Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-02 20:33:17 የካቲት 23/2015 ዓ.ም
የእግዚአብሔር ወገን የሆናችሁ ኢትዮጵያዉያን!
በእግዚአብሔር እዉነት ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵዊነት እንዲሁም ለሕዝቧ ተጋድሎ ያደረጉ፤ ከዚህ በተጨማሪ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትና ለአማኞቿ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ ታሪክ የሰሩ ሁሉ፤ እንደ ተጋድሏቸዉና መስዋዕትነታቸዉ የእግዚአብሔር ወገን በሆኑት ዘንድ ሁሌም ይታሰባሉ፣ ይከበራሉ፡፡

በተቃራኒ ደግሞ በአገር ዉስጥ ሆነ በዉጭ ዓለም ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዉያንን ለማጥፋት፣ ለመከፋፈል እንዲሁም ተዋህዶ እምነቷንና አማኞቿን ለማጥፋትና ለመከፋፈል የተሰለፉና የሚሰለፉ ሁሉ፤ በምድርም በሰማይም በጥቁር መዝገብ የሚመዘገቡና የማይታሰቡ፣ በኢትዮጵያ ቀን መታሰቢያቸዉ የሚጠፋና ከእግዚአብሔር ቁጣና ጠረጋ የሚተርፉ ካሉም እንደ ጥፋት ሥራቸዉ መጠን ዋጋ የሚከፍሉ ናቸዉ፡፡

የዓመጻና የክፋት ልጆች የእግዚአብሔር ቁጣ ሆነዉ ባለ ጊዜ በሆኑበት ዘመን የጨለማዉ ገዥ አገልጋዮች የነበሩትና የሆኑት፤ በጨለማዉ ገዥ መንፈስ በሚመሩና በቁጥጥሩ ዉስጥ ባሉ ሰዎች ዘንድ ለጊዜዉ ከፍ ከፍ ሊሉና ሊታሰቡ ይችሉ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የማይጸናና የእግዚአብሔር ወገኖች ባለ ጊዜ ሆነዉ በሥጋዊ ሆነ በመንፈሳዊ ወንበር ላይ ለአገልግሎት ሲሰለፉ፤ በፀረ ኢትዮጵያና በፀረ ኢትዮጵያዊነት እንዲሁም በፀረ ተዋሕዶ እምነት ላይ የተሰለፉ የዓመጻና የክፋት ልጆች ሁሉ፤ እንኳን ከፍ ከፍ ሊሉና ሊታሰቡ ቀርቶ መታሰቢያቸዉም የሚጠፋና በዉርደት መዝገብ ዉስጥ የሚጻፉት፡፡

ከእግዚአብሔር ወገን በሆኑ ኢትዮጵያዉያንና እንዲሁም ከእግዚአብሔር እዉነት ጋር አንድነት ባላቸዉ በሌሎች ዘጎችም ጭምር “ታላቅ መሪ” የሚባሉ፤ ከጨለማዉ ገዥ ወገንና አገልጋይ በሆኑት በዓመፃና በክፋት ልጆች ዘንድ እንዲሁም ለ31 ዓመት በዘረኞችና በጎጠኞች የሐሰትና የክፋት ስብከት ሕሊናቸዉ በተበከለና በተመረዙ ጥቂት ትዉልዶች ዘንድ ደግሞ “ወራሪዉና ግፈኛዉ” ተብለዉ ስለተፈረጁት አጼ ምኒልክ እና ስለ ሌሎች እዉነታዎችን፤ “የእግዚአብሔር እዉነት ምን ትላለች?!” የሚለዉን በማስተዋል እስከመጨረሻዉ እንድታነቡት በማክበር አሳስባለዉ

“ ጠያቂዉ አገልጋይ፡ የኢትዮጵያ ታሪክ ዘመን ሦስት ሺህ ነዉ ብለዉ የሚናገሩ አሉ፡፡ አንዳንዶች ደግሞ “ነፍጠኞች ወይንም ዐማሮች ወይንም ክርስቲያኖች፣ የተለያዩ ክልሎችንና ብሔር ብሔረሰቦችን ወረዉ ነዉ ኢትዮጵያ የምትባል አገር የፈጠሩት እንጂ ኢትዮጵያ ታሪኳ ወደ አንድ መቶ ዓመት ገደማ ነዉ” ይላሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ታላቁን መሪ ዳግማዊ አጼ ምኒልክን፤ “ወራሪዉና ግፈኛዉ ምኒልክ የፈጠራትን ኢትዮጵያ፤ እንደ ቀድሞ በክልላትና በብሔር ብሔረሰብ ተከፋፍላ መተዳደር አለባት፤ ብሔር ብሔረሰቦች ፍላጎቱ ካላቸዉ “ኢትዮጵያዊ ነን” ብለዉ በመዋሐድ መኖር ይችላሉ፡፡ ካልፈለጉ ደግሞ ተገንጥለዉ እንደ ቀድሞ ነጻ መንግሥታቸዉ፣ እንደ ኤርትራ መስርተዉ መኖር ይችላሉ፡፡ ለዚህም ዋስትና እንዲሆናቸዉ የብሔር ብሔረሰቦች መብትና ነጻነት እስከ መገንጠል የሚለዉን ዐዋጅ በሕገ መንግሥቱ ተረጋግጦላቸዋል… ወዘተ” የሚሉ አሉ፡፡

አዲሱ ትዉልድ ደግሞ “ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ገና የሃያ ዓመት ታሪክ ነዉ፤ ከዚያ በፊት ነጻነት የሌለበት፣ በዐምሓሮች (በክርስቲያኖች) ግፍና በደል የተፈጸመበት፣ ብሔር ብሔረሰቦች እንደ ዜጋ የማይታዩበት፣ እኩልነት ነጻነት ዲሞክራሲ ያልሰፈነበት ስለነበረ እንደ ኢትዮጵያ አገር መቆጠር የለበትም፤ እኩልነት፣ ነጻነት፣ ዲሞክራሲ የሰፈነባት ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ የተፈጠረችዉ ከግንቦት 20/1983 ዓ.ም ጀምሮ ስለሆነ፤ ታሪኳ ከኢሕአዴግ ዘመን መጀመር አለበት” የሚሉ ዘመናዊ ፓለቲከኞችና ካድሬዎች አሉ፡፡ ለነዚህ ምን ምላሽና አስተያየት አሎት?

መላሹ የእግዚአብሔር አገልጋይና መልእክተኛ፡ ከሁሉ ከሁሉ የሚያሳዝነዉና የሚያስገርመዉ ከማንም በላይ ከምሥራቅ ኢትዮጵያ፣ ከምእራብ ኢትዮጵያ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ዉስጥ ካሉ ሕብረተሰብ በላይ ሊአትዮጵያና ለኢትዮጵያዊነት ጥብቅና ሊቆሙና ታሪኳን፣ ቅርሷን፣ ማንነቷን ለቀጣይ ትዉልድ ማስተላለፍ የሚገባቸዉ ከሰሜን የወጡ፤ “ የእሳት ልጅ አመድ” እንደሚባለዉ የሆኑት ሕወሐት(ወያኔ) እና ሻዕቢያ የተባሉ የዓመፃ ቡድኖች ተነሥተዉ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ቆርጠዉ መነሣታቸዉና የ7504 ዓመት ታሪኳን ደምስሰዉ 125 ዓመት ታሪክ ለመፍጠር መነሣታቸዉ ነዉ፡፡

በዘመነ መሳፍንት በሥልጣን ጥማት የተከፋፈሉ የአካባቢ ነገሥታትን ድል አድርገዉ ኢትዮጵያን እንደ ጥንቱ ወደ አንድነት ለማምጣት የጀመሩትን የአጼ ቴዎድሮስን ተጋድሎ፤ አጼ ዮሐንስ የቀጠሉትን ለእናት አገራቸዉና ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታቸዉ በወራሪዎች የተሰዉትን ፈለግ ተከትለዉ፤ በየጎጡ ራሳቸዉን ለማንገሥና የራሳቸዉን የግል ፍላጎት ብቻ ለማሟላት ይታገሉ የነበሩ የተለያዩ የአካባቢ ነገሥታትን ወደ አንድነት ያመጡትን ታላቅ መሪን ዳግማዊ አጼ ምኒልክን፤ “በወራሪነት፣ በግፈኛነት… ወዘተ” መፈረጅ ምን ያህል ዉስጣቸዉ ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ነዉ የሚያሳየን፡፡ ለዚህ ነዉ በሃያ ዓመት ዉስጥ በክርስቲያኖች (በዐምሓራዎች) ላይ የፈጸሙትና ያስፈጸሙት የበቀልና ግፍ ተግባር አላረካ ብሏቸዉ፤ አሁን ድረስ “ አከርካሪያቸዉ እንዳያንሰራራ መሰበር አለበት፣ ሊደመሰሱ ይገባል ” እያሉ በትዕቢትና እብሪት የሚናገሩትና የሚደነፉት፡፡ ሌላዉ የዉስጣቸዉ ጥላቻና በቀልን የሚመሰክርባቸዉ፤ ለአዲስ አባባ መቆርቆር ምክንያት የሆኑት አጼ ምኒልክና እትጌ ጣይቱ በአዲስ አባባ በ125ኛዉ በዓል መታሰቢያ ሊታሰቡ ሲገባ፤ ቀን ከሌሊት በተለያየ መገናኛ ብዙኃን ስሙ ሲጠራ የምንሰማዉ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሣዉና በቃል ኪዳኑ ላይ ዋና መሪ ሆኖ ዓመጻ፣ ክህደት፣ ርኩሰት የፈጸመዉና ያስፈጸመዉ አቶ መለስ ዜናዉ ነዉ፡፡

እግዚአብሔር፤ ሕወሐት ኢሕአዴግን ባለጊዜ ያደረጋቸዉ የሚፈጽሙት ተግባር ስላለዉ ነዉ እንጂ እንደነሱ የክፋትና የተንኮል እንዲሁም የጥፋትና በቀል ተግባር ቢሆን ኖሮ የአንድ ዓመት እድሜ አይሰጣቸዉም ነበር፡፡ አሁን ግን የተፈቀደላቸዉ የሃያ ዓመት እድሜ ስለተጠናቀቀ፤ የሚቀራቸዉ የዘሩትን የዘረኝነት፣ የጎጠኝነት፣ የክፋት፣ የጥላቻ፣ የበቀል፣ የጥፋት ዘራቸዉን ማጨድና ያፈሩትን ፍሬ እጅግ መራራ ቢሆንም ቋቅ እያላቸዉ የሚጠጡት ይሆናል፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ፍርድ የሚገለጸዉ ከሥጋ ሞት በኋላ ብቻ ሳይሆን በዚህች የዐይን ቅጽበት ምድራዊ ዘመናችን ጭምር ነዉ፡፡

በክርስቲያኑ (በዐምሐራዉ) ላይ በደልና ግፍ ያስፈጸሙት የከፋ ተግባራቸዉ ምን ያህል ዋጋ እንደሚያስከፍላቸዉ እጅግ እጅግ በቅርብ ጊዜ ዉስጥ የእግዚአብሔር ቁጣ ሲነድባቸዉ የምንመለከተዉ ይሆናል፡፡ እኛ እንደወገንነታችን አሁንም የእግዚአብሔር ቁጣ መቶ ሳይጠርጋቸዉ በእዉነተኛ ንስሐ ራሳቸዉን በእግዚአብሔር ፊት አዋርደዉ ስለሰሩትና ስላሰሩት የዓመጻ፣ የክህደት፣ የርኩሰት፣ የግፍና የጭከና ተግባር በግልጽ ይቅርታን መጠየቅና ወንበሩን እግዚአብሔር ለመረጣቸዉ ባለሟሎቹ ካለምንም ቅድመ ሁኔታና ድርድር መልቀቅ ብቻ ነዉ፡፡ “አይሆንም የሚሉና ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ እምነታችን ዉጭ አንወጣም፣ በዚህም የማያምኑትን እንደመስሳቸዋለን” የሚሉ ከሆነ ደግሞ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከወንበራቸዉ ተቆርጠዉ ዓመጻ፣ ክህደት፣ ርኩሰት ካነገሡባት ከባለ ቃልኪዳኗ ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር ቁጣ ይጠረጋሉ፡፡
5 views17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 12:16:33
4 views09:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 12:16:33 ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ የኢትዮጵያ ገበዝ፣ ለጀግኖች አባቶቻችንና እናቶቻችን ያደረገው ተአምር ይህ ነው፤
የሰማዕቱ ረድኤት በረከት አይለየን!!! አሜን!!!

ልመናው ጸሎቱ በረከቱ አማላጅነቱ በዕውነት ለዘለላለሙ ይደረግልንና ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ተአምር ይህ ነው ።
በዚያን ወራት ከጌታችን ከኢየሱስ ልደት አንድ ሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ ዓራት በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ በነገሠ በሃያ ስድስት ዓመት የምኒልክ የጦር አለቃ ገበየሁ ድል ከአደረጋቸው በኋላ እንደገና ምኒልክን ወግተው የኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ሊገዙ የሮም ሰዎች መጡ።
ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አገሬ ኢትዮጵያን እወዳለሁ የሚል ኢትዮጵያዊ ኹሉ ባስቸኳይ ይነሣ መስቀለ ሞቱንም ተሸክሞ ይከተለኝ እግዚአብሔር የወሰነልንን የባሕር ወሰን አልፎ አገር የሚያጠፋ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት መጥቷልና ሲል ዓዋጅ አስነገረ ።
ዳግመኛም በፈረሶቻቸው መጣብር ላይ በጦራቸው አንደበት ላይ በጋሻቸው እምብርት ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ጭፍሮቹን አዘዛቸው መስቀል ጠላትን ድል አድራጊ እንደኾነ አስቀድሞ ያውቅ ነበርና
ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ አገር ዘመተና ከትግራይ አውራጃዎች አንዷ የምትሆን አድዋ ከምትባል አገር ደረሰ ።
የሣህለ ማርያም(ዳግማዊ ምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱ) በንጉሡ ትእዛዝ ታቦተ ጊዮርጊስን አሲዛ ከሊቀ ጳጳሱ ከአባ ማቴዎስ ፤እንዲሁም ከቀሳውስቱና መነኮሳቱን ጭምር ከንጉሡ ጋር ወደ ጦርነት ተጓዘች ።
በዚህም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኮሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሥ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከነአቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎተ ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ ።
ቅዳሜ ማታ ለእሁድ አጥቢያ ይኸውም የካቲት ሃያ ኹለት ቀን ነው ንጉሡ ሣህለ ማርያም የጦር ልብሱን ለብሶ ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄደ ። ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋር ተገናኝቶ ከሌሊቱ በዓሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ ።
የንጉሡ የሣህለ ማርያም ሚስት ወለተ ሚካኤል ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ በሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይለ ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር ።በዕውነትም ለተመለከታት ኹሉ እንደ ኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበር እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይም ነበር ።
የንጉሡም ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና የፍየል መንጋ እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፉት ነበር ።መጽሐፍ ሹመቱን ሽልማቱን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም ብሎ ተናግሯል ።
በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አባ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኮሳት እና ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ጊዮርጊንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምህላ ያደርሱ ነበር ።ንግሥቲቱ ወለተ የሚካኤል በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነሱ አትለይም ነበር
የጽዮን አገልጋዮች በእግዚአብሔር የሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር ።በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት ሃያ ሦስት ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ኾነ በዚህም ጊዜ በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ።ማለት የቀስተ ደመና ምልክት ታየ ከዚያም ደመና ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የመሚስል ጢስ ይወጣ ነበር ።ከዚህም ጢስ ውስጥ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ያለ ድምፅ ተሰማ ።
ከዚህም የነጎድጓድ ድምፅ የተነሣ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ኾነ ለመዋጋትም አልቻሉም። ይልቁንም ኃያሉ ገባሬ ተአምር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረስ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በዓየር ላይ በተገለጸ ጊዜ በግምባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ የኢትዮጵያ ሕዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ እንግዲህ ማን ያድነናል አሉ ፤ ምድር ጠበበቻቸው በዚህም ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው ። የተረፉትንም ማረኳቸው ፈጽመውም እስኪአጠቸፏው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታች ሄደች።
ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳኢነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት ድል አድርጎ የድል አክሊል ተቀዳጀ ።
ስለዚህም በዳዊት የምስጋና ቃል የድል የዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔርን ባለ ዘመኔ ኹሉ አመሰግነዋለሁ ለፈጣሪዬም እዘምራለሁ አለ ሕዝቡም ኹሉ በክብር ከፍ ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና እናመሰግነለዋን የሮማውያንን ኃይል ተቀጥቅጦ አጥፍቷልና ሠረገሎቻቸውንም ሠባብሯልና ፤ ሠራዊቱንም ኹሉ በምድር ላይ በትኗልና እያሉ አመሰገኑ ።በፈጣረው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መካከል የረዳቸውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም በፍጹም ማድነቅ አደነቁት።
የሮማም የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያውያን ፊት ተዋረዱ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም ።በምኒልክ ዘመነ መንግሥት ኢትዮጵያ ከጦርነት ለዓርባ ዓመት ያህል ።
የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ ከዓድዋ ጦርነት ከተመለሰ በኋላ አዲስ አበባ በምትባለው ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተክርስቲያን አሠራ ስሟንም ገነተ የጽጌ ብሎ ሰየማት ። ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ቦታ ኹሉ ይረዳው ነበርና ።
ልመናው ክብሩ በኛ ለዘለለዓለሙ በዕውነት ይደርብን።
3 views09:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 11:18:02
2 views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 11:18:02 ያልገባው ኮሎኔል ማልታ ግን ለእርሱ ድጋፍ የሰጡት መስሎት በመደሰት አለቃ ቢረሳውን “አቡን አድርጌ ሾሜዋለሁ” ብሎ የሟቹን አቡን መስቀልና መቋሚያ ስጡት በማለት ቢሸልማቸውም መስቀል የሚገባው ለቤተ ክርስቲያን ስለሆነ ለጎሬ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ይሠጥ በማለት አስረከቡ፤ ካሀናቱም በሰላም ወደ እየቤታቸው ተመለሱ፡፡ ጠላት ከሀገር ተባሮ ነፃነት ከተመለሰ በኋላ በ 1935 (36) ዓ.ም. የሰማዕቱ አፅማቸው ከነበረበት አልባሌ ሥፍራ ተለቅሞ በሣጥን ተደርጎ በክብር በመታጀብ በጎሬ ደብረ ገነት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በክብር ተቀምጧል፡፡

ክቡር ደጃዝማች ጣሰው ዋለሉ የኢሉባቦር ጠቅላይ ገዢ በነበሩበት ጊዜ አቡኑ በተረሸኑበት ቦታ ላይ ለመታሰቢያ እንዲሆን ድንጋይ ከማስካባቸው በስተቀር ደንበኛ ሐውልት እንኳን አልቆመላቸውም፡፡ ሆኖም ፣ በ1934 ዓ.ም ጎሬ ከተማ ውስጥ ለመታሰቢያ በስማቸው የተቋቋመ የአቡነ ሚካኤል ትምህርት ቤት አለ፡፡ በ1952 እስከ 1967 ዓ.ም ድረስ የኢሉባቦር ሀገረ ስብከት ለቀ ጳጳስ የነበሩት ባፁዕ አቡነ ቄርሎስ የአቡነ ሚካኤልን ፎቶ ግራፍ ከግብጽ ሀገር ከአሌክሳንድርያ አስመጥተው ጎሬ ከተማ ውስጥ ከደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው አደባባይ በመስተዋት ውስጥ ተደርጎ በአራቱም ማዕዘን እንዲታይ ሆና ተቀምጦ ነበር፡፡ ሆኖም በዘመነ ደርግ ኢሠፓ “አውራ ጎዳና በዚያ በኩል ያልፋል” ብሎ ፎቶ ግራፉ ከቦታው እንዲነሳ ተደርጓል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በጎሬ ከተማ መታሰቢያ የሚሆን ሐውልት ሊያቆሙላቸው ቀን ቆርጠው፣ ዜና ሕይወታቸውንቸለማዘከር ጽሑፎች ተዘጋጅተው ፤ እንደ ነገ ሊሔዱ እንደ ዛሬ ማታ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ ከ ደርግ ጽ/ቤት ተደውሎ እንዳይሔዱቸተብለው ሐሳባቸውን ተግባራዊ ሳያደርጉ ቀርተዋል ይባላል፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ ጠላት እንኳ ለመውሰድ ያልደፈረውን የብፁዕ አቡነ ሚካኤልን የወርቅ መስቀል፣ ከሃምሳ ዓመት በላይ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተከብሮ የኖረውን፣ በኤግዚቢሽን አመካኝተው በኢሠፓ ባለ ሥላጣናት ትእዛዝ ተወስዶ ሳይመለስ መቅረቱ ነው፡፡ መስቀሉ ታሪካዊነት ያለው የቤተ ክርስቲያንና የሀገር ቅርስ በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከተው ክፍል ትኩረት ሠጥቶበት በወቅቱ የወሰዱት ግለሰቦች በኃላፊነት ተጠይቀው ወደ ነበረበት እንዲመለስ ይደረግ ዘንድ ጉዳዩ የሚመለከተን አማኞች ፣ የቅርስ ጥበቃ እና ተቆርቋሪ ተቋማት የቤት ሥራ እንዲሆነን ለማስታወስ እወዳለሁ፡፡

+++ የሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል ረድኤትና በረከት ይደርብን++

ምንጭ፡- (ዝክረ-ሊቃውንት) በመልአከ ምክር ከፍያለው መራሒ (አቶ ዘውዴ ዱባለ መረጃውን ሰጡኝ ብለዋል)
2 views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 11:18:02 ለዚች ለተጨነቀች ሀገር ከልብህ ለመሥራት መወሰንህን መስቀሌን በመምታት ማልልኝ ሲሉኝ፣ የሀገር ፍቅር እንደቃጠላቸው ተሰማኝ” ጓደኞቼ በዕለት ጥቅም እየተደለሉ ለጠላት መግባታቸውን ስሰማ በጣም አዘንኩ፡፡ ሌላው የልብ ጓደኛዬ አቡነ ጴጥሮስ ግን ለጠላት አልገዛም ብለው ለመስዋዕትነት መቅረባቸውን ስሰማ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ይኽ ነው መሐላን ማክበር፡፡ እኔም የጴጥሮስን ፈለግ ነው የምከተለው ብለው አጫወቱኝ፡፡ በቆራጥነታቸው ስደነቅ፣ ፋሽስት ንፁሐንን ለምን እንደሚገድል በጣም ተገረምኩ፡፡ መስቀላቸውን መትቼ ከጎሬ ተመለስኩ፡፡ ወደ ለንደን ከሄድኩ በኋላ ጳጳሱ ተገድለው ጎሬም በጣላት መያዟን ሰምቼ በጣም አዘንኩ፡፡ “አቡነ ሚካኤል ከማልዘነጋቸው ቆራጥ ኢትዮጵያውያን አንዱ ናቸው፡፡ በነፃነት ጉዳይ ኢትዮጵያውያን የተለየ አቋም አላቸው፣ ቋንቋ ፈጽሞ አይበግራቸውም፡፡ ሁሉም በሀገራቸው ጉዳይ ቀልድ እንደማያውቁ የጎሬው ጳጳስ የአቡነ ሚካኤል ሁኔታ አስረድቶኛል፡፡ የጳጳሱ ድፍረትና የሀገር ፍቅር ምን ጊዜም አይረሳኝም” በማለት ምስክርነታቸውን በአድናቆት ሰጥተዋል፡፡

የጠላት ጦር ወደ ኢሉባቦር እየተቃረበ ሲመጣ የጠቅላይ ግዛቱ አስተዳዳሪ የነበሩት ቢተወደድ ወልደ ጻድቅና ሌሎችም የመንግሥት ሹማምንቶች የጎሬን ከተማ ለቀው ወደ ከፋ ሲሰደዱ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በዚያው ያሉትን ምዕመናን ለነጣቂ ተኩላ ጥዬ አልሄድም በማለት በሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ስቃይና መከራ አብረው ለመካፈል በቁርጠኝነት እንዳሉ በኮሎኔል ማልታ የሚመራው የፋሽስት ኢጣሊያን ጦር በኀዳር ወር 1929 ዓ.ም. የጎሬን ከተማ ሲቆጣጠር አቡኑ በከተማው አጠገብ ሳንቢ ቀበሌ ሄደው ሕዝቡ ጠላትን እንዲከላከል በመቀስቀስ ላይ ነበሩ፡፡ ይህንን የሰማው የጠላት ጦር ከዚያው ባስቸኳይ ወታደር ልኮ በማስከበብ በአቡኑ አጠገብ ከነበሩት አርበኞች ጋር ተኩስ ከተለዋወጡ በኋላ በግራጫ በቅሎአቸው ላይ ተቀምጠው መንገድ እንደጀመሩ አንዱ ኢጣሊያዊ ፊሻሌ (መኮንን) አቡኑን ከበቅሎአቸው ላይ አስወርዶ በእግራቸው እንዲሄዱ በማድረግ እርሱ በበቅሎ ላይ ተቀመጠ፡፡ ይህንን አድራጎት የተመለከቱት ከጠላት ጋር የነበሩ በተለይም የሐማሴን ተወላጆች በፈረንጁ ላይ በመቆጣት “የሃይማኖት አባታችን የሆኑትን አዛውንት በቅሎ ቀምተህ እርሳቸውን በእግራቸው እንዲሄዱ ማድረግህ ግፍ ስለሆነ በቅሎዋን መልስላቸውና አንተ በእግርህ ሂድ ያለዚያ እኛ ከዚህች ሥፍራ አንንቀሳቀስም” በማለት በማመጻቸው ኢጣሊያዊው መኮንን በመደንገጥ ከበቅሎዋ ወርዶ ለጳጳሱ መልሶላቸው በበቅሎዋቸው ላይ ተቀምጠው ጎሬ ሲደርሱ በጠላት ሰፈር በተዘጋጀላቸው እስር ቤት በጥብቅ እንዲታሰሩ ተደረገ፡፡ “አቡኑ መንፈሳዊ አባት ስለሆኑ ይፈቱልን” በማለት ሕዝቡ ልመና ቢያቀርብም የጠላት ጦር አዛዥ ልመናን ሳይቀበለው ቀረ፡፡ እንዲያውም፣ ኮሎኔል ማልታ እስረኛውን ጳጳስ ከእስር ቤት በማስመጣት ሕዝብ በተሰበሰበበት አደባባይ አቅርቦ “ለኃያሉ ለኢጣሊያን መንግስት ለመገዛት ቃል ይግቡና ሕዝቡም እንዲገዛልን ይስበኩልን ይህንን ካደረጉ እንፈታዎታለን” በማለት በልዩ ልዩ የመሸንገያ ዘዴ ቢያባብላቸውም ብጹዕ አቡነ ሚካኤል ከሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጠላት ጋር እንደማይተባበሩ ገልጸው በተናገሩበት ቃል “እኔ የማምነው በአንድ እግዚአብሔር ነው ነው፡፡ የምቀበለውና የነፃነት ምልክት ነው የምለው የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ብቻ ነው፡፡ ኢጣሊያን የሚባል ገዥ አላውቅም፡፡ ለወንበዴ ኢጣሊያን የተገዛ እንደ አርዮስ የተረገመ ይሁን፡፡ እንኳን ሕዝቡ ምድሪቱም እንዳትገዛላቸው አውግዣለሁ” በማለት በዚያ በተሰበሰበው ሠራዊት ሁሉ ውግዘታቸውን አሰሙ፡፡

1ኛ/ የጠላት ጦር ጠቅላይ አዛዥ ኮሎኔል ማልታም የጳጳሱን የዓላማ ፅናት ቆራጥነት ከተመለከተ በኋላ እርሳቸውን መሸንገል እንደማይቻል ስላረጋገጠ በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ ወሰነ፡፡

2ኛ/ ቀኛዝማች ይነሱ የልዑል ራስ እምሩ ወንድም የሆኑት ከሰሜን ጦር ግንባር ጀምሮ ከስመ ጥሩ ጀግና ወንድማቸው ጋር በመሆን የጦሩ ግንባር በጀግንነት ሲዋጉ ቆይተው በመጨረሻው ባደረባቸው ሕመም ከወንድማቸው ተነጥለው ጎሬ ከተማ ውስጥ ስለተገኙና ለጠላትም አደገኛ መሆናቸው ስለሚታወቅ እርሳቸውም ከአቡኑ ጋር እንዲገደሉ ተወሰነ፡፡

3ኛ/ የጎሬ ከተማ ነዋሪ የነበሩት ግራዝማች ተክለ ሃይማኖት ጠላት የጎሬን ከተማ ከመቆጣጠሩ በፊት የአውሮፕላን ማረፊያን ሜዳ የጠላት አገር (ዓየር) ኃይል እንዳይጠቀምበት በማስቆፈርና ድንጋይ በማስኮልኮል ከአገልግሎት ውጭ በማድረጋቸው እንዲሁም ከከተማው ውጭ ወደ ገጠር በመሄድ ምቹ ቦታ በመያዝ የአርበኝነት ሥራ ለመስራት ሕዝቡን በማስተባበር ላይ መሆናቸው ስለተደረሰበት በጠቋሚ አማካይነት በወታደር ኃይል ተከበው እንዲያዙ በመደረጉና ከአቡኑ ጋር አብረው እንዲገደሉ በመወሰኑ ከጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በታች አሮጌው ቄራ አጠገብ ጥልቀት ያለው ጉድጓድ ተቆፈሮ፣ በጉድጓዱ ጫፍ ላይ ቀኝ አዝማች ይነሱ በስተቀኝ፣ ግራ አዝማች ተክለ ሃይማኖት በስተግራ፣ እንዲሁም ጳጳሱ መካከል እንዲቆሙ ተደረገ፡፡ በዚህን ጊዜ አቡነ ሚካኤል ለጥቂት ደቂቃዎች ጸሎት ማድረስ እንዲችሉ ፋታ ጠየቀው ጸሎታቸውን አድርሰው ሲያበቁ መስቀላቸውን በግንባራቸው አድርገው “በል እንግዲህ የፈለግኸውን አድርግ” አሉ፤ የወታደሮችም አዛዥ “ተኩስ” የሚል ትእዛዝ ሰጠ፤ ተዘጋጅተው በተጠንቀቅ ላይ የነበሩት ነፍሰ ገዳዮች ሮምታ ተኮሱ፡፡ ብፁዕነታቸውና ሁለቱ አርበኞች ኅዳር24 ቀም በ1929 ዓ.ም. በግፈኛው የፋሽስት ኢጣሊያ ሠራዊት በጥይት ተመትተው በሰማዕትነት ወደቁ፤ እንደ ወደቁም ወደ ጉድጓዱ እንዲጣሉና አፈር እንደለብሱ ተደረገ፡፡ የአካባቢው ነዋሪ የነበሩ የቤተ ክርስቲያን ፍቅር ያላቸው፣ አቶ ወልደ አብ የተባሉትም ግለሰብ “ጳጳስን ያህል የተከበረ ሰው እንዴት አስክሬኑ ያለ ክብር ይጣላል” ብለው በመቆርቆር፣ በሌሊት ሥፍራው ድረስ በመምጣት ጳጳሱን ከተጣሉበት ጉድጓድ አውጥተው በተለየ ስፍራ በክብር ቀብረዋቸዋል፡፡ የጠላት ጦር ጠቅላይ አዛዥ የነበረው ኮሎኔል ማልታ ከተማና በአካባቢው በሚገኙት አብያተ ክርስተያናት ውስጥ በማገልገል ላይ የነበሩትን ካህናት በሙሉ ሰብስቦ ባደረገላቸው ገለጻ “አቡነ ሚካኤል የተገደሉት ለኃያሉ የኢጣሊያን መንግሥት አልገዛም በማለትና ሕዝቡም እንዳይገዛ በማውገዝ በፈጸሙት የአመጽ ሥራ መገደላቸውን አውስቶ፣ ጳጳሱ ሐሳባቸውን እንዲለውጡ ተጠይቀው በእንቢተኝነታቸው ስለጸኑ መረሸናቸውን አስታወቀ፡፡ በዚሁ ላይ ካህናቱ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ በመጋበዝ አቡኑ መገደላቸው ተገቢነው? ወይስ ተገቢ አይደለም? ሲል አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ አፋጠጣቸው፡፡ ካህናቱም ለዚህ አስቸጋሪ ጥያቄ አፋጣኝ መልስ ለመስጠት ግራ ተጋብተው ነበር፡፡ ይህም የሆነበት ምክንያት አቡኑ ዕድል በመሆኑ፣ የአቡኑ መገደል ተገቢ ነው እንደይሉ ደግሞ ለሀገር ነፃነት መቆርቆርና መታገል ጥፋት ያለመሆኑንና እንዲያውም የተቀደሰ ተግባር መሆኑን በሚገባ ስለሚያውቁ ነው፡፡

ካህናቱ በቀረበላቸው ጥያቄ ላይ ባፋጣኝ ተወያዩና ከመካከላቸው በንግግር ዘይቤ ያውቃሉ ብለው የሚያምኑባቸውን አለቃ ቢረሳው ካህናቱን ወክለው መልስ እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ አለቃ ቢረሳውም ለኮሎኔል ማልታ አስቸጋሪ ጥያቄ በሰጡት መልስ “እናንተም ደግ ገደላችሁ፣ እርሳቸውም ደግ ሞቱ” በማለት ተናገሩ፣ አቡነ ሚካኤል በካሕናቱም ሆነ በምዕመናኑም ዘንድ በጣም የተወደዱ ደግ ሰው በመሆናቸው፣ አለቃ ቢረሳው ሰም ለበስ በሆነ ቅኔአዊ ንግግር የአቡኑን ደግነት በማስታወስ መገደላቸውን ተገቢ አለመሆኑን በማውሳት ቢናገሩም ምስጢሩ
2 views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 11:18:02 #ሰማዕቱ_ብፁዕ_አቡነ_ሚካኤል (ዘጎሬ) ቀዳማይ
✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥

[ግንቦት 14/2008 ዓ.ም ሐውልታቸው ስለቆመላቸው ስለ ሰማዕቱ ጠቅለል ያለ ታሪክና መረጃ ለማወቅ የሚፈልጉ ያነቡት ዘንድ የተለጠፈ]

ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የተወለዱት በ1870 (1877 የሚሉም አሉ) ዓ.ም. በጎንደር(በጌምድር) ክፍለ ሀገር በደብረ ታቦር አውራጃ በአፈረ ዋናት ወረዳ ልጫ መስቀለ ክርስቶስ በተባለ ቦታ ከገበሬ ቤተሰብ ሲሆን በተወለዱበትም አካባቢ ግንድ አጠመም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በጥምቀት እንደገና ሲወለዱ ስመ ጥምቀታቸው ኃይለ ሚካኤል ተባለ በኋላ ጊዜ ደግሞ መምህር ሐዲስ ተብለው ይጠሩ ነበር፡፡ ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በዚያው በትውልድ ሀገራቸው ግንድ አጥም ሚካኤል በተባለው ቤተ ክርስቲያን ከነበሩት መሪጌታ ዋሴ ከተባሉ አስተማሪ የመጀመሪያ ደረጃ የቤተ ክህነት ትምህርታቸውን አጠናቀቁ፡፡ ከዚያ በትውልድ ሀገራቸው ዘገቦ ጽዮን በተባለቤተ መቅደስ በዲቁና አገለገሉ፡፡ ትምህርታቸውንም በመቀጠል እዚያው ጎንደር መካነ ሰማዕት ቅዱስ ገላውዴዎስ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤዘርግተው ያስተምሩ ወደ ነበሩት መሪ ጌታ ተድላ ዘንድ ሔደው ጸዋትወ ዜማን፤ ማኅደረ ማርያም ከነበሩት መ/ርወልደ ሩፋኤልም ድጓ በሚገባ ተማሩ፡፡ የዜማ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ መጻሕፍትን ለመማር ጎንደር ከተማ በመሔድ ከመ/ር ተስፋዬዘንድ የብሉያትንና የሐዲሳትን ትርጓሜ በሚገባ ተማሩ፡፡ የመፅሐፍ ትርጓሜ ትምህርታቸውንም ለማስፋት ወደ ቦሩ ሥላሴ አምርተው መ/ርአካለ ወልድ ዘንድ ሐዲሳቱን በሚገባ በማስፋፋትና ቅኔን ከነ ምሥጢሩና አገባቡ ጠንቅቀው ለቅኔ መምህርነት በቅተዋል፡፡ ከቦሩ ሥላሴወደ አዲስ አበባ አቅንተው በገነት ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር ሰፊ ጉባኤ ዘርግተው ያስተምሩ ከነበሩት መ/ር ወልደ ጊዮርጊስ ዘንድየዓሥራ አራቱን ቅዳሴያት ዜማ በጥንቃቄ ተማሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር መዓረገ ቅስናን በወቅቱ የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ግብፃዊው አቡነ ማቴዎስ የተቀበሉት፡፡

ከነበራቸው ግብረ ገብነትየተነሳ ለመኳንንቱ ፣ ለመሣፍንቱና ለወይዛዝርቱ አበ ነፍስ ለመሆን በቁ፡፡ በዚህም ግን አላበቁቅም እውቀታቸውና ግብረገብነታቸው ታይቶ ወደ ቤተ መንግሥቱ በማግባት የምክር ድጋፍ እንዲያደርጉ ተሾሙ፡፡ ከንጉሡ ቤተ መንግሥት በሚወጣው ሕግና መመሪያ በቀጥታ ተሳታፊበመሆን በማገልገል ላይ የነበሩት ብፁዕነታቸው ከዚያ ከፍ ላለውና ለትምህርታቸውና ለማንነታቸው ተስማሚ የሆነ ቦታ ተመርጦላቸው የዜናማርቆስና የዝቋላ ገዳማት አስተዳዳሪ ሆነው ተሾሙ፡፡ የተሰጣቸውን ሐላፊነት በብቃት እየተወጡ ጥቂት ዓመታት ከቆዩ በኋላ እንደ ገናበአዲስ አበባው ደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቆይቶም በማኅደረ ማርያም በእልቅና ተሹመው ለምእመናኑ ትምህርት በመስጠት ፣ ካህናትንበማትጋት ሲያገልግሉ ቆዩ፡፡

አቡነ ሚካኤል በየአድባራቱና በየገዳማቱ እየተሾሙ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት የተወጡና በሐቅ የፈጸሙ አባት ናቸው፡፡ በኮፕትና በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መካከል ለረጅም ዘመናትዘልቆ የነበረው የጵጵስና ሹመት ክርክር ተፈጽሞ ኢትዮጵያውያን ወደ ጵጵስና ሹመት መድረክ እንዲቀርቡ በተደረገ ጊዜ ለታላቁ ሹመትከተመረጡት የመጀመሪያዎቹ አራት አበው መካከል አቡነ ሚካኤል ሲገኙበት በዓለ ሲመቱ የተፈፀመው ግንቦት 18 ቀን1921 ዓ.ም ካይሮ ላይ ነበር፡፡ በተጠቀሰው ዓመተ ምሕረት ጳጳሳቱ ለሢመት ጵጵስናው ወደ ምደረ ግብፅ በሄዱበት ወቅት አንድ አስደናቂ የሆነ ተአምር ተፈጽሞ ነበር፡፡ ይኸውም ከብዙ አመታት በፊት ጀምሮ በመላው ምድረ ግብፅ ዝናብ ታጥቶ አገሪቱ በድርቅ ተመትታ ከቆየች በኋላ እነዚህ ኢትዮጵያውያን አበው የግብጽን ምድር በረገጡበት ዕለት ወዲያውኑ በአስገራሚ ሁኔታ ሰማይ ደመና አዝሎ መላዋ አገሪቱ በዝናብ ተጥለቀለቀች፡፡ በድርቁ ፅናት የተነሳ በስቃይ ላይ የነበረው የግብፅ ሕዝብ ለፈጣሪው ምስጋና በማቅረብ ባሰማው ቃል “ከነዚህ ኢትዮጵያውያን አበው መካከል የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆኑ ጻድቃን አሉበት” በማለት አድናቆቱን ገልጿል፡፡

አቡነ ሚካኤል ተብለው ወደ ሀገራቸው የተመለሱት በፁዕነታቸው ከ ዓመታት በኋላ ‹‹አባ ሚካኤል ጳጳስ ዘአዜብ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ዜና ማርቆስ›› ተብለው በኢሊባቡርና በከፋ ጠቅላይግዛሮች ተሾሙ፡፡ በዚህም ቦታ ሐዋርያዊ ተልእኮአቸውን እየፈፀሙ ለ ሰባት ዓመታት ቆዩ፡፡

በ1928 ዓ.ም. ፋሽስት ኢጣሊያን አገራችንን በወረረችበት ጊዜ ሠላሳ ሺህ የሚሆነው የኢሊባቦር ሠራዊት ወደ ምስራቅ ጦር ግንባር ወደ ኦጋዴን ሲዘምት ስለ ሀገሩ ነጻነት በርትቶ እንዲከላከል ስምቢ ወደ ተባለች የገጠር ቀበሌ በመሔድበፍጹም ወኔ “ኢትዮጵያ የኢትዮጵያን ብቻ እንጂ የሌላ አይደለችም” በማለት ምክርና ትምህርት በመስጠት ቡራኬ ሰጥተው ከማሰናበታቸውም በላይ፣ እርሳቸውም ከደጀኑ ሠራዊት ጋር በጾም በጸሎትና በምሕላ ወደ እግዚአብሔር እየማለዱ፣ ሕዝቡን በማጽናናት ላይ ነበሩ፡፡ ፋሽስት ኢጣሊያን ጦር አዲስ አበባ መግባቱንና ቆራጡም የልብ ጓደኛቸው በፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለሃይማኖታቸውና ለሀገራቸው ነጻነት መሥዋዕት ለመሆን መዘጋጀታቸውን፣ እንዲሁም ከነፃነት አርበኞች ጎን በመሰለፍ ሕዝብ ስለ ሃይማኖቱና ስለ ሀገሩ ነፃነት እንዲዋጋ በመቀስቀስ ላይ መሆናቸውንም ሲሰሙ በጣም ተደሰቱ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ በጊዜው የነበሩ ሌሎች አባቶች ከጠላት ጋር መወገናቸውንና፣ የእርሳቸውን ጠንካራ መንፈስ የተረዳው ጠላት በእነዚህ ባንዳዎች አማካኝነት በአማላጅነት ወደ ጎሬ ሄደው እንዲያመጧቸው ሲጠየቁ አቡነ ሚካኤል በሰጡት መልስ “አቅም የለኝም እንጂ ብችል ኖሮ እናንተም ከኔ ጎን ቆማችሁ ለሃይማኖታችሁና ለሀገራችሁ ነጻነት ብትሞቱ እፈልግ ነበር፡፡ ስለዚህ ወደ እኔ አትምጡ፡፡ አርበኞች ይጣሏችኋል፣ እኔ በሞቴ ቆርጫለሁ፡፡” ብለው የመለሷቸው መሆኑን ታሪክ ያስረዳል፡፡

አገር ወዳዱ አቶ ታደሰ ሜጫ “ጥቁር አንበሳ በምዕራብ ኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ ስለ ገነት ጦር ትምህርት ቤት ምሩቃንና ስለ ጥቁር አንበሳ ሠራዊት ገድል በጻፉት ታሪክ ውስጥ ስለ አቡነ ሚካኤል በሰጠው ምስክርነት “ጎሬ በገባን ጊዜ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በከተማው እንደሚገኙ ሰማን፤ መልእክታችንን ለክቡር ራስ እምሩ አድርሰን ወደ ተሰጠን ስፈር ከመመለሳችን በፊት የጥቁር አንበሳን የሰላምታ መልእክት ይዘን ወደ ብፁዕነታቸው መኖሪያ ቤት ሄድን፤ እርሳቸውም ከተቀበሉንና ቃለ ቡራኬ ካደረጉልን በኋላ ከዋነኞቹ መልእክተኞች ጋር ተነጋግረው የማበረታቻ ቃላቸውንም ወደ ጥቁር አንበሳ ጦር እንዲያደርስላቸው አሳስበው በድጋሚ ቃለ ቡራኬ ሰጥተው አሰናበቱን እኛ ወደ ጥቁር አንበሳ ጦር ከተመለስን በኋላ ራስ እምሩም ጎሬን ለቀው ወደኛ በመጡ ጊዜ ብፁዕነታቸው ‘በዚያው ያሉትን ምዕመናን ለነጣቂ ተኩላ ጥዬ አልሄድም’ በማለት መንፈሳዊ ተግባራቸውን በቆራጥነት ያካናውኑ ነበር” በማለት አድንቀዋቸዋል፡፡

እንዱሁም እስከ ሕይወት መሥዋዕትነት ድረስ የኢትዮጵያና የሕዛቦቿ ፅኑ ወዳጅ የነበሩት ስዊድናዊው ኮሎኔል ካውንት ካርል ጉስታፍ በንሮዝን ስለ ብፁዕ አቡነ ሚካኤል በሰጠው ምስክርነት ቃል እንዲህ ብሎ ነበር፡፡ “ ፎከር የምተባለውን አውሮፕላን እያበረርኩ በጎሬ አቅራቢያ አረፍኩ፡፡ በምዕራብ ኢትዮጵያ የነበሩትን ሚሲዮናዊያን ሌሎች ስደተኞችን አግኝቼ በራስ እምሩ ይመራ ለነበረው ጦር መገናኛ ከፈትኩ፡፡ ጎሬ እንዳረፍኩ አቡነ ሚካኤል አስጠሩኝ፡፡” “በእርግጥ አንተ ዘመዶችህን ከድተህ ለሀበሻ ሕዝብ ለማገልገል ወስለሃልን? ክርስቲያን ነኝ ብለኸኛል፡፡ ለዘመዶችህ ሳታደላ፣
2 views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 09:20:40
2 views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 09:20:39 #የሚኒልክ_ማንነት(ጡት¿)
========//=======
ይግረማችሁና ነገሩ (ዘረኝነቱ) በጣም ከመክረሩ የተነሳ ጭራሽ ታቦት ይዘዉ የተዋጉትን ሖይማኖተኛ ንጉስ ጡት ቆርጠዋል በሚል ተረት አራቅቀው የፈጠራ ታሪኩ በሐሰት በተፃፈበት የመጽሐፉ መቼት በሆነው ኣካባቢ በንጉሱ እጅ የተቆረጠ ጡት የሚያሳይ ሀዉልት በብዙ ሚሊዮን ብር ገንብተው ፣ ያ ትውልድ ያልናቸው ምሁራን ባሉበት መርቀዉ አጨብጭበው ሲከፍቱ ብታዩ ምን ይሰማቸኋል? ሚኒልክን እኮ ነው!
እንደ ሰው አታዝኑም እንዴ ?
ወይስ ታሪክ አላነበባችሁም ?
ምኒልክን የሚያውቅ የለም?
ኢጣሊያ ምነው ዝም አልክ?"
(*ኧረ እናውቃለን ንግስት ሆይ*)
እዘኑዋ ታዲያ የምን ዝም ብሎ ማፍጠጥ ነው ?

ሚኒሊክ ማለት የማረከውን የእናንተን ጄኔራል አልበርቶኒን ያን ሁለ ጉዳቶ እንዳደረሰበት እያወቀ እንኳ የሮም ህዝብ ካሁን አሁን ምርኮኞቹን ሊሰቅሏቸዉ ነው ብሎ ሲጠብቅ << አምላካችን ይቅር ባይ ነውና ይቅር ብለንሃል ሂድ ወደ ሚስትህ፤ ይህን የሟች ባልደረባህን የጄኔራል አርሞንዲ ሻምላም ወስደህ ለሚስቱ በክብር ስጥልኝ ። ብሎ ክእነ ማእረጉ ፣ ከእነ ሻምላው በክብር የሸኘው ንጉስ ማለት ነው፥ በወቅቱ ምርኮኛ ጄኔራል እራሱ ማመን አቅቶት ነበር ፤ የኢጣሊያ ሀዝብም በንጉሱ ምህረት ተደንቆ የአድናቆት መፈክሩን ይዞ በመውጣት በሮም
አደባባይ << ሚኒልክ ቪቫ>> በሚል መፈክር ከተማዋን ሲንጣት ነበር የዋለው!!!

ይህ ንጉሠ_ነገስት እንኳን የሰው ጡት ያውም የዜጎቹን ጡት ሊቆርጥ ቀርቶ ታቦት ይዞ ጦር ሜዳ የሄደ የዓለማችን ብቸኛ ብልህና አማኝ ንጉስ ነው።። አያችሁ እምነት ?

ራስህን አድን መሆኑ ነው፤ ይህን ንጉስ እንደ እኛ የሚያውቀው የለም፣ በየእለቱ የሚፅፋቸው ደብዳቤዎች ወደ እኛ ቤተ መንግስት ይደርሱ ነበር ! አሁንም ድረስ አሉ! በጣም ወዳጃችን ነበር ለአገሩ ፍቅርና ለህዝቦቹ ያለው ክብር ከንጉስ የሚጠበቅ አልነበረም ከዓለማችን ደግና ሩህሩህ ንጉስ አንዱ ፤ ምናልባትም ብቸኛው እሱ ነው።

ይህን ነው የዛሬ ፖለቲከኞች የሚሰድቡት! እሱን የሚሰድቡ ሰዎችን ሳይና ስሰማ(( አይ አሼምድ ! ›) እላለሁ ብቻየን ስለ እነሱ እኔ አፍራለሁ !

በእርግጥም ያሳፍራል ! እንደዚያ አድርገው አዋርደው የመለሷቸው ጠላቶቻቸው እንኳን ስለ ስብዕናቸዉ ይመሰክራሉ ! በቁጭት ተነሳስተው እንኳ እንዲህ ያለ ስም ማጥፋት ውስጥ አልገቡም ! ይህ ታሪክ በየትኛውም የታሪክ ሰነድ ተመዝግቦ አይገኝም በየትኛውም ! ወደ እዚህ የሚጠጋጋ ታሪክ እንኳ የላቸውም እንዴት እንዴት አድርገው እንዳሰቡትና እንደፈጠሩት ያውም በኣጭር ጊዜ ! ግራ ግብት ይለኛል አንዳንዴማ በትክክል ልዑላችን(ዲያብሎስ) በዚያች አገር እየነገሰ እንዳለም እረዳበታለሁ !

ጊዜው ትናንት ነው ፣ መዋሸት የማይቻልበት ትናንት :: የድሮ ታሪክ ቢሆን መቸም ቢዋሽ ያስኬድ ይሆናል ፡፡ በአፈ ታሪክ… እየተባለ ሃሰተኛ ወሬን ማሰራጨት ይቻላል ፤ ዕሁፍ በነበረበት ታሪክ ፀሃፊዎች አገር አጥኝዎች በነበሩበት ፣ ፎቶ ግራፍ ሳይቀር በነበረበት በትናንቱ በሚኒሊክ ዘመን እንዲህ ያለ ተግባር ተፈፅሞ ነበር የሚል ውሸት ነው የሚዋሸው ።

በሚኒሊክ ዘመን የኛ ቆንሲሎች ኢትዮጵያ ውስጥ ነበሩ አገር ጎብኝዎች ሚሲዮኖች ስልጣኔ አለማማጆች ወዘተ… ብዙዎች ነበሩ ቤተ - መንግስቱን ውስጣ ውስጡን ሁሉ እናውቀዋለን፡ እንዲህ ያለ ታሪክ ጨርሶ አልተፈፀመም ማንም ለዚህ ማስረጃ አያቀርብም ! እንዴት ሊታመንና ሊራገብ እንደቻለ ይገመኛል ።

የእነ <<ሻካ ዙሉን>> አይነት አረመኔነት በገዛ ህዝባቸው ላይ ሊፈፅሙ ? የማይታሰብ ነው! ጭራሽ ደግሞ ሚኒልክን! ሚኒልክን በጡት ቆረጣ?!
የሚያማ ትውልድ ተፈጥሮ አየን፣ ልብ በሉ! ይህ ታሪክ ከተፈጠረና ከተሰራጨ ገና ሩብ ምዕተ አመቱ ነው !
አያችሁ የሃሰት ፕሮፖጋንዳ ምን ያህል ክፉ ነቀርሳ እንደሆነ ? የ 7 ሺ ዓመት ታሪክ ያውም የተፃፈ ታሪክ ያላት አገር ፣ ፍርስርሷ የወጣው 25 ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ነው ! አገር ማፍረስ ምን ያህል ቀላል እንደሆነ ተገንዘቡ ! 25 ዓመት በአንድ ብቸኛ የቴሌቪዥን ጣቢያ አንድ አይነትና ተደጋጋሚ መንግስታዊና ህጋዊ የሆነ ውሸት ሲጋት የኖረ ትውልድ ነውና፣ ውሸትንም በሐውልት ቀርዖ ያስቀመጠ መንግስት ነውና መመለሻው ላይገኝ ይችላል ! ይህ እንግዲህ ሁለቱን ትልልቅ ብሄሮች ለዘላለሙ ለማጋጨትና በስልጣን ለመቆየት ሲባል የተደረገ ነው !
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የእንግሊዟ ንግስት በቤልጄም ብራስልስ G 20 ሀገራት ዝግ ስብሰባላይ የተናገሩት ነው ።።
የሳ.ጎ/ቁ.፫
================================

*(እግዲህ እውነቱ ኢሄ ነው የኢትዮጵያ ጥንተ ጠላት የነበሩት እራሱ የማይክዱት የሚመሰክሩት ግን በተረኝነትና በዘረኝነት ከታመሙ ሰዎች አፍ ኢሄ ክርፋት ሲወጣ እደ ቫይረስ ደግሞ ተሰራጭቶ ህዝቡም በዚህ በማይድን በሚመስል በሽታ መታመሙን ስታይ በጣም ያሳፍራል ያሳዝናልም ከላይ ያለችውንም እዉነት ለታመማችሁበት በሽታ መድሀኒቱ ስለሆነ እየመረራችሁም ቢሆን ጠዋት አንድ ማታ አንድ ፍሬ ዋጡበት።።)*

"በዚህ በሽታ ለታመሙትም #ሼር አድርጉላቸው።" "እግዚአብሔርም #ጨርሶ እዲምራቸው።"
#አድዋ
#እውነት_እውነቷን
2 views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-02 09:06:55
2 views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ