልቼ ሕግህን ተከተልኩ ረዳቴና መጠጊያዬ አንተ ነህ በቃልህም አመንኩ የአምላኬን ትዕዛዝ እፈፅም ዘንድ  ዐማፅያን ከእኔ ራቁ በሕይወት እኖር ዘንድ እንደ ቃልህ ተቀበለኝ ተስፋዬንም አታስቀርብኝ ርዳኝ አድነኝ ሁል ጊዜ ሕግህን እናገራለሁ ከትእዛዝህ የሚርቁ ሁሉ ምኞታቸው አመፃ ነውና አዋረድኻቸው እሊኽ በምድር ያሉ ኃጥአን ከዳተኞች ናቸው፡፡ ስለዚህም አምልኮተ ሕግህን ወደድኹ፡፡ከሕግህ የተነሣ ፈርቻለሁና በአንተ መታመንን ከሰውነቴ ጋራ አስማማ፡፡ የሚለውን ጸሎት ጸለየ፡፡

የእግዚአብሔር አገልጋይ ቡላም በዚህች ቀን በሚያዝያ 18 አንገቱን ተቆረጠ በዚህን ጊዜ መልአከ እግዚአብሔር ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም ወርዶ ራሱን ወስዶ ከሥጋው ቢያገናኘው እንደነበረ ሆኖ ተነሣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤልም አይዞህ አትፍራ እመን ጽና እግዚአብሔር ይረዳሃል ፡፡በሃገሪቱ ዳረቻ ወደ አለዉ ገዳም ሂድ እኔ የምሰጥህ በእጄ ያለች ልብስህ ሁል ጊዜ ይህች ናት ጌታችን ከወዳጆቹ ቅዱሳን መነኮሳት ጋራ ተሳታፊ እንድትሆን አዝዞኻል ብሎ የብርሃን መስቀል ምልክት ያላት አስኬማንም ሰጥቶት ከእርሱ ዘንድ ተሰወረ፡፡

ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ(ቡላ) ጌታችንና መድኃኒታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱ መፍቅሬ ሰብእ (ሰውን ወዳጅ) አምላካቸውን አርአያ ያደረጉ ለሰው ያላቸውን ፍቅር አድንቆ ከማዕድ በኀላ ስብሐት ተብሎ የተረፈውን በእንተ አቡነ አቢብ ብሎ ሦስት ጊዜ የተመገበውን ሰው ሁሉ እስከ አሥር ትውልድ እምርልሃለሁ ብሎ ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡

የንዑድ ክቡር ጻድቁ አባታችን አቡነ አቢብ (ቡላ) ጸሎታቸዉና በረከታቸው ከእኛ ጋር ይኹን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ ✞
4 views04:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 14:40:01 ትንቢተ አሞጽ Amos 9

ምዕራፍ፡9።
1፤ጌታን፡በመሠዊያው፡አጠገብ፡ቆሞ፡አየኹት፤ርሱም፡እንዲህ፡አለ፦መድረኮቹ፡ይናወጡ፡ዘንድ፡
ጕልላቶቹን፡ምታ፥በራሳቸውም፡ዅሉ፡ላይ፡ሰባብራቸው፤እኔም፡ከነርሱ፡የቀሩትን፡በሰይፍ፡
እገድላለኹ፤የሚሸሽ፡አያመልጥም፥የሚያመልጥም፡አይድንም።
2፤ወደ፡ሲኦል፡ቢወርዱ፡እጄ፡ከዚያ፡ታወጣቸዋለች፤ወደ፡ሰማይም፡ቢወጡ፡ከዚያ፡አወርዳቸዋለኹ፤
3፤በቀርሜሎስም፡ራስ፡ውስጥ፡ቢሸሸጉ፡ፈልጌ፡ከዚያ፡አወጣቸዋለኹ፤በጥልቅ፡ባሕርም፡ውስጥ፡ከዐይኔ፡
ቢደበቁ፡ከዚያ፡እባቡን፡አዛ፟ለኹ፥ርሱም፡ይነድፋቸዋል፤
4፤በጠላቶቻቸውም፡ፊት፡ተማርከው፡ቢኼዱ፡ከዚያ፡ሰይፍን፡አዛ፟ለኹ፥ርሱም፡ይገድላቸዋል፤ዐይኔንም፡
በእነርሱ፡ላይ፡ለክፋት፡እንጂ፡ለመልካም፡አላደርግም።
5፤የሰራዊት፡ጌታ፡እግዚአብሔር፡ምድርን፡ይዳስሳል፡ርሷም፡ትቀልጣለች፥የሚኖሩባትም፡ዅሉ፡
ያለቅሳሉ፤መላ፟ዋም፡እንደ፡ግብጽ፡ወንዝ፡ትነሣለች፥ደግሞ፡እንደ፡ግብጽ፡ወንዝ፡ትወርዳለች።
6፤አዳራሹን፡በሰማይ፡የሠራ፥ጠፈሩንም፡በምድር፡ላይ፡የመሠረተ፥የባሕርንም፡ውሃ፡ጠርቶ፡በምድር፡ፊት፡
ላይ፡የሚያፈሰ፟ው፡ርሱ፡ነው፤ስሙም፡እግዚአብሔር፡ነው።
7፤የእስራኤል፡ልጆች፡ሆይ፥እናንተ፡ለእኔ፡እንደ፡ኢትዮጵያ፡ልጆች፡አይደላችኹምን፧ይላል፡
እግዚአብሔር፦እስራኤልን፡ከግብጽ፡ምድር፥ፍልስጥኤማውያንንም፡ከከፍቶር፥ሶርያውያንንም፡ከቂር፡
አላወጣኹምን፧
8፤እንሆ፥የጌታ፡የእግዚአብሔር፡ዐይኖች፡በኀጢአተኛ፡መንግሥት፡ላይ፡ናቸው፥ከምድርም፡ፊት፡
አጠፋታለኹ፤ነገር፡ግን፥የያዕቆብን፡ቤት፡ፈጽሜ፡አላጠፋም፥ይላል፡እግዚአብሔር።
9፤እንሆ፥አዛ፟ለኹ፥እኽልም፡በወንፊት፡እንዲነፋ፡የእስራኤልን፡ቤት፡በአሕዛብ፡ዅሉ፡መካከል፡
እነፋለኹ፤ነገር፡ግን፥አንዲት፡ቅንጣት፡በምድር፡ላይ፡አትወድቅም።
10፤ክፉው፡ነገር፡አይደርስብንም፥አያገኘንምም፡የሚሉ፡የሕዝቤ፡ኀጢአተኛዎች፡ዅሉ፡በሰይፍ፡ይሞታሉ።
11፤በዚያ፡ቀን፡የወደቀችውን፡የዳዊትን፡ድንኳን፡አነሣለኹ፥የተናደውንም፡ቅጥሯን፡
እጠግናለኹ፤የፈረሰውንም፡ዐድሳለኹ፥እንደ፡ቀደመውም፡ዘመን፡እሠራታለኹ፤
12፤ይኸውም፡የኤዶምያስን፡ቅሬታ፥ስሜም፡የተጠራባቸውን፡አሕዛብን፡ዅሉ፡ይወርሱ፡ዘንድ፡ነው፥ይላል፡
ይህን፡የሚያደርግ፡እግዚአብሔር።
13፤እንሆ፥አራሹ፡ዐጫጁን፥ወይን፡ጠማቂውም፡ዘሪውን፡የሚያገኝበት፡ወራት፡ይመጣል፥ይላል፡
እግዚአብሔር፤ተራራዎችም፡በተሓውን፡የወይን፡ጠጅ፡ያንጠባጥባሉ፥ኰረብታዎችም፡ዅሉ፡ይቀልጣሉ።
14፤የሕዝቤን፡የእስራኤልን፡ምርኮ፡እመልሳለኹ፥የፈረሱትንም፡ከተማዎች፡ሠርተው፡
ይቀመጡባቸዋል፤ወይንንም፡ይተክላሉ፥የወይን፡ጠጁንም፡ይጠጣሉ፤አታክልትንም፡ያበጃሉ፥ፍሬውንም፡
ይበላሉ።
15፤በምድራቸውም፡እተክላቸዋለኹ፥ከእንግዲህም፡ወዲህ፡ከሰጠዃቸው፡ከምድራቸው፡አይነቀሉም፥ይላል፡
አምላክኽ፡እግዚአብሔር፨
5 views11:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 12:21:44
5 views09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 12:21:44
በጌምድር ጎንደር ስማኝ ባዶ እንዳትቀር ፤
ጎጃምና ሸዋ ስማኝ ባዶ እንዳትቀር፤
አንተ ቤተአምሐራ ስማኝ ባዶ እንዳትቀር ፤
ከዐረቦቹ በፊት ኦሮሞ ሊወርህ
መምጫ መድረሻውን ሌትከቀን ሲመክር፤
ባዶ እጅህን ሆነህ ተው አታንቀላፋ
መንግስት አለኝ ብለህ ሳታደርግ ተስፋ
ተዘጋጅተህ ጠብቅ ባንድነት በይፋ ፡፡
ጎንደር ተነስና ንገረው ለጎጃም
ጎጃም ተነስና ንገረው ለሸዋ
ሸዋ ተነስና ንገረው ለወሎ
ተዘጋጅቶብሃል ሊወርህ ኦሮሞ
በዓብይ አትታለል ንቃበት በቶሎ፡፡
ትግሬ እና ኦሮሞ መጥፊያቸው አንድ ነው
የሁላችን ጠላት ዐረብ ሲገባ ነው፡፡
የአባ አምሃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ድንገተኛ መልእክት
ቁጥር አራት ገጽ 7
ሚያዝያ 3 /8/2013 ዓ፡ም የተጻፈ፡፡
5 views09:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 06:30:45

"እንበለ ኪዳንኪሰ ወመስቀለ ክርስቶስ ወራሲ፡፡
አልቦ እምሲዖል ዘይድኅን ብእሲ፡፡"

/ እመቤቴ . . .... ባንቺ ኪዳን ያላመነ፤ በመስቀለ ክርስቶስም ያልታመነ እንዴት ከሲዖል መዳን ይቻለዋል!? /
1 view03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 22:01:10 ሥርዓተ ቤተክርስቲያን
1.ጫማ ተደርጎ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት ክልክል ነዉ።
ዘጽ.3፥5-6
የሐዋ.7፥39
፪ኛ ዜና 7፥14
2.ለሃጩን የማዝረክረክ ነዉር ያለበት ሰዉ ቤተክርስቲያን መግባት ክልክል ነዉ።
3.በቤተ ክርስቲያን አጸድ ግብዣ ማድረግ አይገባም።ፍት.ነገ አንቀጽ 1..ክርስቶስ ሥጋና ደም በሚሰዋበት ምዕመናን ሥጋ ወደሙን ከሚቀበሉበት ከቤተክርስቲያን ራቅ ብሎ በደረጃ ሰላም አቅራቢያ በዓዉደ ምሕረት ላይ ሥጋዊ መብል መጠጥ ማቅረብ መብላት አይገባም።
4.የቤተክርስቲያን መገልገያ ንዋያተ ቅዱሳት ለግል አገልግሎት ማዋል አይገባም።
ዳን.5፥31-35
ፍት ነገ አንቀጽ 1 አስጣ 28
5.በቅጽረ ቤተክርስቲያን ገበያ መገበያየት አይገባም።
ዮሐ.2፥14-17
ፍት.ነገ.አንቀጽ1
6.በቤተ መቅደስ በማኅበር ጸሎት ወቅት የግል ጸሎት ማድረግ ክልክል ነዉ።
7.ከቤተ መቅደስ በቅዳሴ ስዓት አሀዱ ከተባለ ጊዜ ጀምሮ አቋርጦ መዉጣትም ሆነ መንቀሳቀስ ክልክል ነዉ።
ማቴ.26፥26
ዕንባ.2፥20
8.ሴት ልጅ በወር አበባ ወቅት ወደ ቤተ መቅደስ መግባት አይፈቀድላትም።
ዘሌዋ.15፥18-30
ፍት.ነገ.አንቀጽ.14፥583
9.ወንድ ልጅ ሕልመ ሌሊት /ዝንየት/ ከመታዉ በዕለቱ ወደ ቤተ መቅደስ ከይገባም።
ዘሌዋ.15፥2-18
10.የሌሊት ልብስ /የአረማዉያን ልብስ/ ለብሶ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት ክልክል ነዉ።
፩ኛ ቆሮ.11፥5-14
11.ባልና ሚስት ከተራክቦ በኋላ ዕለቱን ወደ ቤተ መቅደስ ለመግባት አይፈቀድላቸዉም።ጋብቻ ቅዱስ መኝታዉም ንጹሕ ሲሆን በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት ከተራክቦ በኋላ ዕለቱን ወደ ቤተ መቅደስ መግባት አይቻልም።ቅዱስ ጳዉሎስ "ለጸሎት በመፈቃቀድ ካልሆነ በስተቀር ባልና ሚስት አይከላከሉ" እንዳለዉ ባልና ሚስት ከተራክቦ የሚርቁት በበዓላት፤በአጽዋማት ለጸሎትና ለቅዳሴ በሚዘጋጁበት ዕለታት በሰንበት ነዉ።ስለዚህ ጠዋት ለቅዳሴ በሚዘጋጁበት ጊዜ እራሳቸዉን ሊጠብቁ ይገባል።
፩ኛ ቆሮ.7፥5
ኩፋሌ.34፥12
ዘጸ.19፥15
12.በቤተ መቅደስ ዉስጥ መሳቅ፤መሳለቅ፤ዋዛፈዛዛ ነገር መነጋገር ክልክል ነዉ።ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በምድርዊ ንጉሥ ፊት በቆምክ ጊዜ በምንም ምክንያት ቢሆን ለመሳቅ አትደፋፈርም ታዲያ በሰማያዊ ንጉሠ ነገሥት ፊት ትስቃለህን?ብሏል።
ተግሳጽ ዘዮሐንስ አፈወርቅ አንቀጽ ስድስት(6) በቅዳሴ ስዓት ጊዜ የሚስቅ ዓለማዊ ቢሆን ወደ ዉጭ ያዉጡት ከቅዱስ ምስጢር/ከቁርባኑ/አያቀብሉት ተብሏል።
ቀኖና ባስሌዎስ አንቀጽ 79
13.አብዝቶ ጠጥቶና ሰክሮ መግባት ክልክል ነዉ።እንዳትሞቱ ወደ መገናኛዉ ድንኳን ስትገቡ አንተና ልጆችህ የወይን ጠጅና የሚያሰክር ነገር ሁሉ አትጠጡ።
ዘሌዋ.10፥8-10
ሉቃ.21፥34
ምሳሌ.23፥29-35
ይሁንና ይህን ወይን አትጠጣ ቀምሰህ ፈጣሪህን ለማመስገን ያህል ብቻ ይሁን እንጂ እንደ ጢሞቴዎስ ብትታመም ከገድል ጽናት የተነሳ ጽኑ ደዌ ብትያዝ።ግን ከወይን ጥቂት ጠጣ እርሱ ለሥጋ ሕይወት ይሆንሃልና።
፩ኛ ጢሞ.5፥24
ሃይማኖት አበዉ ዘሠለስቱ ምዕት 21፥17-18
14.በቂም በቀል ሰዉን አስቀይሞ የሰዉ ገንዘብ በማጭበርበር ወስዶ ቤተክርስቲያን መጥቶ መጸለይ ክልክል ነዉ።
ማቴ.5፥23-24
ማር.11፥25
ሉቃ.18፥9-14
15.ወደ እግዚአብሔር ቤት በገባህ ጊዜ እግርህን ጠብቅ ከተቀደሰ ስፍራ እንደቆምክ አስተዉል።
መክ.5፥1

"ቤተ ክርስቲያን የመሳለም ስርዓት"
ጠዋትና ማታ ቤተክርስቲያንን ለመሳለም መትጋት ያስፈልጋል።ምሳ.8፥34
ወደ ቤተክርስቲያን ሲገባ ከቅጽረ ቤተ ክርስቲያኑ በር ላይ ሲደርሱ መሳለም ይገባል።
መዝ.28፥2፣95፥9
ኤር.26፥2
ሕዝ.46፥3
ፊልጵ.2፥9-10
ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ ጫማ አዉልቆ ወገብን ታጥቆ አደግድጎ መግባት ነዉ።
ጫማ አድርጎ ወደ ቤተክርስቲያን መግባት ክልክል ነዉ።
የሐዋ.7፥33
ኢያ.5፥15
ፍት.ነገ.12
"ወደዚህ አትቅረብ አንተ የቆምኽባት ስፍራ የተቀደሰች መሬት ናትና ጫማኽን ከእግርኽ አዉጣ"(ዘፀ.3፥5)።
"አሁን ስሜ ለዘላለም በዚያ ይኖር ዘንድ ይክነን ቤት መርጫለኹ ቀድሻለሁም ዐይኖቼና ልቤም ዘወትር በዚያ ይኾናሉ" ፪ኛ.ዜና 7፥16።
"ቤተ መቅደስኽ ቅዱስ ነዉ፤በጽድቅም ድንቅ ነዉ" መዝ.64፥5
"በቅድስት ከተማ ስም የተጠራችሁ ስሙም የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር በሚባል በእስራኤል አምላክ የምትደገፉ የያዕቆብ ቤት ሆይ ይኽነን ስሙ"(ኢሳ.48፥2)
"እድፈት ወይንም የፊት መጨማደድ ወይም እንዲኽ ያለ ነገር ሳይኾንባት ቅድስትና ያለ ነዉር ትኾን ዘንድ ክብርት የኾነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ" (ኤፌ.5፥27)
"እኛም በቅዱሱ ተራራ ከርሱ ጋር ሳለን ይኽነን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን"(፪ኛ ጴጥ.1፥18)

አሳብን በመንፈሳዊ ነገር ወስኖ ወደ ዉጪ ወደ ዓለማዊ ነገር እንዲይሔድ መግታትና መቆጣጠር ያስፈልጋል።
ከካህን ቀርቦ መስቀል መሳለምና በረከትም መቀበል ያሻል።
በቤተ ክስስቲያኑ ዉስጥ ተስለዉ የሚገኙትን የሥላሴን፤የመድኀኒታችንን የኢየሱስ የክርስቶስን፤የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን፤የመላእክትን፤የነቢያትን፤የሐዋርያትን፤የጻድቃንን፤የሰማዕታትን፤የደጋጎች የቅዱሳን አበዉን ሥዕሎች እጅ መንሳትና የአክብሮት የስግደት መስገድ ይገባል።
በቤተ ክርስቲያን ዉስጥ መሳቅ ስለዓለማዊ ሥራ መሳቅ ስለዓለማዊ ሥራ መነጋገር ክልክል ነዉ።ከገቡ በኋላ በዝምታ፣በጸጥታ፣በፍርሃት፣የእግዚአብሔርን ምሕረት በጥብዓተ ልብ መፈለግ አለ።ምክንያቱም ቤተ ክርስቲያን የመዘምራንን ማሕሌት፣የቅዱሳን መላእክትን ምስጋና፣የነቢያትን ትንቢያትን፣የሐዋርያትን ስብከት መስሚያና የልዑል እግዚአብሔርን ነገር መማሪያ ቦታ ስለሆነች ነዉ።ከዚህ ሌላ የሥጋ ወደሙ ምስጢር የሚፈጸምባት ናት።
ዘሌ.26፥2
ዮሐ.አፈ ወርቅ.19፥32 "እስመ ቤተ ክርስቲያን በአምሳለ ሰማይ ወመሐይምናን ይኩኑ ወሰቲታ አምሳለ መላእክት ወያፅምዑ በትዕግሥት ወበአርምሞ ወይትመሐለሉ በልቦሙ ዘእንበለ ዕረፍት" ዮሐ.አፈ.አንቀጽ48። "ኢይትናገር አሐዱ ለግሙራ በዉስተ ቤተክርስቲያን እስመ ቤተ እግዚአብሔር ቤተ ጸሎት ወአኮ ቤተ ነገር ወዘተናገረ በዉስቴታ ይጻዕ ወኢይቅረብ በይእቲ ዕለት (ቀኖና አቡሊዲስ ከንቀጽ 7) ወሶበ ትቀዉም ቅድመ ንጉሥ ምድራዊ ዘኢትደፍር ከመ.ትስሐቅ ወኢምንተኒ ትስሕቅኑ ሶበ ትቀዉም ቅድመ ንጉሠ ነገሥት ሰማያዊ" ዮሐ.አፈወርቅ.አንቀጽ 6።
"እመኬ ዓለማዊ ሶበ ይስሕቅ በዉስተ ቅዳሴ ያዉጽእዎ አፍአ ወኢይመጥዉዎ እምሥጢር ቅዱስ" ቀኖና ባስልዮስ አንቀጽ 79

አጭርና ያደፈ ልብስ ለብሶ ወደ ቤተክስስቲያን መሔድ ክልክል ነዉ።ረዘም ያለና ንጹሕ ልብስ ለብሶ መሔድ ያስፈልጋል ዘፀ.19፥10-11

በተለይ ሴትች ራሳቸዉን ተከናንበዉ እንዲጸልዩ ታዝዘዋል።"ኢይባዕ ብእሲ ኀበ ቤተ ክርስቲያን ወኢይጸሊ ዉስቴታ ዘእንበለ ይኩን ልብሱ ድርማንቀ በከመ ይቤ ጳዉሎስ ሐዋርያ ለብሔረ ቆሮንጦስ ቀዳማዊ ለእመ ኮነ ዘይጺሊ አልባሲሁ ሐፂረ ወይትከሠት እምኔሁ ጊዜ ስግዴቱ ይእቲ መፅዓሉ ዘቀበጽነ በእንቲአሁ ወይከዉን ጌጋየ ለዘነጸረ ለዘተነጸረ እስመ ለዘነጸረ ይመጽእ ዐቱ ስሐ ወበእንተዝ ይወርድ ላእሌሁ ከመ ወረደ ላዕለ ወልያ ኖኅ ሶበ ስሐቀ ዲበ አቡሁ በከመ ይቤ መጽሐፈ ኦሪት ወዘነጸረ እስመ ኮነ ምክንያተ ለአብጽሖ ጌጋዩ ለዘነጽቱ አበሳሁ " ዮሐንስ አፈወርቅ አንቀጽ 4፥49-72
ዘፍ.9፥21-27
፩ኛ.ቆሮ.11፥5-14
ወደ ቤተ ክርስቲያን ባዶ እጅ መሔድ አይገባም መባዕ፣ምጽዋት ይዞ መሔድ/ዘፀ.34፥20።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
ይቆየን።
3 views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ