Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-01 09:21:22
2 views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-01 09:21:22 እንኩዋን ለታላቁ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ የሰማዕትነት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ዐቢይ ወክቡር: ጊዮርጊስ: ሰርዌ አዕላፍ: ወመክብበ ሰማዕታት

=>መጽሐፈ ገድሉ እንደሚለው የሰማዕታት አለቃቸው: አንድም ሞገሳቸው ታላቅና ክቡር ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ7 ዓመታት ስቃይ በሁዋላ በዚህ ቀን ተሰይፏል:: ይሕስ ጥንተ ነገሩ እንደምን ነው ቢሉ:-

+ቅዱሱ የተወለደው ከአባቱ ዘረንቶስ (አንስጣስዮስ) እና ከእናቱ ቴዎብስታ የድሮው ፋርስ ግዛት ፍልስጥኤም (ልዳ) ውስጥ ነው:: የተባረኩ ወላጆቹ ክርስትናን ጠንቅቀው አስተምረውት አባቱ ይሞታል::

+ቅዱስ ጊዮርጊስ 20 ዓመት ሲሞላው የአባቱን ስልጣን እጅ ለማድረግ ሲሔድ የቢሩት (የአሁኗ ቤይሩት-ሊባኖስ) ሰዎች ዘንዶ (ደራጎን) ሲያመልኩ አገኛቸው:: እርሱ ግን የከተማውን ሕዝብ አስተምሮ: አሳምኖ: ደራጎኑንም በፈጣሪው ኃይል ገድሎ መንገዱን ቀጥሏል::

+ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ዱድያኖስና 70 ነገሥታት ዘንድ ሲደርስ ክርስቶስ ተክዶ ለጣዖት ይሠገድ ነበር:: በዚያች ሰዓት ድንግል እመቤታችን ወደ ሰማዕቱ መጥታ መከራውንና ክብሩን ነገረችው:: እርሱም በክርስቶስ ስም መሞት ምርጫው ነበርና ከእመቤታችን ተባርኮ ወደ ምስክርነት አደባባይ (ዐውደ ስምዕ) ደረሰ::

+ከዚያም ለተከታታይ 7 ዓመታት ብዙ ጸዋትወ መከራዎችን ተቀበለ:: 3 ጊዜ ሙቶ ተነሳ:: ከሰው ልጅ የተፈጥሮ ትዕግስት በላይ የሆነ ስቃይን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በመቀበሉ የሰማዕታት አለቃቸው: ፀሐይና የንጋት ኮከብ በሚል ይጠራል::
"ተውላጠ ጻማሁ ወሕማሙ:
ዘተለዐለ ሞገሰ ስሙ" እንዲል መጽሐፍ::

=>ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዘመናት በብዙ ስቃያት ሲያስጨንቁት ኖረው በጽናቱ አሸነፋቸው:: 70 ነገሥታትን ከነ ሠራዊታቸው ከማሳፈሩ ባሻገርም በርካታ (በመቶ ሺ የሚቆጠሩ) አሕዛብን ማርኮ ለሰማዕትነት አበቃ::

+በዚህ የተበሳጨ ዱድያኖስም ኮከበ ፋርስ ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲቆራርጡት አዘዘ:: ወታደሮቹም ቅዱሱን ቆራርጠው: በብረት ምጣድ ላይ ጠበሱት:: ያለ ርሕራሔም አካሉን አሳረሩት:: ቀጥለውም ፈጭተው አመድ አደረጉት::

+በአካባቢው ወደ ነበረው ትልቅ ተራራ ጫፍ (ደብረ ይድራስ) ወጥተውም በነፋስ በተኑት::
"ሐረድዎ ወገመድዎ: ወዘረዉ ሥጋሁ ከመ ዓመድ" እንዲል:: (ምቅናይ)
+እነርሱ ይህንን ፈጽመው ዘወር ሲሉ ግን የቅዱሱ ዓጽም ባረፈባቸው ዛፎች: ቅጠሎችና ድንጋዮች ሁሉ "ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት" የሚል ጽሑፍ ተገኘ::

+ወዲያው ግን ኃያል ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከተበተነበት ተነስቶ ወታደሮችን አገኛቸውና "በክርስቶስ እመኑ" ብሎ: አስደንቆ ወደ ሕይወት መራቸው:: 70ው ነገሥታት ግን አፈሩ::
+ከ7 ዓመታት መከራ በሁዋላም በዚሕች ቀን ከብዙ ተዓምራት ጋር ተሰይፎ ደም: ውሃና ወተት ከአንገቱ ፈሷል:: 7 አክሊላትም ወርደውለታል::

=>በ390ዎቹ አካባቢ (ሰማዕት ከሆነ ከጥቂት ዓመታት በሁዋላ) በዚያው በሃገሩ ደብር አንጸው: አጽሙን አፍልሠው ቀድሰዋታል::
+ቅዱሱ ሰማዕት ከሰማዕትነቱ በፊትም ሆነ በሁዋላ ተአምረኛ ነው:: በዘመኑ የክርስቲያኖችን ደም ሲያፈሱ ከነበሩ አራዊት (ነገሥታት) መካከል አንዱ የሆነው ዲዮቅልጢያኖስ ርጉም የ47 ሚሊየን ክርስቲያኖችን ደም አፍስሶ ነበርና ፈጣሪ ደመ ሰማዕታትን የሚበቀልበት ጊዜ ደረሰ::

+በ305 ዓ/ም አካባቢ አረመኔው ንጉሥ ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተአምረኛነት ሰምቶ እንዲያፈርሱት ሠራዊት ላከ:: የሠራዊቱ አለቃም ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ገብቶ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስዕል ላይ ተሳለቀ::

+ከፊቱ የነበረውን ቀንዲል በሰይፍ እመታለሁ ሲል ግን ቀንዲሉ ተገልብጦ መሐል አናቱን መታው:: እንደ እብድ ሆኖ ሞተ:: ሠራዊቱም ሰምቶ ወደ ንጉሡ ሸሸ:: ይሕን ሰምቶ የተበሳጨው ዲዮቅልጢያኖስ ግን ራሱ ሊያፈርሰው ሔደ:: ከቤተ ክርስቲያኑ በር ላይ ሲደርስ ሚካኤልና ገብርኤል ዐይኑን አጠፉት::

+እገባለሁ ሲል ቅዱስ ጊዮርጊስ ከላይ መረዋውን (ደወሉን) ለቀቀበት:: ራሱን ቢመታው ደነዘዘ:: የብዙ ቅዱሳንን ደም የጠጣው ርጉሙ ንጉሥም አብዶ ለ7 ዓመታት ፍርፋሪ ሲለምን ኑሮሰ ይጣን ከገደል ጫፍ ወርውሮ ገድሎታል::

=>አምላካችን እግዚአብሔር ከኃያሉ ሰማዕት ጽናትና ትእግስት: ከበረከቱም ይክፈለን::

=>ሚያዝያ 23 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት
2.ቅዱስ ሮቆ ጻድቅ (በስሙ ለተማጸነ ከወባ በሽታ እንዲጠብቀው ጌታ ቃል ኪዳን ገብቶለታል)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት
2.ቅዱስ ሰሎሞን ንጉሠ እስራኤል
3.አባ ጢሞቴዎስ ገዳማዊ
4.አባ ሳሙኤል
5.አባ ስምዖን
6.አባ ገብርኤል

=>+"+ የሚበልጠውን ትንሳኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ:: ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ:: በድንጋይ ተወግረው ሞቱ:: ተፈተኑ: በመጋዝ ተሰነጠቁ: በሰይፍ ተገድለው ሞቱ:: ሁሉን እያጡ: መከራን እየተቀበሉ: እየተጨነቁ: የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ:: ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ: በዋሻና በምድር ጉድጉዋድ ተቅበዘበዙ:: +"+ (ዕብ. 11:35-38)

✞✞✞ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ✞✞✞
     ✞✞✞ወወላዲቱ ድንግል ✞✞✞
     ✞✞✞ ወለመስቀሉ ክቡር ✞✞✞
2 views06:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 14:23:31 #ማን ፈጠረን ሥላሴ
#ሥላሴ ስንት ናቸው ??
አንድም ሶስትም ናቸው
ሶስትነታቸው በምን በምን ነው ???
በስም
በአካል
በግብር
#አንድነታቸውስ በምን ነው ??
#በባህሪ በህልውና በመለኮት በፍቃድ በስም በአካል #በግብር ይህችን አለም በመፍጠርና በማሳለፍ
የስም ሶስትነታቸው እንዴት ነው ??
አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
የአካል ሶስትነታቸውስ እንዴት ነው ???
አብ ፍፁም አካል ፍፁም መልክ
ፍፁም ገፅ አለው ።
#ወልድ ፍፁም አካል ፍፁም መልክ
ፍፁም ገፅ አለው ።
#መንፈስቅዱስ ፍፁም አካል ፍፁም መልክ
ፍፁም ገፅ አለው ።
#የግብር ሶስትነታቸው እንዴት ነው ?
አብ ወላዲ ፤ ወልድ ፤ተወላዲ
#መንፈስ ቅዱስ ፤ ሰራፂ
#አብ ምን ማለት ነው አባት
ወልድ ምን ማለት ነው ልጂ
#መንፈስ ቅዱስ ምን ማለት ነው ሰራፂ
ከማን ሰረፀ ??
አብ አክሎ ወልድን መስሎ ከአብ የተገኘ
ወይም የሰረፀ
#ሚስጥረ ሥላሴ ከረጂሙ ባጭሩ ከብዙ በጥቂቱ የገለፀልን የአባቶቻችን አምላክ ልኡል እግዚአብሔር
#ከምድር _ አርእያም ስሙ የተመሰገነ ይሁን
3 views11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 14:13:37 መልስ 14ቱ ቅዳሴወች እነዚ ናቸሁ ከላይ እንደጠቀስኩላችሁ ፦

1, ቅዳሴ ሐዋርያት
2, ቅዳሴ እግዚእነ
3, ቅዳሴ እግዝእትነ
4, ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
5, ቅዳሴ ሠለስተ ምዕት
6, ቅዳሴ አትናቴዎስ
7, ቅዳሴ ባስልዮስ
8, ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
9, ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ
10, ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ
11, ቅዳሴ ቄርሎስ
12, ቅዳሴ ያዕቆብ
13, ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ
14, ቅዳሴ ሁለተኛዉ ጎርጎርዮስ

መልካም ንባብ ይሁንላችሁ ።
3 viewsedited  11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 14:13:37 #ኦርቶዶክስተዋህዶለዘለአለም_ትኑር አሜን፫
2 views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-30 14:13:37 #በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን

#ጥያቄና_መልስ

ኦርቶዶክስ ማለት ምን ማለት ነው

#መልስ ኦርቶ ዶክስ 2 ሁለት ቃል ጥምርት ሲሆን ኦርቶ ማለት ቀጥተኛ ትክክለኛ ማለት ነው። ዶክስ ማለት ደግሞ አመለካከት እምነት ነው ስለዚህ ኦርቶዶክስ ማለት ቀጥተኛ እና ትክክለኛ ማለት ነው።

ለእግዚአብሔር ስትታወቁ እንደገና ደካማ ወደ መናቅም ወደ መጀመሪያ ወደ ክህደት ትምርት ለምን ትሄዳላችሁ ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ሀይለ ቃል የት ይገኛል ም&ቁ ጥቀስ?

መልስ ገላ 4፥9 ላይ ይገኛል።

ኢየሱስ የሚለው ቃል የምን ቃል ነው ትርጉሙስ ምንድነው?

መልስ ከእብራይስጥ የተወረሰ የግሪክ ቃል ነው። ትርጓሜውም #አዳኝ ማለት ነው።

ማቴ 1፥21 ይገኛል።

እስከመጨረሻ የፅና ግን እርሱ ይድናል የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ሀይለ ቃል የትላይ ይገኛል?

መልስ ማር 10፥22 ይገኛል።

በሀገራችን ኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሊቀ,ጳጳስ ማን ይባላል?

መልስ ፋሪ ምናጦስ ወይም አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሀን ይባላል።

ቅዳሴ ማርያምን የፃፈ አባት ማነው?

መልስ አባ ሕርያቆስ ነው።

የትንሳኤ መጀመሪያ ማነው?

መልስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

የመጀመሪያ የብሉይ ኪዳን ሰአሊው ማነው?

መልስ #እግዚአብሔር ሙሴን በታቦተ ህጉ ፅላትን ኪዳኑ ላይ ስዕለ ክሩቤልን እንዲስል አዞት ነበር ስለዚህ ሙሴ ነው የሳለው ኦሪ ዘጽ 25፥19
ኦሪተ ዘጽ 37፥6 ላይ ይገኛል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ጌታችን የሳለው ማነው?

መልስ ወንጌላዊው ዮሐንስ ነው።

የእመቤታችንን ስዕል ለመጀመሪያ ጊዜ የሳለው ማነው ?

መልስ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ነው።

ቅዱሳን መላእክት አንድ ጊዜ የተፈጠሩና የማይባዙ በእለተ---------------የተፈጠሩ ናቸው? ተፈጥሮ አቸውም ከ---------እና በ----------የተፈጠሩ ናቸው??

መልስ በእለተ እሁድ የተፈጠሩ ናቸው .ከሳትና .ከንፋስ. የተፈጠሩ ናቸው መጽሐፈ ኩፋሌ 2፥6፥8 ላይ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስተያን የነገር ማርያም አስተምሮ መሰረት እመቤታችንን ድንግል ማርያም የምትጠራባቸው 3/ ሦስቱ ዋና ዋና ስያሜዎች አሏት እነሱም ምን ምን ናቸው ዘርዝሩ???

መልስ 1ኛ በአማን ንፅህት 2 ኛ ወቅድስት 3ኛ .በኩሉ ናቸው።

እነሆ እኔ ከአንተ ጋር ነኝ በምሄድበትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሀለሁ ወደዚችም ምድር እመልስሀለሁ የነገርኩህ ሁሉ እስክገለፅልህ አልተውህም ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ሀይለ ቃል የት ይገኛል የፃፈለት ማነው የተፃፈለትስ ለማን ነው?

መልስ የፃፈው እግዚአብሔር ነው።የተፃፍለት ለያእቆብ ነው ኦሪት 28፥15። ላይ ይገኛል።

እራቁቴን ከእናቴ ማህፅን ወጥቻለሁ እራቁቴን ወደዛ እመለሳለሁ እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን ያለው ማነው??

መልስ ፃድቁ እዮብ ነው። መጽሐፈ እዮብ 1፥21 ላይ ይገኛል።

ሁሉ ተፈቅዶልኛል ግን ሁሉ አይጠቅመኝም የሚያነፃኝ አይደለም። ይህ ሀይለ ቃል የት ይገኛል??

መልስ 1ኛ ቆሮ 10፥፦፦

ሰው ዝም ብሎ የእግዚአብሔርን ማዳን ቢጠባበቅ ምን አለ ያለው አባት ማነው??

መልስ ነብዩ ኤርሚያስ ነው።

መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ ብሎ በራእይ የተነገረው አባት ማነው???

መልስ አፄ ዘርያእቆብ ነው።

ለመጀመሪያ ጊዜ እግዚአብሔር ይፍታ ያለው አባት ማነው።

መልስ አባ ጴጥሮስ ነው።

በእለተ ረቡዕ የተፈጠሩ ፍጥረታት እነማናቸው ??

መልስ ፅሀይ እና ጨረቃ ከዋከብት ናቸው።

የጦቢትን ዓይን ያበራው ማነው???

መልስ ቅዱስ ኡራኤል ነው።

7 ሰባቱ ሚስጢራተ ቤተክርስቲያን የሚባሉትን ዘርዝሩ ???

1 ሚስጢረ- ጥምቀት
2 ሚስጢረ- ሜሮን
3 ሚስጢረ- ቁርባን
4 ሚስጢረ- ክህነት
5 ሚስጢረ- ተክሊል
6 ሚስጢረ- ንስኃ
7 ሚስጢረ- ቀንዲል

በቅዳሴ ጊዜ 5 አምስት ምስዋቶች አሉ። እነሱን ዘርዝር???

መልስ 1 የቁርባን ምስዋት
2 የከንፈር ምስዋት
3 የመብራት ምስዋት
4 የእጣን መስዋት
5 የሰውነት ምስዋት ናቸው

ቤዛ ማለት ምን ማለት ነው??

መልስ ዋጋ ማለት ነው። ወይም ስለ አንድ ነገር አልፎ የተሰጠ መከታ ማለት ነው።

ቤተ ክርስቴያን 3/ሦስት መቅደሶች አሏት እነሱም ምን ምን ናቸው ዘርዝሩ???

መልስ 1 ቤተ መቅደስ
2 ቤተ ልሄም
3 ቤተ ቅድስት ናቸው።

ጌታችን መድኃኒታችን በመስቀል ላይ በዋለ ጊዜ የተፈጠሩ ታምራቶችን ዘርዝሩ ???

መልስ ፅሀይ ጨልማለች ከዋከብቶች እረግፈዋል መቃብራት ተከፍተዋል የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለ2 ሁለት ተከፍለዋል ጨርቃ ደም መስላለች አለቶች ተሰነጣጥቀዋል ሙታን ተነስተዋል ።

ለመጀመሪያ ካህን ሁኖ የተመረጠው እና ላገልግሎት የተጠራው አባት ማነው??

መልስ መልከ ፃዴቅ ነው
ኦሪት 14፥18

ቤተክርስቲያን ውስጥ በዓመት ስንት አይነት ቅዳሴዎች አሉ???

መልስ 14 ቅዳሴ አሉ።

ፀጋ ሲሰጥህ በተሰጠህ ፀጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ ያለው ቅዱስ አባት ማነው???

መልስ ማር ይሳሀቅ ነው።

እራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪ ጥበብ ይለየዋል ያለው አባት ማነው??

መልስ አባታችን አርጋዊ መንፈሳዊ ።

ፍጡራንን መርምሮን ማውቅ ካልቻልን ሁሉን የፈጠር እርሱን መርምሮ ማውቅ እንደት ይቻላል ያለው አባት ማነው???

መልስ አባ አትናቴወስ ነው።

በማንም ላይ ክፋትን አትስሩ አትፍረዱ ይህን ከጠበቃችሁ እርስቲቱን ትወርሳላችሁ ያለው አባት ማነው??,

መልስ ታላቁ አባ መቃርስ ነው።

ስጋዊ ፍለጓቶችን ማሸነፍ ለአክሊል ህይወት የሚያበቃ #ሰማእትነት ነው ብሎ የተናገርው አባት ማነው??

መልስ ብፁ አቡነ ጓርጓርዮስ ካአል ነው።

የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ #የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ ብሎ የተናገርው አባት ማን ይባላል??

መልስ ብፁ አቡነ ጓርጓርዮስ ነው።

5 አምስቱ ፍኖተ ፃድቅ የተባሉትን እነማናቸው ዘርዝሩ???

መልስ 1ፍቅር
2 ትህትና
3 ጾም
4 ፆሎት
5 ምፅዋት ነቸው።

5 አምስቱ እቀባተ መስቀል የተባሉት እነማናቸው ዘርዝሩ ???

መልስ 1 ጣወትን ማምለክ
2 አፍቅሮ ነዋይ
3 ተጣልቶ አለመታረቅ
4 ሰው መግደል
5 እናት አባትን አለማክበር ናቸው።

5 አምስቱ ፍኖተ ኃጢአት የተባሉት እነማናቸው ዘርዝሩ ????

መልስ 1 ትንቢት
2 ስስት
3 ምቀኝነት
4 ስርቆት
5 ዝሙት ናቸው

7ሰባቱ ሊቃነ መላእክት ይሚባሉትን ዘርዝሩ???

መልስ 1ቅዱስ ሚካኤል
2 ቅዱስ ገብረኤል
3 ቅዱስ ፋኑኤል
4 ቅዱስ ራጉኤል
5 ቅዱስ ኡራኤል
6 ቅዱስ ሳቁኤል
7 ቅዱስ አፍኒን

7 ሰባቱን አፅዋማት ዘርዝሩ???

መልስ 1 ዐብይ ፆም
2 የሐዋርያት ፆም
3 የፍልሰታ ፆም
4 የነብያት ፆም
5 የነነዌ ፆም
6 ፆመ ገሀድ
7 ፆመ ድህነት

#ወስብሀት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
#ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን አሜን

#የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት
የቅዱሳን መላእክት ልመናቸው ፀሎታቸው
ፃድቃን ሰማእታት ረደኤት በርከታቸው ከሁላችንም ጋር ይኑር አሜን፫
3 views11:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 22:01:07 2.ጉባኤ ቁስጥንጥንያ

ጉባኤው የተካሄደው በ381 ዓ.ም በቁስጥንጥንያ ነው፡፡ ምክንያት የሆነ መቅዶኒዮስ መንፈስ ቅዱስ ሕጹጽ ነው በማለት ባስተማረው ትምህርት ነው፡፡ ይህ ክህደት ሲነሳ የቁስጥንጥንያ ንጉስ የነበረው ቴዎዶስዮስ ቀዳማዊ ይህ የቤተክርስቲያን ችግር በጉባኤ እንዲፈታ ባስተላለፈው መልእክት መሠረት 150 ሊቃውንት ተሰብስበዋል፡፡

በዚህ ጉባኤ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን የተወያዩባቸው መሠረታዊ ጉዳዮችም የሚከተሉት ናቸው::

1. መቅዶንዮስና ትምህርቱን ለማውገዝ

2.አቡሊናርዮስንና ትምህርቱን (በምሥጢረ ሥጋዌ ቃል እግዚአብሔር ሰው በሆነ ጊዜ ሥጋን እንጂ ነፍስን አልተዋሃደም የሚለውን ክህደት) ለማውገዝ

3.ወልድ የተዋሃደው የአዳምን ሥጋ አይደለም ሌላ በቅድምና የነበረ ሥጋ ነው እንጂ የሚሉ መናፍቃንን ለማውገዝ፡፡

4.በኒቅያ ጉባኤ ላይ በተረቀቀው ጸሎተ ሃይማኖት ላይ የተጨመሩ

5ቱን የሃይማኖት ቀኖናዎችን ማርቀቅ

በዚህ ጉባኤ ላይ መቅዶንዮስ መንፈስ ቅዱስ ሕፁጽ፣ ፍጡር ነው ያለበትን ምክንያት ሲጠየቅ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ አላቀረበም፡፡ ከዚህም በኋላ ጉባኤው በኢሳይያስ 6-3፣ በማቴዎስ 28-19 በሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አንድነትንና ሦስትነን በማስረዳት ቢነገረው ከኑፋቄው አልመለስም በማለቱ 150ው ሊቃውንት የክህደት ትምህርቱንና እርሱን አውግዘው ለይተውታል፡፡

ሌላው ጉባኤው የአቡሊናርዮስን በምሥጢረ ሥጋዌ ቃል እግዚአብሔር ሰው በሆነ ጊዜ ሥጋን እንጂ ነፍስን አልተዋሃደም የሚለውን የክህደት ትምህርት አውግዘዋል፡፡ ለዚህም በዮሐንስ 1-14 ላይ "ቃል ሥጋ ሆነ" የሚለውን በመጥቀስ በትክክል የቃልና የሥጋን ውህደትና መጽሐፍ ቅዱሳዊነት ሊቃውንት አስረድተዋል፡፡

ቅዱስ ጎርጎሪየስ ዘኢንዝናዙም ሰው ማለት ነፍስና ሥጋ ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋን እንጂ ነፍስ አልነሳም ከተባለ ያዳነው ሥጋን እንጂ ነፋስን አይደለም ብሎ በመመለስ የአቡሊናርዮስን ክህደት ተናግሯል፡፡ ከዚህም በማያያዝ ጉባኤው በኒቅያ ጉባኤ አንቀጸ ሃይማኖት ከተጠቀሱት ተጨማሪ 5 አንቀጾችን አስቀምጧል፡፡ እነርሱም
1. በጌታ በአዳኝ ከአብ በሠረፀ ከአብና ከወልድ ጋር በነቢያት በተናገረ በመንፈስ ቅዱስ እናምናለን፣ እንስገድለት እናመስግነው

2. በሁሉ ባለች በሐዋርያት ጉባኤ በአንዲት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፡፡

3. ለኃጥያት ማስተሰርያ በምትሆን በአንዲት ጥምቀት እናምናለን

4. የሙታንን ትንሳኤ ተስፋ እናደርጋለን

5. የሚመጣውንም ሕይወት እንጠባበቃን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡

ይንን ከዚህ በላይ ያየነው በጉባኤ ቁስጥንጥንያ የረቀቀው አንቀጸ ሃይማኖት በኒቅያ ጉባኤ ከተወሰነው ጋር አንድ ሆኖ ዛሬም እኛ በሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያናችን  ሥር የምንኖር የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች የምናምነው የምንቀበለው አንቀጸ ሃይማኖት ነው።
18 views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 22:01:07
የዕለቱ መወያያ ርዕስ

1.ጉባኤ ቁስጥንጥንያ በስንት ዓ.ም ተካሄደ?
2.የጉባኤው መከናወን ዋናው ምክንያት ምንድነው?ከሀዲውስ ማን ይባላል?
3.ያወገዙት ሊቃውንት ብዛት ስንት ነው?ዋናው አውጋዥስ ማነው?
4.ጉባኤውን የጠራው ንጉስ ማን ይባላል
2 views19:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 21:58:54 ሳልሳዊ ቴዎድሮስ

ከአባ አመሃ እየሱስ መልእክት የተወሰደ

በተረፈ ስለ ንጉሡ ማንነት አሁን የምነግራችሁ በጣም ባጭሩ ነው። ዝርዝር ሁኔታ አልገባም።
ለወደፊቱ በድምፅ ሰፊ የሆነ ምስጢራዊ የትርጉም ትምህርት ስለ ንጉሡና ስለ ጳጳሱ ማንነት
ስለምለቅላችሁ በተስፋ ጠብቁኝ አትቸኩሉ። ሳለቅላችሁ ቀድመው ከመጡ ግን መጡ ነው።
የማቀርብላችሁ ራሴ በጥያቄና በመልስ ባዘጋጀሁት መሠረት ነው። ይኸውም በደንብ
እንዲገባችሁ ብየ በማሰብና በማመን ነው። በሉ ተቀበሉኝ፦
ጥያቄ፦ ንጉሥ ቴዎድሮስ የሚባል አለ የለም?
መልስ፦ በደንብ አለ እንጅ።
ጥያቄ፦ የት ነው የሚኖረው?
መልስ፦ ከጥንት ጀምሮ እንደነ ሄኖክ፣ኤልያስ፣ዕዝራ፣አቡነ አረጋዊ፣ቅዱስ
ያሬድ...........በክብር ተሰውሮ የሚኖር ነው እንጅ ጊዜው ደርሶ እስኪገለጥና
እስኪመጣ ድረስ ከአሁን በፊት ለማንም ለማን አልታየም አይታይም።
ጥያቄ፦ መቼ ነው የሚመጣ? መልስ፦ አይነገርም። ግን ግን በጣም በጣም ቅርብ ጊዜ ነው።
ከበራፋችሁ ደርሶ ሊገባ ቆሟልና ደስ ይበላችሁ። ጥያቄ፦ በየት ነው የሚመጣ?
መልስ፦ በምሥራቅ።
ጥያቄ ፦ በየትኛው የኢትዮጵያ ምሥራቃዊ ክፍል ነው? በበጌምድር ጎንደር ምሥራቅ? በሸዋ
ምሥራቅ? በጎጃም ምሥራቅ? በቤተ አምሐራ ( ወሎ) ምሥራቅ?
መልስ፦ አሁን አይነገርም፣ ሲመጣ ማየትና መቀበል ብቻ ነው።
ጥያቄ፦ ነገዱ ምንድን ነው?
መልስ፦ ቤተ አይሁድ እስራኤላዊ እና ኢትዮጵያዊ አማራ ነው።
ጥያቄ፦ ትውልድ ሀገሩ የት ነው?
መልስ፦ አሁን አይነገርም። የት እንደሆነ ያኔ ሲመጣ ታውቁታላችሁ።
ጥያቄ፦ ቴዎድሮስ ማለት ትርጉሙ ምን ማለት ነው?
መልስ፦ ቴዎድሮስ ቃሉ የግሪክ ነው እንጅ አማርኛም ግእዝም አይደለም። ትርጉሙም ስጦታ፣
የፈጣሪ ስጦታ ማለት ነው።
ጥያቄ፦ ግዛቱ እስከምን ነው?
መልስ፦ መላ ኢትዮጵያን፣ መላ አፍሪካን፣በፈጣሪ ፈቃድና ትእዛዝ እንደዛሬዋ አሜሪካ መላ
ዓለምን በኃያልነት ይገዛል ይመራል። እንደ ንጉሥ ሰሎሞን ዘመን መላው ዓለም ሁሉ ወዶና
ፈቅዶ ይገብርለታል፣ ይሰግድለታል..........ያኔ ግብጽና ሱዳን እንደዛሬው ኢትዮጵያን
መረበሽ ይቅርና መተንፈስም አይችሉም።
ጥያቄ፦ በሌላ መልኩ ደግሞ የሚመጣው ንጉሥ ንጉሥ ሕዝቅያስ ነው የሚሉ ስላሉ ይህስ
እንዴት ነው? ለምትሉኝ፦
መልስ፦ ሌላ ሁለተኛ ሆነ ሦስተኛ ንጉሥ ሕዝቅያስ የሚባል የለም፣ አይመጣምም። ንጉሥ
ሕዝቅያስ የሚባለው ራሱ ንጉሥ ቴዎድሮስ ነው እንጅ ሌላ አይደለም። ሰዎች ትምህርትና
እውቀት ሳይኖራቸው ዝምብለው ንጉሥ ሕዝቅያስ የሚባል ከቴዎድሮስ ቀድሞ ይመጣል፣
አገሩንና ሕዝቡን ያረጋጋል ምናምን ምናምን እያሉ ይቀባጥራሉ። ይህ ካለመማርና ካለማወቅ፣
እንዲሁም የፈጣሪን ምስጢራዊ የፀጋ ስጦታ ያለማግኘት ነው እንጅ የሚያናግራቸው ሕዝቅያስ
የሚባለው ራሱ ቴዎድሮስ ነው። ሕዝቅያስ የተባለበትም ራሱን የቻለ ትምህርታዊ ትርጉምና
ምስጢር ስላለው በድምፅ በምለቅበት ጊዜ ስለምተረጉምላችሁ በትእግስት ጠብቁኝ አትቸኩሉ።
ጥያቄ፦ ስንት ዓመት ይገዛል? መልስ፦ ከቁጥር አራት የጽሑፍ መልእክቴ ከሆነው መጨረሻ
ላይ ብሥራት ከሚለው ላይ አለላችሁ ያንን አንብቡ እላችኋለሁ።
በአንጻሩ ደግሞ የሚመጣው ጳጳስ መደበኛ ስሙ ፀሓይ ነው። ግን ግን በትንቢቱ ላይ ኤርምያስ
የሚባል ጳጳስ ይመጣል፥ አቡነ አረጋዊ የሚባል ስውሩ ጳጳስ ሆኖ ይመጣል እየተባለም ይነገራል።
አዎ ልክ ነው። ግን ግን ኤርምያስ የሚባለውም ሆነ አረጋዊ የሚባለው ራሱ ፀሐይ ነው እንጅ
ሌላ ኤርምያስና ሌላ አረጋዊ አይደሉም። ፀሐይን ኤርምያስና አረጋዊ የሚባልበትም ምክንያት
ራሱን የቻለ ትምህርታዊ ትርጉምና ምስጢር ስላለው ሁሉንም በድምፅ ስለቅ
እተረጉምላችኋለሁና በተስፋና በትእግስት ጠብቁኝ አትቸኩሉ። ከዚህ ውጭ ስውሩ አቡነ
አረጋዊ አሁን ጳጳስ ሆነው የሚገለጡና የሚመጡ ሳይሆን በሐሳዊ ዘመን ስውራን ሁሉ
ተገልጠው ሲያስተምሩና ሲዋጉ እሳቸውም ያኔ ተገልጠው የሚያስተምሩ፣ የሚዋጉና ሰማዕት
የሚሆኑ ናቸው። በጥቅሉ የጳጳሱ ማንነትም ምስጢሩ እንደ ንጉሥ ቴዎድሮስ ነው። ሳልነግራችሁ
የማልተወው ሌላ ተጨማሪ ጉዳይ ግን የሚመጡት ጳጳሳት ሁለት ናቸው። አንደኛው በትንቢት
የታወቀው አቡነ ፀሐይ ሲሆን ይህ ጳጳስ ዓለምን የሚመራ የዓለም ፓትርያርክ ነው። ፀሐይ
የተባለበትም ምስጢርና ትርጉም ስለዚህ ነው ባጭሩ። ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ ነው። ትውልድ ሀገሩ
ግን አሁን አይነገርም። ያኔ ሲመጣ ታውቁታላችሁ። ሁለመናው እንደ ንጉሡ ነው። ነገዱ ግን
በእስራኤል በኩል ነገደ ሌዊ ሲሆን በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ ነገደ አምሓራ (አማራ) ነው።
ሁለተኛው ጳጳስ ደግሞ ትንቢት ያልተነገረለትና ሱባኤ ያልተቆጠረለት ሲሆን ሆኖም ግን ያኔ
የሚሾም ነው። ይኸውም የኢትዮጵያ ፓትርያሪክ የሚሆን ነው። ሥራውም ከዋናው የዓለሙ
ፓትርያሪክ ከፀሐይ በታች ሆኖ ኢትዮጵያን ይመራል። ይህኛውም ጳጳስ ነገዱ ኢትዮጵያዊ
አማራ ሲሆን ነገደ እስራኤል ይኑርበት አይኑርበት አላውቅም፣ አልተገለጠልኝም።
የምነግራችሁ የተማርኩትን፣ የተገለጠልኝንና የማውቀውን ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ መናገር
የወንጌል ደላላዎች ሰይጣናዊ ስብከት ነው። ትውልድ ሀገሩን ግን አሁን አይነገርም። ሁሉንም
ነገር ያኔ ከፈጣሪ መቅሰፍት፣ ከኢትዮጵያ ቅጣት በሥጋ ሕይወት የተረፈ ሁሉ በደስታ ሆኖ ያያል
ያውቃል።
2 views18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 06:36:34

ሚያዝያ 21 | የእመቤታችን ፍቅር የበዛላቸው፥ ከፈላስፋነት እና ከእስላምነት የተመለሱ ሁለት ቅዱሳን የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው።

  ◈ ቅዱስ ብሩታዎስ ሐዋርያ

ይህም ቅዱስ አባት፥ ከመድኃኔዓለም ዕርገት 14 ዓመት ሲሆን በፍልስፍናው ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር ይከራከር ነበር።

በኋላ ግን አመነ እና በቅዱስ ጳውሎስ እጅ ተጠመቀ፤ ቅስናን ተሾመ።

ዘወትርም እመቤታችንን ሄጄ ባየኋት እያለ ይመኝ ነበር። በአንደኛው ቀንም ከአቴና ተነሣ እና ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ። እግዚአብሔርም መንገዱን አቀናለት።

ኢየሩሳሌም የደረሰውም በእመቤታችን የዕረፍት ቀን ጥር 21፥ 49 ዓ.ም ሆነለት። ከማረፏም በፊት አግኝቷት፣ በእጇ ተባረከ።

ከደስታውም ብዛት የመጀመሪያውን ጥዑም ውዳሴ ደረሰላት። ሐዋርያትም በጣዕሙ ተጽናኑ፨

        ◈ አቡነ እጨጌ ዕንባቆም

የመናዊው እጨጌ ዕንባቆም በዐረብ ምድር በየመን የተወለዱ ሲሆን አስቀድመው እስላም ነበሩ።

በኋላ ግን መጻሕፍትን መርምረው ዕውነትን ይፈልጉ ጀመር። ከነጋዴዎችም ጋር በዳህላክ በኩል ወደ ኢትዮጵያ ገቡ።

መርሐ ቤቴ አካባቢም የሃይማኖት ትምህርትን ጀመሩ። ከግእዝ ንባብ የጀመሩ ተአምረ ማርያም ሲደርሱ የእመቤታችን ፍቅር እጅግ ሳባቸው።

በጌታችን በክርስቶስ አምነው ተጠምቀው ከመነኮሱ በኋላ በደብረ ሊባኖስ በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ወንበር ተሾመው እስከማገለግል የደረሱ ታላቅ አባት ናቸው፨
~ ~ ~
የእመቤታችንን ፍቅሯን የቅዱሳኑን በረከት ያድለን።
4 views03:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ