Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 37

2022-07-08 07:53:13
8 views04:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 07:53:13 ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ ማለት ልዩ ነው ትርጉሙ።
➊.ኢትዮጵያ ማለት “ለአምላክ የሚሰጥ የወርቅ ሥጦታ” ማለት ነው።
:
➋.ኢት=አምላክ፣ ፈጣሪ፣ እግዚአብሔር ማለት ሲሆን ዮጵ= ቢጫ ወርቅ፣ ውድ ወርቅ፣ ልዩ ወርቅ ማለት ነው።
:
➌.ኢትዮጵያ ማለት እኔና እናንተ በምናውቃት ልክ ብቻ ያለች ሀገር አይደለችም።
:
➍.ኢትዮጵያ ማለት ከምድር ሀገራት ሁሉ እጅግ ምስጢራዊና ረቂቅ ሀገር ናት።
:
፩."ብሉይ ኪዳን!"
:
➊ኛ).ሊቀ ነብያት ሙሴን የአመራርነት ጥበብ ያስተማረው ኢትዮጵያዊው ዮቶር ነው።
:
ስለዚህ ለእስራኤል ከፈርዖን ነጻ መውጣት የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሚና አለበት ማለት ነው።
:
አዎ የዮቶር ርስት ውብ ሀገር ኢትዮጵያ ነች።
:
➋ኛ).አሁንም የሊቀ ነብያት ሙሴ ሚስት ሲጳራ ኢትዮጵያዊት ነች።
:
ሲጳራ የኢትዮጵያዊው የዮቶር ልጅ ነች። ሙሴ ይቺን ኢትዮጵዊት ሴት በማግባቱ ወንድሙ አሮንና እህቱ ማርያም ያጉረመርሙበት ነበር። እግዚአብሔርም ገሰፃቸው።
:
➌ኛ).አብርሐምን የቀባው የክርስቶስ ምሳሌ የሚባለው የመጀመሪያው ካህን መልከጼዴቅ ኢትዮጵያዊ ነው።

ይህ ካህን በክርስትና አስተምህሮ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ተደርጎ ይቆጠራል።

➍ኛ).በሀገረ እስራኤል የራሷ ቦታ ያላት (ዴር ሡልጣን) ብቸኛዋ ሀገር ኢትዮጵያ ነች።
:
ይህንን ቦታ ምዕራባውያንና አንዳንድ የምሥራቅ ሀገራት ለመውሰድ ቢሞክሩም እንዳልተሳካላቸው ታሪክ ይዘክራል።
:
➎ኛ).ከባቢሎን ዘመን አስቀድሞ የነበረው ብቸኛው የሰው ልጅ ቋንቋ (ግዕዝ) የሚገኘው ኢትዮጵያ /ቤተ-ክርስቲያን/ ውስጥ ነው።

ይህ ቋንቋ ዓለም እጅግ የሚያከብረው ትልቅና ቀዳሚ ልሣን ነው። ይሄንን ደግሞ ራሳቸው ምዕራባውያን ይመሰክራሉ። በዚህ ቋንቋ ብዙ እልፍ ድርሳናትና ምሥጢራት ተከትበዋል።

➏ኛ).ጻዲቁ አባታችን የሄኖክ የልጅ ልጅ ኖኅ የተቀበረው ኢትዮጵያ/ጎንደር/ ውስጥ ነው።
:
የሰው ልጅ ኃጢአትን በመሥራቱ እግዚአብሔር ምድርን በንፍር ውኃ መላት፣ ኖኅና ቤተሰቦቹ ብቻ ቀሩ። ይህ ሰው መቃብሩ የሚገኘው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።
:
➐ኛ). ኖኅ ራሱንና ልጆቹን ከንፍር ውኃ ያዳነባት መርከቡን ያሳረፋት ኢትዮጵያ/ ጣና አካባቢ ከሚገኘው አራራት ተራራ ላይ ነው።
:
➑ኛ).የመጀመሪያው ሰው አዳም የተፈጠረው ከአቱተ ባሕርያተ ሥጋ ነው።
:
ከእነዚህም መካከል ደግሞ የተፈጠረበት እሳት ውኃና ነፋስ የተገኘው ከኢትዮጵያ ነው። ከዚህም በመነሳት አንዳንዶች አዳምና ሄዋን ኢትዮጵያዊያን ናቸው ይላሉ።
:
እውነት ነው! ኢትዮጵያ የሰው ዘር መገኛ ነች። ያች በቁፋሮ የተገኘች የዝንጀሮ አጽም ድንቅነሽ (ሉሲ) ስለተገኘችባት ሳይሆን የእግዚአብሔር የእጁ ሥራ የሆነው አዳም ስለተገኘባት ነው።
:
➒ኛ).ከገነት ከሚመነጩና ገነትን ከሚያጠጡ አራት አፍላጋት/ምንጮች/ ትልቁ ግዮን ኢትዮጵያዊ ነው።
:
ግዮን ከገነት ይመነጭና ወደ ምድር ይፈሳል፣ ከዚያም የኢትዮጵያን ምድር ይከባል። ይህ ወንዝ ጎጃም ውስጥ ሰከላ አካባቢ ግሽ ዓባይ የተሰኘ ቦታ ላይ ነው የሚፈልቀው። ከዚያም ሙሉ ጎጃምን እንደመቀነት ይዞርና ወደ ግብጽ ይፈሳል።
:
➓ኛ).ሞትን ሳይቀምስ ወደ ብሔረ ሕያዋን የተወሰደውና አዕምሮውን መቶ በመቶ(100%) የተጠቀመበት ብቸኛው የምድራችን ሰው ሄኖክ/ ኢትዮጵያዊ/ ነው።
:
እስከዛሬ ድረስ አዕምሮውን ሙሉ በሙሉ የተጠቀመ ምድራዊ ሰው የለም። የሰው ልጅ የአእምሮው ልዕልና የሚለካው በምድራዊ እውቀት ሳይሆን በሰማያዊ ጥበብ ነው።
:
ሰው የአዕምሮው ልዕልና (IQ) ሲያድግ ወደ ቅድስና ደረጃ ይሸጋገራል እንጅ ምዕራባዊያን እንደሚሉት በምድራዊ ጥበብና እውቀት አይመላም። ይሄን ደግሞ ያደረገ ብቸኛው ሰው ሐበሻው ሄኖክ ብቻ ነው።
:
➊➊ኛ)ሲኦልም ገነትም የሚገኙት በመልአኩ 15 ክንድ ከምድር ከፍ ብለው ኢትዮጵያ (አፋር ኤርታሌና ጎጃም ጣና አካባቢ በቅደም ተከተል) ነው።
:
በድሮው ወሎ ክፍለ ሀገር በዛሬው አፋር ውስጥ የሚገኘው ኤርታሌ የሚባለው ቦታ የራሱ ሰማያዊ ምሥጢር አለው።
:
እዚህ ቦታ ላይ የሚገኘው እሳተ ገሞራ ወይም የእሳት ባህር ሉሲፈር (ሳጥናኤል) የታሰረበት ቦታ መሆኑን አንዳንድ መዛግብት ላይ ለማንበብ ችያለሁ።
:
አዎ ይህ ቦታ የሲኦል መገኛ እንደሆነና ጎጃም የሚባለው ሀገር ላይ በተለይም ደግሞ ጣና ዙሪያ የገነት መገኛ ናቸው።
:
➊➋ኛ).በዓለም ትክክለኛነቱ የተረጋገጠለት የዘመን ስሌት ያለው ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ (ኢትዮጵያ) ውስጥ ነው።

ይህ የዘመን ስሌት አጽዋማትና በዓላት የሚከበሩበት ቀመር የቀናት ብሎም የዓመታት ስሌቱ ያልተበረዘና ትክክለኛ ነው።
:
➊➌ኛ).በነብያት እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች የተባለች ብቸኛዋ ሀገር ኢትዮጵያ ነች።

አዎ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች። መመኪያዋም አለኝታዋም እርሱ ነውና።
:
ይች ሀገር ከፈጣሪዋ ጋር ልዩ ትስስር ያላት የዓለማችን ብቸኛ ሀገር ነች። ፈጣሪ በስጋ የተመላለሰባት ሀገር እስራኤል እንኳን የኢትዮጵያን ያህል ክብር በፈጣሪ ዘንድ የላትም።
:
ለዚህ ደግሞ ማሳያ የሚሆነን ነገር አለ። እግዚአብሔር በነብያቱ በኩል እስራኤላዊያንን ሲገስጽ እናንተ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያዊያን ልጆች (ሐበሾች) አይደላችሁም ነበር ያለ። ልብ በሉ! እንደ ኢትዮጵያዊያን!
:
➊➍ኛ).ታቦተ ጽዮን የሙሴ ጽላት የምትገኝባት ሀገር ኢትዮጵያ ነች።
:
በአምላክ ትዕዛዝና ቀመር የተሰራችው ይህቺ ጽላት በጠቢቡ ሰለሞን የንግሥና ጊዜ የደቡብ ንግስት (ንግስተ አዜብ) ወይም የሳባ ንግስት (ንግስተ ሳባ) ተብላ በምትጠራዋ ንግስት ማክዳ ልጅ በቀዳማዊ ምኒልክ አማካኝነት ነበር ወደ ሀገራችን የገባችው።
:
ምዕራባዊያን ይህቺን መመኪያችንን ጽላት ዘሙሴ ለመውሰድ ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ነገር ግን አልተሳካላቸውም፣ አይሳካላቸውምም። ምክንያቱም እነርሱን ትታ በእኛ ምድር በሀገራችን ትኖር ዘንድ በእግዚአብሔር ፍቃድ መጥታለችና ሊወስዷት ቢኳትኑም አያገኟትም።

➊➏ኛ).የዘንዶ ራስ ተቀጥቅጦ ልዩ ምግብ (ጤፍ) ከፈጣሪ የተሰጣቸው ሕዝቦች /ሐበሾች/ ያሉባት ምድር ነች ኢትዮጵያ።
:
አንተም የዘንዶውን ራስ ቀጠቀጥህ፣ ለኢትዮጵያዊያን ሰዎችም ልዩ ምግብን ሰጠሀቸው ይላል ቅዱስ መጽሀፍ። አስተውሉ! መርምሩም! የእኛ ምግብ አይጥ፣ እባብ፣ አህያ፣ ውሻ ወይም ሌላ የረከሰ ምግብ አይደለም። እንጀራ ነው እንጅ።
:
፪."ሐዲስ ኪዳን!"
:
➊ኛ).የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከድንግል ማርያም በተወለደ ጊዜ በኮከብ እየተመሩ ሄደው የእጅ መንሻ /ገጸበረከት/ ካቀረቡለት (ሰብዐ ሰገል) መካከል የሀበሻው ንጉሥ ባዜን ይገኛል።
:
መድኃኒታችን ሲወለድ መወለዱን በኮኮብ የገለጸላቸው ለእስራኤላዊያን ወይም ለዐረቦች አይደለም። ለሐበሾች እንጅ። ይሄን ክብር ማን አገኘው?
:
➋ኛ).ማኅደረ መለኮት እመብርሃን ድንግል ማርያም በስደቷ ጊዜ በሰላም ኢትዮጵያ ያረፈችባትና በአስራትነት የተሰጠቻት እንዲሁም በተደጋጋሚ በልጇ መስቀል የባረከቻት ቅድስት ሀገር ቅድስት ኢትዮጵያ

እንዴት ነው ወደዳችሁት? ከተመቻችሁ #share በማድረግ ለሌሎች አድርሱ ።

እርሶ ያወቁትን እውቀት ሌሎች ያውቁ ዘንድ ቻናላችንን ሼር በማድረግ ጓደኛዎን ይጋብዙ
7 views04:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 07:21:49 ልብያለዉ ልብ ይበል ጆሮ ያለዉ ይስማ !!!
9 views04:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 07:20:45 አዲስ አበባ
*
4ኪሎ ፒየሳ እንዲሁም መርካቶ
ጠላት ሊያጠፋህ ነው ሳታስበው ገብቶ
ሜክሲኮ ካዛንችስ ቦሌና ሳሪስ
ለምሳ ሳይበቁ አለቁ በቁርስ
አየ መገናኛ አያት ለገጣፎ
ተጨፍጭፎ አለቀ በጥይት ወጨፎ
ወይ አዲስ አበባ ወይ አዲስ አበባ
ድንገት ሳታስበው ልትሆን ነው ገለባ
እንዲያው በጥቅሉ የሸዋ ከተማ
ፊኒፌኔ የሚሏት ያቺ አዲስ አበባ
ጠላት ደመሰሳት በድንገት ገባና
ወደ እንጦጦ ቢሮጥ ወደ የካ ቢሮጥ
ምልክት ከሌለ አይቻልም ማምለጥ።
.
ምጽዋ አደዋ ሸዋ

ሀገሬ ምፅዋ ሀገሬ አደዋ ወየ ሀገሬ ሸዋ
ተቆለለ እሬሳው ሆነ እንድ አሸዋ።
.
ሲዳሞ
*
አዋሳ ይርጋለም በሙሉ ሲዳሞ
ጠላት ሊፈጅህ ነው እንድ እህል ፈጭቶ።
.
ሐረርጌ
*
ወይ ሀገሬ ሀረር ወይ ሀገሬ ሀረር
ተጠርጋ ተበላች እንድ እንጀራ ፍርፍር።
.
ድሬደዋ
*
አንቺ ድሬደዋ አንቺ ድሬደዋ
ሰው ሁሉ አልቆብሽ ልትልብሽ ነው ዳዋ።
.
ጎጃም
*
ኧረ ንቂ ጎጃም ኧረ ንቂ ጎጃም
በልቶ ሊጨርስሽ መጣ አድብቶ ሆዳም።
.
ቤተ አማራ
*
ወልዲያና ደሴ ቤተ አምሀራ ወሎ
ማምለጫ ሊያጣ ነው አላማጣ ቆቦ
.
በጌ ምድር/ጎንደር/
*

ወይ ሀገሬ ጎንደር ስመጠሩው ፋሲል
መሆኑም አልቀረ በአንድ ቀን ሌሊት የድንጋይ ከሰል
አንቺ ደብረ ታቦር እንዲሁም ባህር ዳር
ማንም አያመልጥም ተለይቶ ከሀገር።
.
ወለጋ
****
ወለጋ ወለጋ ወለጋ ወለጋ
ሊጨርስሽ መጣ አራዊት በመንጋ።
.
ጅማ
*
ክርስቲያን አራጇአንቺ አገሬ ጅማ
ዝልልሽን ቅመሽው ጣፋጭ ነው መራራ በይ ቅመሽውማ ቀምሶ መቅረት የለም በደንብ ጠጭውማ አዙሮ እስኪደፋሽ የክርስቲያን እምባ
.
ትግሬ
*
ከሀዲቱ ትግሬ ከሀዲቱ ትግሬ
መሄጃ አጣሁ አለች ተሰበረ እግሬ
ዋይ ዋይ ብላ ጮኸች ዘሎ ሲያንቃት አውሬ
ድረሽልኝ አለች ኢትዮጵያ ሀገሬ
ያድንሽ አለቻት አለኝ ያልሽው ጦሬ።
27 አመት ኢትዮጵያን አጥፍቶ ሲዘል የነበረው ትግሬ በከበሮ
ገባለት ከአገሩ ሙሾ ተደርድሮ
ማን ሊጨርሰው ነው እሬሳውን ቀብሮ።
እንቅፋቱም ይምታህ እሾህም ይውጋህ
እባቡም ይንደፍህ ሰርዶውም ይጥለፍህ
ከእንግዲህስ በቃኝ ጫማ አልገዛልህ
የታባህ አንተግሬ መሄጃም የለህ
መቆሚያ ልታጣ ደረሰ ቀንህ
እንዲያው ዝም ብለህ ለምን በእጆችህ።
.
ኦሮሞ
*
ሁሉ ነገር ኬኛ የምትል ኦሮሞ/2/
ደምህ ሊፈስ ነው እንድ ወንዝ ሞልቶ
ሞት መጣ ሊጠርግህ በየቤህ ገብቶ
አራዊቱም ይጥገብ እሬሳህን በልቶ
.
አማራ
*
አየ ጉድ አማራ አየ ጉድ አማራ
ምነው ከበደበት የቁጣው መከራ
ወገኑን ወገኑ በመግደሉ ነዋ።
.
ኢትዮጵያ
****
የኢትዮጵያ ምድር እንዲያው በጥቅሉ
ሰሜኑ ደቡቡ ምዕራቡ ምስራቁ
ገጠሩ ከተማው ትንሹ ትልቁ
እንዲያው ሳያስቡት በሌሊት ደቀቁ
ከመቶ ሚሊዮን ዘጠናው አለቁ።
ሰአሊ ለነ ቅድስት።
.
ምንጭ፡- አባ አምኃ ኢየሱስ ገብረ ዮሐንስ መልክት ሁለት 2011 ዓ.ም
10 viewsedited  04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:37:13 ንስሓ ምንድን ነው?

የንስሓ ነገር ሲነገር ከሥሩ
ብዙ ታሪክ አለው ብዙ ነው ምሥጢሩ፡፡

የንስሓ ምሥጢር ሲነገር በቅኔ
ዘላለም መራቅ ነው ከክፉ ኩነኔ፡፡

ንስሓ ምንድን ነው ? ካላችሁ በቃል
መጸጸት ነው በቃ በሰሩት በደል፡፡

ከልብ ተጸጽቶ ባለፈው ኀጢአት
በጾም ጸሎት ስግደት እንዲሁም ምጽዋት
መልካም እየሰሩ እስከ እለተ ሞት
ሁሌም እግዚአብሔርን ከልብ በመፍራት
መኖር ነው በደስታ እስካሉ በህይወት፡፡

የጠባቧ መንገድ አስጎብኚና መሪው
የንስሓን ነገር እስኪ እንመርምረው፡፡

ንስሓ እምነት ነው ንስሓ ተስፋ ነው
ንስሓ ፍቅር ነው ንስሓ ለውጥ ነው
ክፉ የሆነውን ለይቶ ማወቅ ነው
እሱን ላለመስራት ሁሌም መወሰን ነው፡፡

ባለፈው ኀጢአቱ ያልተማረ ፍጡር
ምንም አልገባውም የንስሓ ምሥጢር ፡፡

በመቶ ብርና በመቶ ስግደት
በሦስት ቀን ጾምና በሦስት ቀን ጸሎት
አይቆምም ንስሓ ገናም ወደፊት፡፡
መልካም እየሰሩ መኖር ነው ንስሓ
በሳምንት አያልቅም በትንሽ አምኀ፡፡

የነነዌ ሰዎች ንስሓ ገቡና
ሦስት ቀን ሦስት ሌሊት በአንድ ላይ ጾሙና
የታዘዘው መቅሰፍት ወደላይ አቀና፡፡

ሁሉም ዳኑ ያኔ ተቀስፎ ከመሞት
ግን ከዚያ በኀላ ንስሓውን ተውት?፡፡
ቢተውት አይተውም ያልተዋቸው ጌታ
ያወርደው የለም ወይ መቅሰፍቱን አንድ አፍታ፡፡

ስለዚህ ንስሓ የነፍስ ምግብ ነው
ሥጋ ሦስት ቀን በልቶ ይኖራል ወይ በዚያው?
እንኳን በዚያ ሊኖር ሥጋ አስችሎት
ቁርስ ምሳ በልቶ ካልደገመ እራት
አበቃልኝ ይላል የሞተ መስሎት፡፡

እንደዚህ ነው በቃ ንስሓ ማለት
ቶሎ ተጸጽቶ በሰሩት ኀጢአት
መልካም እየሰሩ ለላይኛው ቤት
ዘላለም መራቅ ነው ከዓለም ክፋት፡፡

ተፈጸመ ቀን 22 /10/2014 ዓ፡ም
13 views08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 23:03:20
13 views20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 23:03:20 ✞✞✞ እንኩዋን ለታላቁ ነቢይና ሰማዕት "ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ" ዓመታዊ የልደት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*" ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ "*+

=>ቅዱስ ወንጌል ላይ ዘካርያስ ካህኑና ቅድስት ኤልሳቤጥ በሰውና በእግዚአብሔር ፊት ያለ ነቀፋ የሚኖሩ ጻድቃን ነበሩ" ይላቸዋል፡፡(ሉቃ. 1:6)
እሊህ ቅዱሳን ባልና ሚስት ግን መካኖች በመሆናቸው ልጅ ሳይወልዱ ዘመናቸው አልፎ ነበር:: እንደ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ዕድሜአቸው የኤልሳቤጥ 90 የዘካርያስ 100 ደግሞ ደርሶ ነበር::

*ፍጹም መታገሳቸውን የተመለከተ ጌታ በስተርጅናቸው ከሰው ሁሉ በላይ የሆነ: ትንቢት ለብቻው የተነገረለት (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) ታላቅ ነቢይን ይሰጣቸው ዘንድ መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤልን ላከላቸው::

*ቅዱስ ዘካርያስ ሰው ነውና ከደስታ ብዛት በመከራከሩ ድዳ ሆነ:: ቅድስቲቷ ግን መስከረም 26 ቀን ታላቁን ሰው ጸንሳ ለ6 ወራት ራሷን ሠወረች:: በ6ኛው ወር የፍጥረት ሁሉ ጌታ በተጸነሰ ጊዜ የአርያም ንግሥት ድንግል እመቤታችን ደጋ ደጋውን ወደ ኤልሳቤጥ መጣች:: ሁለቱ ቅዱሳት የእህትማማች ልጆች ናቸው::

*የአምላክ እናቱ ስትደርስና "ሰላም" ስትላቸው መንፈስ ቅዱስ በእናትና ልጅ ወርዶ ኤልሳቤጥ በምስጋና: ዮሐንስ ደግሞ ገና በማሕጸን ሳለ በደስታ ዘለለ (ሰገደ):: ከዚህ በሁዋላ ሰኔ 30 ተወልዶ: አባቱ ዘካርያስ "ዮሐንስ" ሲለው አንደበቱ ተፈወሰ::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከተወለደ 2 ዓመት ከ6 ወር በሆነው ጊዜ ሰብአ ሰገል በመምጣታቸው በእሥራኤል ምድር የሚገኙ ሕጻናትን ሔሮድስ ቁዝ አስፈጀ:: ትንሽ ቆይቶም አይሁድ ለሔሮድስ
ስለ ቅዱሱ ሕጻን ነገሩት:: "ሲጸነስ የአባቱን አንደበት የዘጋ: ሲወለድ ደግሞ የከፈተ 'ዮሐንስ' የሚባል ሕጻን አለና
እሱንም ግደል" አሉ::

*እናቱ ቅድስት ኤልሳቤጥ ይዛው ስትሸሽ ካህኑንዘካርያስን ግን በቤተ መቅደስ መካከል ገድለውታል::አረጋይት ኤልሳቤጥም ሕጻኑን እያሳደገች በገዳመ ዚፋታ ለ3 (5) ዓመታት ቆይታለች:: ቅዱስ ዮሐንስ 5 (7) ዓመት ሲሞላው ግን
እዚያው በበርሃ እናቱ ዐረፈች:: ከሰማይ ዘካርያስና ስምዖን ወርደው ቀበሯት::

*ሕጻኑ ዮሐንስ ሲያለቅስ ድንግል ማርያም ስንት አገር አልፋ ሰማችው:: እርሷም ስደት ላይ ነበረችና:: ከጌታ ጋር
በደመና ሒደው ድንግል አቅፋ አጽናናችው:: ጌታንም "እንውሰደው
ይሆን?" አለችው:: ጌታችን ግን "ለአገልግሎት እስክጠራው እዚህ
ይቆይ" አላት:: ባርካው: አጽናንታውም ተለያዩ::

*ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ በኋላ በዚያ ቆላ የግመል ጠጉር ለብሶ: ጠፍር ታጥቆ ብህትውናውን ቀጠለ:: ለ25 (23)
ዓመታትም በንጽሕና ሲኖር ከምድር አራዊትና ከሰማይ መላእክት በቀር ማንንም አላየም:: ይሕችን ዐመጸኛ ዓለምም አልቀመሳትም::

*ከዚህ በኋላ 30 ዘመን ሲሞላው እግዚአብሔር ከሰማይ ተናገረው:: "ሒድ! የልጀን ጐዳና ጥረግ" አለው:: ነቢያት
ስለዚህ ነገር ተናግረው ነበርና:: (ኢሳ. 40:3, ሚል. 3:1) አባቱ
ዘካርያስም "ወአንተኒ ሕጻን ነቢየ ልዑል ትሰመይ: እስመ ተሐውር ቅድመ እግዚአብሔር ከመ ትጺሕ ፍኖቶ" (ሉቃ.
1:76) ብሎ መንገድ ጠራጊነቱን ተናግሮ ነበርና::

*ቅዱስ ዮሐንስ በዚያ ጊዜ በኃይለ መንፈስ ቅዱስ እየገሰገሰ ከበርሃ ወደ ይሁዳ መጣ:: ያዩት ሁሉ ፈሩት: አከበሩት:: ቁመቱ ቀጥ ያለ: ጽሕሙ እንደ ተፈተለ ሐር የወረደ: ጸጉሩ የቁራ ያህል የጠቆረ: መልኩ የተሟላ: ግርማው የሚያስፈራ ገዳማዊ ነውና::

*ፈጥኖም ሕዝቡን ለንስሃ ሰበከ: ለንስሃም በርካቶችን አጠመቃቸው:: በዚህ አገልግሎት ለ6 ወራት ቆይቶ
ጌታችን ወደ እርሱ ዘንድ መጣ:: ዮሐንስ ሰማይን ናምድርን የያዘ ፈጣሪ 'አጥምቀኝ' ብሎ ሲመጣ ደነገጠ::
የሚገባበትም
ጠፋው::

*"ጌታዬ! አንተ አጥምቀኝ" አለው:: ጌታ ግን "ፈቅጄልሃለሁ" አለው: አጠመቀው:: በዚህ ምክንያት ቅድስት ቤተክርስቲያናችን "መጥመቀ መለኮት" ትለዋለች፡፡

=>"የመጥምቁ ዮሐንስ ስሞች"

1.ነቢይ
2.ሐዋርያ
3.ሰማዕት
4.ጻድቅ
5.ካሕን
6.ባሕታዊ/ገዳማዊ
7.መጥምቀ መለኮት
8.ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ)
9.ድንግል
10.ተንከተም (የብሉይና የሐዲስ መገናኛ ድልድይ)
11.ቃለ አዋዲ (አዋጅ ነጋሪ)
12.መምሕር ወመገሥጽ
13.ዘየዐቢ እምኩሉ (ከሁሉ የሚበልጥ)

❖ጌታችን መድኃኔ ዓለም የመጥምቁ ዮሐንስን አስቦ ይቅር ይበለን:: ጸጋውን: በረከቱንና ክብሩንም ያሳድርብን::

++"+ ጌታ ኢየሱስ ለሕዝቡ ስለ ዮሐንስ ሊናገር ጀመረ . .

ምን ልታዩ ወጣችሁ? ነቢይን? አዎን እላችኋለሁ፥ ከነቢይም የሚበልጠውን።
እነሆ፥ መንገድህን በፊትህ የሚጠርግ መልክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ ተብሎ የተጻፈለት ይህ ነውና። እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም።
(ማቴ. 11:7-15)

❖ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ❖
13 views20:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 21:13:47 በተረጋጋ መንፈስ አዳምጡት ቤተሰቦቸ
14 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 21:11:06
15 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 21:11:05
15 views18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ