Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-13 20:49:48
የመድኃኔዓለም የስቅለቱ በዓል

⓷ በዚህች ዕለት ክፉዎች አይሁድ ከምሽቱ 3:00 ጌቴሴማኒ ውስጥ ያዙት።

ሙሉውን ሌሊት ከቀያፋ ወደ ሐና: ከሐና ወደ ቀያፋ ሲያመላልሱት፣ አስረው ሲደበድቡት አደሩ።

ዝም ቢላቸው ዓይኑን ሸፍነው በጥፊ መቱት። ምራቃቸውን ተፉበት፤ ዘበቱበት፤ ራሱንም በዘንግ መቱት። እርሱ ግን ሁሉን ታገሰ።

❸ በጧት ከገዢው ዘንድ ሞት እንዲፈረድበት አቀረቡት። በሠለስት (ሦስት ሰዓት ላይ) አካሉ እስኪያልቅ እየተዘባበቱ 6,666 ገረፉት።

ሊቶስጥሮስ አደባባይ ላይ እርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት።

❻ ስድስት ሰዓት ላይ በረዣዥም ብረቶች አምስት ቦታ ላይ ቸንክረው ሰቀሉት። ሰባት ታላላቅ ተአምራት በምድርና በሰማይ ታዩ።ዓለም በጨለማ ሳለች ጌታ በመስቀል ላይ ሰባት ቃላትን ተናገረ።

➒ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ላይ በባሕርይ ሥልጣኑ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። በዚያች ሰዓትም ወደ ሲዖል ወርዶ የታሠሩትን ሁሉ ፈታ።



በዚያች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተቃጠለ። ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍጹም ለቅሶን አለቀሰ። ቅዱሳት አንስት በዋይታ ዋሉ። [ማቴ 27:1፣ ማር 15:1፣ ሉቃ 23:1፣ ዮሐ 19:1]
~●~
ለእኛ ለኀጥአን ፍጡሮቹ ሲል ይህንን ሁሉ መከራ የታገሰ አምላክ ስለ አሥራ ሦስቱ ሕማማቱ፣ አምስቱ ቅንዋቱ፣ ስለ ቅዱስ መስቀሉ፣ ስለ ድንግል እናቱ ለቅሶና ስለ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስ ብሎ ይማረን።
~●~ የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች እንኳን አደረሳችሁ፨
2 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 20:49:47
ጉልባን:-  ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው። በጸሎተ ሐሙስ በቤት ውስጥ ከሚፈጸሙ ተግባራት አንዱ ጉልባን ማዘጋጀት ነው። ጉልባን እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ በችኮላ መጓዛቸውን የምናስታውስበት ከእስራኤላውያን የመጣ ትውፊታዊ ሥርዓት ነው።

በአገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ይህ ሥርዓት ዛሬም በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዘንድ ይከበራል።፡ ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን ያስታውሰናል።

በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ፤ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ የመንገድ ተግባራቸው ነበርና። ይህን ታሪክ ለማሰብም በሰሙነ ሕማማት በተለይም በጸሎተ ሐሙስ ቂጣና ጉልባን ይዘጋጃል። በጸሎተ ሐሙስ የሚዘጋጀው ጉልባንና ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል። ይኸውም ጨው ውኃ እንደሚያስጠማ ዅሉ፣ ጌታችንም በመከራው ወቅት ውኃ መጠማቱን ለማስታወስ ነው።
2 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 20:52:28 3.#የምሥጢር #ቀንም ይባላል፡፡
ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አንዱ በዚህ ዕለት ተመሥርቷል፡፡
ይኸውም ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው፤ እንካችሁ ብሉ፡፡ ጽዋውንም አንሥቶ አመሰገነ ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል የሚፈስ ደሜ ነው፤ ከእርሱም ጠጡ፡፡በማለት እኛ ከእርሱ ጋር አንድ የምንሆንበትን መንገድ ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡
በዚህ ዕለት ቅዳሴ ይቀደሳል፡፡ የሚቀደሰውም በለሆሳስ ሲሆን እንደ ቃጭል በመሆን የሚያገለግለውም ጽናጽል ነው፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ ሲመጡ ድምፃቸውን ዝግ አድርገው በለሆሳስ እየተነጋገሩ መምጣታቸውን ለማሰብ ነው፡፡ በቅዳሴውም ኑዛዜ አይደረግም፡፡ ሥርዓተ ቁርባን ግን ይፈጸምበታል፡፡ ይህም ጌታችን የሰጠውን ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን ለማሰብ ነው፡፡ በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሐ ታጥቦ ተዘጋጅቶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ይኖርበታል፡፡

4.#የሐዲስ #ኪዳን #ሐሙስ ይባላል፡፡
ምክንያቱም መሥዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንስሳ ደም የሚቀርበው መሥዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኅነተ ዓለም ራሱን የተወደደ መሥዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ /ሉቃ. 22፤18-20/ ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው ደሜ የሚሆን የአዲስ ኪዳን ነው፡፡ ከእርሱም ጠጡ በማለቱ ይታወቃል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘለዓማዊ ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት መሆኑን በማሰብ የቃል ኪዳኑ ፈጻሚዎች ጠባቂዎች መሆን እንደሚገባን እንማራለን፡:

5.#የነጻነት #ሐሙስ ይባላል፡፡
ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው፡፡ ራሱም ጌታችን መድኃታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጅ ነጻነት ሲናገር ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባሪያ ጌታው የሚደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆቼ ግን ብያችኋለሁ በማለቱ /ዮሐ.15፤15/ ከባርነት ነጻ የወጣንበት ቀን መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል፡፡ ስለዚህ እያንዳንዱ ክርስቲያን ከኃጢአት ባርነት በመራቅ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያወዳጀውን መልካም ሥራ በመሥራት ሕይወቱን በቅድስና መምራት ይኖርበታል፡፡ እርሱ ጠላቶቹ ስንሆን ወዳጆቹ አድርጎናል፡፡ /ማቴ 26፤17-19/

6.#አረንጓዴው #ሐሙስ ይባላል፡፡
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአትክልት ቦታ ስለ ጸለየ፡፡

ሐሙስ የሚጸለዩና የሚነበቡ ምንባባት

ሕዝ.42፥1-21
ሕዝ.43፥1-11
አሞ.4፥2-13
ሃ.አበ.ዘአባ ዲዮናስዮስ 99፥1:11-13
አሞ.3፥1-11
ሃ.አበ.ዘአባ ዲዮናስዮስ 101፥1-19
ሕዝ.20፥27-33
ኤር.8፥4-9
ዘፀ.17፥8-15
ሃ.አበ.እመልእክት ሲኖዲቆን ዘአባ ዮሐንስ 102 ቁጥር እያለፉ ያንብቡ ።ለምሳሌ፦ቁጥር 1፣7፣22፣25እና 27ይሆናል።
ተግሳጽ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ዘፀአ.32፥30-35
ዘፀአ.33፥1-3
ሚኪ.2፥3-13
ሲራ.24፥1-11.
አረጋዊ መንፈሳዊ 34፥1-8
ሃ.አበ.ዘአባ ዮሐንስ ንሰምን 103፥1፣10-14
ኤር.27፥2-15
ሕዝ.20፥39-44
ሚክ.2፥7-14
ሚክ.3፥1-8
ሶፍ.1፥7-18
ሲክ.12፥13 እስከ ፍጻሜ
ድርሳን ዘሰምዖን ዐምዳዊ
መጽሐፈ ስንክሳር
ሃ.አቀ.ዘአባ ፊላታዎስ ለበዉኩ ዘጸሐፍከ ሊተ 104፥1-5
መጽሐፈ ሊቃዉንት ዮሐንስ፣ ሳዊሮስ ይነበብ
መጽሐፈ ታምር
ዘፍ.22፥1-19
ኢሳ.61፥1-7
ኢዮ.27፥1-22
ኢዮ.28፥1-13
ሚል.1፥9-14
ሚል.2፥1-4
ሃ.አበ.ያዕቆብ ዘሥሩግበዉስተ ድርሳኑ 88፥8-10
ሃ.አበ.እመልእክተ ሲኖዲቆን ዘአባ ፊላታዎስ 95፥1፣6-9
ኤር.31፥15-26
ኢሳ.31፥1-9
ኢሳ.32፥1-20
ኢሳ.33፥1-11
ኢሳ.52፥13-16
ኢሳ.53፥1-12
ኢሳ.54፥1-8
መጽሐፈ ዶርሆ
መጽሐፈ ዲድስቅልያ አንቀጽ 19
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ፃዕማ ወድካም አመ ከመዮም ያብጽኀነ ያብጽዕክሙ እግዚአብሔር በፍስሃ ወበ ሰላም አሜን።

መልካም የሰሞነ ሕማማት የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
3 views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 20:52:28
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

እንኳን ለሰሞነ ሕማማት አራተኛ ለሕጽበተ እግር፣ ለጸሎተ ሐሙስ፣ ለምስጢር ቀን፣ ለሐዲስ ኪዳን ሐሙስ፣ ለነጻነት ሐሙስና ለአረንጓዴው ሐሙስ በሰላም አደረሰን።

#ስሙን #ሕማማት #ዘሐሙስ
ከስቅለትና ከትንሣኤ በፊት ያለው ሐሙስ በቤተ ክርስቲያናችን የተለያዩ ስያሜዎች አሉት፡፡

1.#ሕጽበተ #እግር ይባላል
ይህ ስያሜ የተሰጠው ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት ነው፡፡ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠብ” እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ከአጠብኩ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል፤ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ እንዲሁ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁ” (ዮሐ. 13÷13-15) በማለት ትኅትናን በተግባር እየተረጎመና በድርጊት እያሳየ ለቀደ መዛሙርቱ ያስተማረው በዚሁ ዕለት ነው፡፡ይህም የሚያሳየው የዓለምን ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው፡፡ ይህንን ለማስታወስ ዛሬ ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳት በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝቡን ኃጢአት እጠብ ሲሉ በቤተ ክርስቲያናችን የተገኙትን ምእመናን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ሲያጥቡ ያረፍዳሉ፡፡ /ዮሐ. 13፤4-15/

2.#የጸሎት #ሐሙስ ይባላል
የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ የሚደክም ሥጋን የተዋሐደ አምላክ ፍጹም ሰው መሆኑን ለመግለጽና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴ ሴማኒ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ነው፡፡ /ማቴ. 26፤36፣ ዮሐ. 17፤1/ ።
በጌቴ ሴማኒ እየጸለየ ጸሎት ከችግርና ከፈተና እንደሚያድንም ለማስረዳት “ወደፈተና እንዳትገቡ ጸልዩ” በማለት ለደቀ መዛሙርቱ መመሪያና ትምህርት ሰጠ (ማቴ. 26÷40)፡፡
3 views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-24 08:47:55
«ኖኅ ገና ስለማይታየው ነገር ተረድቶ እግዚአብሔርን እየፈራ ቤተ ስዎቹን ለማዳን መርከብን በእምነት አዘጋጀ፥ በዚህም ዓለምን ኰነነ፥ በእምነትም የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ።» ዕብ11፥7

«የእምነት መርከባችን /የኖህ መርከብ/
የሰራዊት ጌታ ወገኖች፣ የድንግል ልጆች፣ የከበሩት ቅዱሳን መላእክት ወዳጆች፣ የሰማእታት፣ የጻድቃን ወዳጆች እዚህ ሰዓት ላደረሰን አምላካችን ምስጋና ይፍሰስለት። ባሳለፍነው መከራ፣ ውጣ ውረድ፣ እንግልት ያልተለዩን ልዑል፣ ድንግልና፣ ቅዱሳን መላእክት ከልብ እናመሰግናለን። በእግዚአብሄር ተሰፋ ፀንታችሁ የጠላትን ማናቸውንም ጥቃት በእግዚአብሄር ፀጋና ቸርነት በተስፋው ታምናችሁ ለተቀበላችሁ፤ የእግዚአብሄር ልጆች፤ እነሆ በትእግስት እፍጻሜው ደርሳችኋል፡፡ የተገባችሁ ስለሆነ ነጩን ልብስ ለብሳችኋል፡፡ ጉዞዋን በጀመረችው የእምነት፣ የጽድቅ መርከብ ተሳፍራችኋል። አንዳንዶች ውስጧ ገብተው ተደላድለው ስፍራቸውን ይዘዋል፡፡ አንዳንዶች በሁለመናዋ ላይ ተንጠላጥለዋል /ዘግይተው ንስሃ የገቡት/ የሆነ ሆኖ እግዚአብሄርን መጠጊያቸው፣ ምሽጋቸው ያደረጉ ሁሉ፤ ዓለም ከገጠማት የእሳት ወንፊትና መጠረግ አምልጠዋል። እግዚአብሄር የገባላቸውን የተስፋ ቃል ታምነውበታልና ድሉን ሊጨብጡ በመገስገስ ላይ ናቸው /በመረከባቸው ተሳፍረው/፡፡ ይህ የሁለተኛው የእሳት ወንፊት ዛሬ በአንደኛው የእሳት ወንፊት ውስጥ የምትበጠረውን ዓለም ወደከፈው የእሳት ወፍጮ የሚያሸጋግር ነው። ጉልበቱም፤ ዛሬ የምናየውንም ሆነ እስከዛሬ ያላየነውን የጥፋትና የጠረጋ ማእበል፤ በ49 እጥፍ አሳድጎ ዓለም በውኑአም በህልሙአም ያላየችውን ጥፋት ይዞ መጥቶአል፡፡» ከመልዕክት 5 ገፅ145

«የእምነት መርከብ ድንግል ናት። የታመኑት 
የትንሣኤው ሙሽሮች ናቸው የሚሳፈሩባት።» ከመልዕክት 9

#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን!
#የእምነት_መርከብ
!
1 view05:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 23:04:38
5 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 23:04:38 . >| በየዕለቱ ከሴተኛ አዳሪ ጋር የሚያድረው መነኵሴ ሞተ |<

~ እጅግ ግርም ያለኝ ታሪክ እነግራችሁ ዘንድ ግድ ይለኛል። ታሪኩ እንደዚህ ነው፦

#_በቅርብ_በምናውቃት_ሀገር ፥ በአንዱ ገዳም ውስጥ መንኵሶ የሚኖር አንድ መነኰስ ነበር። እሱ ያለበት ገዳም አበምኔት፥ እዛው ባሉ መነኰሳት ላይ ነገረ ሠሪን እንደሚቀበል ሲሰማ በዓቱ ትቶ ይወጣል። ሹልክ ብሎ ወጥቶ፣ ከተማ ገብቶ የቀን ሥራን ይሠራ ጀመር።

ከቀን ሥራው የሚያገኘውን ገንዘብ ጥቂት ለሆዱ ያደርግና የተቀረውን ይዞ ወደ ሴተኛ አዳሪዎች ይሄድ ጀመር። የምንኵስናውንም ልብስ ሳይጥል በዚህ ድርጊቱ ገፋበት። ነዋሪውም ያዝንበትና ያማው ጀመር።

{ ቆይ እዚህ ጋር፥ ምን ተሰማችሁ }
{ በዚህ መነኰስ አዘናችሁበት? ወይስ አፈራችሁበት? }

ነገሩ ግን እንዲህ ነው፦
ይሄ በሰው ድርጊት ሰውን ማማት የማይወድ መነኰስ የቀን ሥራውን ሂሳብ ተቀብሎ ይሔድና በከተማ ያሉትን ሴተኛ አዳሪዎች ስም ይጽፋል፤ ይመዘግባል።

ለምን?
ምክንያቱም ከቀን ገቢው ላይ የሽንብራ ቂጣ በልቶ ያስቀረውን ገንዘብ በቀን አንድ ሴተኛ አዳሪ ወደ ኃጢአት እንዳትገባ ይሰጣታል። #_ወደ_ኃጢአት_እንዳትገባ

... በየቀኑ ወደ ሴተኛ አዳሪ ጋር እየሔደ፦ "በዚች ቀን ከአንቺ ጋራ አድራለሁና ራስሽን ለእኔ አዘጋጂ" ይላታል። ከኃጢአትም ሊጠብቃት ከእርስዋ ዘንድ ያድራል። #_ሌሊቱን_ሁሉ_ተነሥቶ_ሲጸልይና_ሲሰግድ_እግዚአብሔርንም_ሲለምን_ያድራል። ሲነጋም ሥራውን ለማንም እንዳትገልጥ አምሏት (ቃል አስገብቷት) ወደ ቀን ሥራው ይሔዳል።

... በዚህም የተነሣ...በከተማው.. እጅግ ይታማ ጀመር። ይህንን መታማቱን ያልወደደች አንዲቱ አመንዝራ ምሥጢሩን (ንጽሕናውን) ተናገረችበት። እርሷም "እንዳናመነዝር ገንዘብ በመስጠት ከኃጢአት ይጠብቀናል እንጂ ነውር የለበትም" አለች።

#_ስትናገርም_ጋኔን_ይዞ_አሳበዳት። የአካባቢው ሰዎችም "ስለዚህ ክፉ ሽማግሌ 'ክፉ ሥራ የለበትም' ብላ ዋሽታለችና እግዚአብሔር መልካም አደረገባት" ተባባሉ።

የቀሩት አመንዝራ ሴቶች ደሞ በእርሷ ላይ የሆነውን በአዩ ጊዜ ደነገጡ። እንደርሷም እንዳያብዱ "እውነቷን ነው" ማለትን ፈሩ። መነኰሱም እውነቱን ሳይናገር ወደ አመንዝራዎቹ ጋር መግባቱን ቀጠለ። ሰዎችም ሁሉ እጅግ ይነቅፉትና ይንቁት ጀመር። (የሚያዝንለትና ከክፉ ድርጊቱ እንዲመለስ የሚጸልይለት ኖሮ ይሆን?!)

°°° በሐሜቱ ያልተበገረው መነኰስ "መነኰስ ሰው አይደለምን? በፍትወት መቃጠልና መሞት አለበትን?" ይላቸው ነበር። እነርሱም "ልብስህን ለውጠህ ሚስት አግባ" አሉት።

እርሱም፦ "አዎን ብወድ በሚስቴ እጠነቀቃለሁ። በዚህም በክፉ አኗኗር እኖራለሁ። እናንተ ግን ከእኔ ዘንድም ሒዱ ምን ትሻላችሁ? በእኔ ላይ እግዚአብሔር ፈራጆች አድርጓችኋልን? ይልቁንስ #_እናንተ_እንዳይፈረድባችሁ_ለራሳችሁ_አስቡ። ፈራጅ አንድ ነውና ዕለቲቱም አንዲት ናትና" አላቸው።

... ይህም #_ቅዱስ_መነኰስ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን አገኘ በሰው ዘንድ ግን የተናቀ ሆኖ ኖረ።

#_ታዲያ_መጨረሻው_ምን_ሆነ?
°°° ከመነኰሱ ድርጊት በኋላ ከእርሱ ጥቅም የአገኙ አመንዝራዎች ዝሙታቸውን ተዉ። አንዳንዱ ሕጋዊ ጋብቻ ተጋብቶ መኖር ጀመረ። አንዳንዱ ወደ ገዳም ገብቶ መንኵሶ፣ በጾም በጸሎት ተወስኖ የኖረ አለ።

°°° ይህ መነኰስ እንደለመደው፥ በአንዲት ዕለት፥ ከአንዲት አመንዝራ ቤት ሲወጣ ያቺን ሴት አስቀድሞ የለመዳት አንድ ሰው አገኘውና "ይህ ሽማግሌ እስከ መቼ ድረስ በዚህ በክፉ ሥራ ይኖራል" ብሎ ፊቱን በጥፊ መታው።

✧ ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን በበዓቱ ውስጥ ሰግዶ ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ውስጥ ሰጥቶ በቤቱም መድረክ፦

"የዚች አገር ሰዎች፥ #_ጊዜው_ሳይደርስ_እንዳይፈረድባችሁ_በማንም_ላይ_አትፍረዱ!" የሚልም ጽሑፍ ተጽፎ ተገኘ።
•• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• ••
✧ እኚህ መነኰስ ፍጹማን መነኰሳት ከሚባሉት ውስጥ አንዱ የሆኑት #_አባ_ባጥል_ዘእስክንድርያ ናቸው። መጋቢት 14 የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው።

"በባሕርይህ ንጹሕ የሆንክ አምላከ አባ ባጥል ሆይ፥ ንጹሕ ልብን ፍጠርልን፤ የቀናውንም መንፈስ በውስጣችን አድስ" እያልን በስማቸው እንማፀን፤ እንዘክራቸው።
•• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• •• ••
5 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 13:17:29
8 views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-20 13:17:29 አዲስ አበባን ለቀን እንውጣ ወይ?
(አባ አምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ)

አዲስ አበባን ለቀን እንውጣ ወይ? ያላችሁኝ ግን በጣም ታበሽቃላችሁ። ለማንና ለምን ብላችሁ ነው የምትለቁ? ለኦሮሞ ወረራ? ለዐረብ ወረራ? የትም ለማይቀረው የጠረጋ ሞት? ኦሮሞም ሆነ ዐረብም እኮ ለወረራ ቢመጣና ቢገባም ራሱ መውጣትና ማምለጥ እንደማይችል ምን ብየ ልንገራችሁ? አዲስ አበባ እኮ መሠረቷም መጨረሻዋም የአማራ ናት። የርስት አገራችሁን ለማን ጥላችሁ ነው የምትወጡ? የሀገሬ የበጌ ምድር ጀግና ገበሬ ብሶቱንና የወንድነት አልጠቃም ባይነቱን በቀረርቶ ሲገልጽ የሚያሰማውን ስነ-ቃል በልጅነቴ እረኛ ሳለሁ የምሰማውንና ዛሬም ድረስ በልቤ ያለውን እስቲ ልንገራችሁ!!
___አባቴ አባቱን ልጁን እኔ ሳውቀው፣
___እንዲያው ባረባ ሰው ሀገሩን ለቀቀው። ወይኔ አምኃ ኢየሱስ!!

ስለዚህ ይህ ምስጢራዊ የጀግንነት መታወቂያ የሆነው ስነ-ቃል ከገባችሁ ሀገራችሁን፣ ርስታችሁን፣ ባድማችሁን ለማንና ለምን ብላችሁ ነው ለቃችሁ የምትሄዱ? የእነሱ እጅ ጠብመንጃ ሲይዝ የእናንተስ እጅ በሶ ነው እንዴ የሚጨብጠው? አዲስ አበባም ሆነች ኢትዮጵያ ዛሬ ለጊዜው በኦሮሞና በትግሬ ትውልዶች እየታመሱ ቢሆንም ነገ ግን በአማራ መንግሥትና በአማራ ጦር ሠራዊት እጅ እንደሚገቡ ምንም አትጠራጠሩ፣ አይዟችሁ፣ ተረጋጉና ከንስሐ ኑዛዜ ጋር ተቆራኝታችሁ በያላችሁበት ሥራችሁን ሥሩ። ኦሮሞና ትግሬ መጨረሻቸዉ ሰዶም ገሞራ ነው አልኳችሁ እኮ።

ዛሬ እንዲህ እንደ ቁንጫ የሚያዘልላቸዉና እንደ ቆርቆሮ የሚያስጮሃቸው ለመጥፋት ነውና አይዟችሁ። እኛም የኢትዮጵያ ጦር፣ የአማራ ጦር፣ የክርስቲያን ጦር የሆንነው ኢትዮጵያንና አዲስ አበባን ለመረከብ በእግዚአብሔር ፈቃድ እየመጣን ስለሆን ተረጋጉ አትጨነቁ። ከዐረብ ወረራ በኋላ ሁሉም ነገር የኛ ነውና ደስ ይበላችሁ።

የአምኃ ኢየሱስ ገ/ዮሐንስ ቁጥር ፰ ለሃይማኖታዊ ጥያቄአችሁ መልስ የተሰጠበትና የጽሑፍመልእክትነው።
6 views10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 23:49:01
8 views20:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ