Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-17 21:59:14 #ጠማማ_የሆነው_ዛፍ ሁሉ ትልቅ ትንሽ ሳይባል ሙሉ በሙሉ ይቆረጣል! ለማገዶነት እንዲውልና አመዱም ሳይቀር በነፋስ ፊት እንዲበተን፡ ስም አጠራሩም እንዳይገኝ #በአብርሃሙ_ሥላሴ ተወስኗል። ከጥመት ይሰውረን!
2 views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-17 21:35:28 ሰባኛ ተአምር
ስለ ባለጠጎችና ስለ ችግረኞች
፩ ይቅርታው ቸርነቱ ለዘለዓለም በዕውነትህ ለሁላችን ይደረግልንና ጌታችን አምላካችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገው ተአምር ይህ ነው ።
፪ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ አላቸው፤ በዚያን ጊዜ ለካደኝና
ለከዳኝ ወዮለት ለማትጠፋ የእሳት እራት ይሆናልና ።
፫ ፤ በክርስቲያናውያን ምዕመናኖቼ ላይ የሣቅ የተሣለቀ ወዮላት ፤ በፍርድ ቀን በሰው ሁሉ
ፊት መላእክት ይሣለቁበታልና። የቤተ ክርስቲያናትን መመዝበር የሚደግፉ ሁሉ ወዮላቸው
ሥጋቸውን እሳት ታንጨረጭረዋለችና ።
፬ ፤ በክርስቲያናዊ ጥምቀት ያልተጠመቀችውን የአረመኔያዊት ሴት ያገባ ወዮለት አጋንንት
በሲኦል እንደ ጭቃ ይረግጡታልና ፤ ከጠላቶቼ መናፍቃን ጋር አብሮ የሚበላ የሚጠጣ
ወዮለት ፤ በፍርድ ቀን ከነሱ ጋር እደምረዋለሁና ።
፭ ፤ የመበለታትን ልጆች የሚንበድል ወዮለት ፤ ማደሪያው እና በጨለማ ይሆናልና ፤
በአገልጋይ ካህናቶቼ የሚሣለቅ በነሱም ላይ በሐሰት የሚመሰክር ወዮለት ፍርዱ ሊሻሻልለት
አይችልምና ፤ በቅዱስ ሥጋዬና በክቡር ደሜ የሚሣለቁ ወዮላቸው የቅጣት ፍርዳቸው
ይግባኝ የለውምና ።
፮ ፤ በጐቼን ለማጥፋት የሚያስቡ ወዮላቸው ከመጻሕፍት ውስጥ ስሜን ለሚሠርዙ
ወዮላቸው ፤ ከነገሥታትና ከመኳንንት ጋር ወንድሞቻቸውን ለሚያጣሉ ወዮላቸው ፤
በተድላቸውና በደስታቸው ከነዳያን ጋራ ለማይተባበሩ ባለጸጐች መዮላቸው ፤ መኖሪያ
ቦታቸው ከዚያ በእሳት ወላፈን ከሚለበለበው ባለጸጋ ጋር ይሆናልና።
፯፤ በምዕመን ወንድሙ ላይ ዋሽቶ ክፉ ስም የሚያወጣ ወዮለት ፤ የሰው ገንዘብ ለሚሠርቅ
ወዮለት ፤ የነዳያንን ገንዘብ በግፍ ነጥቆ የሚበላ ወዮለት፤ የወንጌልን ቃል ለማይሰሙና
ለሚቀጣጠቡበትም ወዮላቸው
፰ ፣ ንጹሓን የሚሆኑ አል ዮቼ የቤተ ክርስቲያናትን ካህናት የሚረግም ወዮላቸው። ከአፀደ
ቤተ ክርስቲያን አንዲት ጠጠር ስንኳ ያነሣ ወዮለት ፤ ከበጐቼ አንዱን ያናቀ ያቃለለ
ወዮለት አገልጋዮች ካህናቱቼን በግዞት አሥረው ለሚገርፋቸው ለሚወጓቸው
ለሚጠቀጥቋቸው ወዮላቸው ።
፱ ፤ የክህነትን ሕግ ለሚደፋፈሩ ወዮላቸው። ካህን ሥልጣን የሚሰጠው በእኔ ፈቃድ ነውና
የክህነቱንም ሕግ በትክክል ቢጠብቅ እሱ የዘለዓለም ሕይወት አለው ፤ አገልጋዮች ካህናትን
ከክብር የሚያሳንሱ ወዮላቸው ፤ እኔ ከዘመናት በፊት መርጬ ሾሜአቸዋለሁና
እወዳቸዋልሁምና ።
፲ ፤ መንድሞቻቸው ነዳያን እየተራቡ ከመጠን በላይ ለሚመግቡ ወዮላቸው ፤ ከርኵሳን
አሕዛብ ጋር ሥጋቸውን ለሚያረክሱ ወዮላቸው ፤ ዕውነትን ሽሽገው ሐሰትን ለሚያንፀባርቁ
ወዮላቸውን ፤ ክርስቲያኖችን በችግራቸው ጊዜ ለማይራዱ ወዮላቸው። መድ%ቸ@ኑ ።
፲፩፤ ከኢአማንያን ጋር ሥጋቸውን ለሚያረክሱ ሴቶች ወዮላላቸው፤ ላልተጠመቁ
አረማውያንም ምቹ አልጋ መኝታ ለሆኑ ሴቶችም ወዮላቸው ፣ ክብርት ቤተ መቅደሴን
ለሚያረክሱ ወዮላቸው፤ ይህች ቤተ መቅደሴ በሷ ህልዉ ሆኜ የምኖርባት ናትና ።
፲፪ ፤ አገልጋዮቼ ካህናት ወደነሱ ሲመጡ እያዩ ተነሥተው በክብር ላልተቀበሏቸው

፲፪ ፤ አገልጋዮቼ ካህናት ወደነሱ ሲመጡ እያዩ ተነሥተው በክብር ላልተቀበሏቸው
ወንዶችና ሴቶች ወዮላቸው። ካህናት የኔን ሥልጣን የተጐናፀፉ ናቸውና ።
፲፫ ፤ ክፋትን በገዛ እጁ ለሚያመጣት ወዮለት ። እሱስ ባልተወለደ በተሻለው ነበር ፤
ዳግመኛም የወፍጮ መጅ በአንገቱ ላይ አሥረው ከጥልቅ ባሕር በጨመሩት በተሻለው ነበር
፲ሽ እህል ከበላ በኋላ ሥጋዬን ለሚበላ ወዮለት ፤ ከመናፍቃን ጋር በበዓላት ቀን ተድላ
ደስታ በማድረግ በመብል በመጠጥ አብሮ የሚሳተፍ ወዮለት።
፲፭፤ነገር ግን ከወገኖቼ ጋር የፋሲካዬን በዓል የሚያከብር እሱ የተመሰገነ ነው፤ እሱ ከእኔ
ጋር ይሆናል እኔም በጌትነቴ ክብር ከሱ ጋር እሆናለሁ ።
፲፮ ፤ በእኔ ስም የተጠመቁትን ክርስቲያን የሚገድል ወዮላት። በእኔ ዘንድ ኃጢአቱ
አይሠረይለትምና ፤ ልጆቻቸውን ወንድሞቻችውን የሚክዱ ሁሉ ወዮላቸው።
፲፯ ፤ እኔ ሳልልካቸው ነቢይ ነን ብለው ራሳቸውን በነቢይነት ለሚሠይሙ ወዮላቸው፤
ሐዋርያችን ለማይቀበሉ ወዮላቸው፤ ከአረማውያን ጋር በዓል የሚያከብሩ ለአጋንንትም
የታረደውን የሚበሉ ወዮላቸው፤ የምሥራቼን ለልጆቻቸው ለማይናገሩ ወዮላቸው።
፲፰፤የደወል ድምፅ ሰምተው ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን ለመሄድ የማይፋጠኑ ወዮላቸው
በዕለተ ሰንበት ሥራ የሚሠሩ ወዮላቸው፤ በዕለተ ሰንበት የሚሸጡ የሚለውጡ የሚገዙ
ወዮላቸው ፤ በዕለተ ሰንበት የመንገዳቸውን በር ለሚከፍቱ ወዮላቸው ፤ በዚህም
ጥምቀታቸው ይሻርባቸዋልና ።
፲፱ በዕለተ ትንሣኤ ዕድል ፈንታቸው ከሰዶምና ከገሞራ ጋር እንደሆነ በልዑል ክንዴና
በመለኮታዊ ሥልጣኔ እናገራለሁ ፤ ሰንበቶቼን የሻረ ፈጽሞ ፀጥታና ዕረፍት አይኖረውም ።
የክህነትን ሥራ ጊዜያዊ የሚያደርሱ ሥጋዬን ከመብላትና ደሜን ከመጠጣት ቸል የሚል
ወዮለት።
፳ በቅዳሴ ጊዜ ቄሱ ቅዱስ ሥጋዬን እየፈተተ እያለ የሚጫወቱ ወይም የሚነጋገሩ
ወዮላቸው። በዕለተ ሰንበት በመታጠቢያ ትቤ ገብተው የሚታጠቡ ሰዎች ወዮላቸው።
በአምላክነቴ ባሕሯ የሚሰነካከል ወዮለት።
፳፩ ፤ ከቤተ ክርስቲያንና ከመሠዊያው አገልጋዮች ካህናትን ያበረሩ ያሳደዱ ወዮላቸው ፤
ከመናፍቃን ጋር በዓልን ለማክበር የሚተባበሩ ወዮላቸው ። በእኔ ስም ያልተጠመቀችውን
ጡት ለልጁ ያጠባ እንድታሳድገውም ሞግዚት ያደረገ ወዮለት።
፳፪ ከአረማውያን ጋር ለሚጋቡ ወዮላቸው ። መወለዴን መሰቀሌን ክብርት ትንሣኤንም
የሚክዱ ወዮላቸው ። ወንድሞቻቸው በረኃብ በችግር ሲንገላቱ ከመጠን በላይ በድሎትና
በምቾት የሚኖሩ ወዮላቸው፣ በዕለተ ሰንበት ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገስግሰው
ለማይመጡ ወዮላቸው ።
፳፫፤ እሱ ክብር ምስጋና ይሁንና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሕዝብ ሕጉንና ሥርዓቱን
ያስተምሩ ዘንድ ለደቀ መዛሙርቱ ይህን አስተማራቸው።
፳፬ ፤ ይቅርታው ቸርነቱ ለዘላለሙ በዕውነት ለሁላችን ይደረግልን።
2 views18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 20:42:48
4 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 20:42:48 #የኢትዮጵያ_ተዋህዶ_ኦርቶዶክስ_ቤተ_ክርስቲያን -- ጳጳሳት ፤ ቆሞሳት ሊቃውንት መምህራን ዲያቆናት የደብር አለቆች ፤ የሰንበት ትምህርት ቤት አደራጆችና አስተማሪዎች የካህናት ማህበራት ሁሉም ካህናት ፤ አባቶች ባሕታውያን መነኮሳት ተብለው በቤተ ክርስቲያኗ የሚታዘዙ የሚደገፉ ፤ የተወገዙበትን ጥፋት ያላረሙ አሁንም ውግዘቱን የናቁና ያላከበሩ በግልፅ እግዚአብሔርንና ፈቃዱን የናቁ ሆነዋል ፡፡

ማህበረ እርኩሳንም እንዲሁ ፈቃደ እግዚአብሔርን በተግባር አፍርሰዋል ፡፡ ወጣቱንም ቀይደው ወኔ ቢስ ውሽልሽል ስለ ቤተ ክርስቲያኑም ስለእምነቱም የማይጠይቅ የመዝሙር ሰራዊት አድርገውታል ፡፡
ቅኖች ለበጎነት መስርተውት እንደስሙ ማህበረ ቅዱሳን ሁኖ ያሳለፈ ዛሬ ሰሙን ፍፁም ባረከሱ በግብር በለወጡ የመንግሥት ሰላዮች የደህንነት ተቀጣሪዎች ተሞልተው ከፍተኛውን ስውር የማፍረስ ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ ፡፡ ቤተ ከርስቲያናችን ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ የከፋ መፍረስ ውስጥ ወድቃለች ፡፡ የተጉት አባቶቻችን ሞተውላት ተቀጥቅጠውላት የእግዚአብሔርን እውነትና ፈቃድ ያለነቀፋ ኖረውበት እንዳላስረከቡን የዛሬው የቤተ ክርስቲያን እረኞች በጎቻቸውን የበተኑ ፤ ለአውሬ ያስበሉ ፤ የወፈረውን አርደው የበሉ ፍፁም እግዚአብሔርን የካዱ ሆነው ተገኝተዋል ፡፡ ከዚ ሁሉ በላይ ቤተ ክርስቲያንን የፖለቲከኞች ፤ የዘረኞች ፤ የወያኔና የኦሮሙማ ሰላዮች ፤ ዘራፊዎች ፤ ካቶሊኮች መናፍቆች ሁሉ የተደራጁበት እንዲሆን አድርገዋል ፡፡ አለመፀፀትም የጥፋት ሁሉ መፈፀሚያ ሥፍራ ሆኖአል ፡፡ ቤተ ክርስቲያን ተዋህዶ ቤታችን ዘረኞች ሌቦች የመንግሥት ተጠዋሪዎች የሚዘውሯት የጠፋች የነጋዴዎች የተብታቢዎች የአጋንንት ሳቢዎች የሰላቢዎች መናኸሪያ ሆናለች ፡ ከሁሉ የሚደንቀው የምእመኑ ጅልነት ነው ፡፡ቤተ ክርስቲያንን እያፈረሱ እያየ የአባቶቻችንን መሰረትና ሕግ ድንበር ሲፈርስ እያየ የሚሰሩትን ዲያብሎሳዊ ሥራ በግልፅ እየተመለከተ እኔ ምን አገባኝ እንደሥራቸው እያለ ልማዱን ብቻ የሚያደርስ በምግባር የሞተ እምነቱን ሲያጠፉ ድንበሩን ሲያፈርሱ እየተመለከተ በርቱ አፍርሱ የሚል ያህል ገንዘቡን ለነዚህ አፍራሾች በአሥራት ሥም በበኩራት ስም በማልማት ስም እየቸረ ይበልጥ ቤተ ክርስቲያን እንድትጠፋ አድርጎአል ፡፡

በመሆኑም ምእመኑም ለቤተ እግዚአብሔር መጥፋት እኩል ተጠያቂ ሆኖአል ፡ ፍርዱም ተከትሎታል ፡የሚያሳዝነውም ያፈረሱትን እንደ እውነተኛ አገልጋዮች ቆጥሮ አብሮ መጥፋቱ ነው ፡፡ በደብዳቤያችን በሁሉም መልእክቶች ስለ ኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ስለ ኢትዮጵያ ጉዳት በዝርዝር ገልፀናል ፡፡ ማንም አልሰማም ፡ አገልጋዮች የተባሉ ሁሉ እግዚአብሔርን በተግባራቸው ክደውታል ፤ ንቀውታል ፤ አቃለውታል ፡፡ ፍፁም ደፍረውታል አስቀንተውታል ፡፡ ቁጣው እንዲነድ አድርገዋል ፡፡ ማህበረ ቅዱሳን ነን የሚሉ ግን በግብራቸው እርኩሳን ቤተ ክርስቲያንን ምን ያህል እንዳጠፏት የወጣቱን ውሽልሽልነትና የመዝሙር ሰራዊት ወኔ ቢስ የአባቶቹን ገድል ሰምቶ ትንሸም እንኳን ወኔ ያልፈጠረበት አፍርተው ቆሞ እንደሃውልት ቤተ ክርስቲያን ስትጠፋ ስትወረር ስትፈርስ አይሰማም ይዘምራል መዝሙር ያጠናል ፡፡ በቃ ! ትውልዱ የደነበሸ ነው የምንለው በዚህም እንደሆነ ልብ ሊባል ይገባል ፡፡

የተዋህዶ ቤታችን ቀኖናዋ ዶግማዋ ስርአቷ ሲጣስ እንደድንጋይ ተጎልቶ ይመለከታል ፡፡ የሰንበት ትምህርትም ቤት እንዲሁ የመቀጣጠሪያ የምግጠት ቦታ ሆኖአል ፡ ሙሉ በሙሉ ቤተ ክርስቲያናችን ውሉ የጠፋ ልቃቂት ሆናለች ፡ በተለይ ወጣቱን ኢትዮጵያዊ በፍፁም የማይሰማ የማይለማ እንዲሆን ትልቅ ሥራ ተሰርቶአል ፡፡ መሃበረ እርኩሳኖች የቀደሙትን መልካም የእግዚአብሔር ሰዎች በድካማቸው በእውነተኝነታቸው በትክክለኛ ተዋህዶነታቸው የደከሙበትን መንፈሳዊ ምግባር ዛሬ የተኮለኮሉት ቦታውን ሁሉ የተቆጣጠሩት ሙሉ በሙሉ ከመንግሥት የሥለላ መረብ ጋር የተቆራኙ ናቸውና ለዚያ አገልጋይ እንዲሆን አድርገውታል ፡፡

መንግሥት ብቻ ሳይሆን መላው አለም ያሉ ዋና ዋና የሥለላ ተቋሞችም በሥልጠና ስም ብዙዎችን የሥውር ማህበራቸው አባል አድርገዋቸው ወጣቱን የተዋህዶ አማኝ ውሽልሽል ስለአገሩ የማይገደው መዝሙር ብቻ ሕይወት የሚመስለው የመናፍቃንን ስልት ያጠና አድርገው ቀርፀውታል ፡፡ አካሄዳቸውን በሚገባ የገለፀባቸው የኢትዮጵያ አለም ብርሃን በመሆኑ እጅግ በመበሳጨታቸው ከነጩም ከኛውም ከመንግሥትም የተውጣጡ ሰላዮች እንዴት የኢትዮጵያ አለም ብርሃን ቤተሰቦችን እንደሚበትኑ ስልት ተነድፎ በመላው አገሪቱ በነዚሁ የማሕበረ እርኩሳን መሪዎች ጋር በመቀናጀት በኛ ላይ የማያቋርጥ ዘመቻ ከፍተው ብዙ ወጣቶችን ከእውነት መንገድ እኒዲወጡ አድርገዋል ፡፡

ስልታቸው ሥጋዊ ነውና ፈሪሳዊያንም ፀሃፍትም ይህንኑ ስልት ይከተሉ ስለነበር እነሱም በዚያው ስልት ሄደውበታል ፡፡ በኛ ላይ ስለፈፀሙት ጥቃት ሥራቸውን ስለሚያውቁት አንደግመውም ውጤታቸውን ወደፊት ያፍሱታል ፡፡ ያለፍርድም አያመልጡም ፡፡ ነጮች ሙሉ በሙሉ የዲያብሎስ ታማኝ ሰራተኞች እንደመሆናቸው ሁሉ ፈቃዱን ፈፃሚዎች በመሆናቸው ቤተ ክርስቲያንንም በሃይማኖቶች ሕብረት ስም ተጣብቀዋት የነሱ ጉዳይ ፈፃሚ ሆናለች ፡፡ እግዚአብሔርም የመጀመሪያውን እርምጃ በቤተ ክርስቲያን ላይ እንዲጀመርና እንዲፀዳ ወስኖአል ፡፡ ትእዛዝም ተላልፎአል ፡፡

ለማህበረ እርኩሳን በእናንተ አሳብ በማስመሰያ ስማችሁ በግብራችሁ መጥራት ስላለብን ነው ማሕበረ እርኩሳን የምንላችሁ ሙሉ በሙሉ ትወገዳላችሁ ፡፡ እዚያ ውስጥ ያላችሁ በአለማወቅ የተነገራችሁን ብቻ አንጠልጥላችሁ በኢትዮጵያ የአለም ብርሃን ላይ ለተደረገው ዘመቻ በሃሳብም በአቋምም በማናቸውም መንገድ የደገፋችሁ ሁሉ የብርቱው ቅጣት ፍርደኛ ናችሁ በጥቂት ቀናት ውስጥ ነገ ተነገወዲያ ሳትሉ ከዚህ የእርኩሳን ማሕበር እንድትወጡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ነውና ይድረሳችሁ ፡፡ ደግሜ እላችኋለሁ ከፊታችሁ ባለው ጥቂት ቀኖች ውስጥ ውጡ ንስሀ ግቡ ምናልባት ብታመልጡ የዋህ ለሆናችሁ ሳታነቡ ሳትሰሙ ሳትረዱ እኛን ስታወግዙ ዘመቻ ስታካሂዱ የነበራችሁ ሁሉ ፍርዱ በደጃችሁ ነውና !! ሰው ሰው ነው አስቦ ማድረግ የሚገባው አረጋግጦ አመሳክሮ ተረድቶ አንብቦ ማስረጃ ጨብጦ ነው መወሰን የሚገባው ፡ የዚህ የእርኩሳን ማሕበር አባል የሆናችሁ ሁሉ በግልፅ ልታውቁ ይገባል የሰላዮች የመንግሥት አገልጋዮች መጠቀሚያ ናችሁ ፡፡ አንድ እንስሳ አለች በቀቀን ትባላለች አንተ የተናገርከውን ቃል መልሳ የምትናገር ከፍ ዝቅ ሳታደርግ ያንኑ ቃልህን የምትደግምልህ በቃ እናንተ የሰው በቀቀኖች ናችሁ በሉ የተባላችሁትን አድርጉ የተባላችሁት ያንኑ የምታደርጉ የምትናገሩ ሳታጣሩ ሳትመረምሩ እውነቱን ከውሸት ሳትለዩ እንዳመጣላችሁ የምትናገሩ ስለሆናችሁ ፍርዳችሁ እጅግ ብርቱ አጥፊአችሁ ሆኖ ለአፈፃፀም ወጥቶአል ፡ በፈፃሚዎችም እጅ ደርሶአል ፡፡

ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሀናዊ መንግስት በአብርሀሙ ሥላሴ ፍቃድ በጥር 7 /2015 የወጣ አስረኛ መልእክት ገፅ 27 እና 28 ላይ የተወሰደ
ሙሉዉን ለማንበብ ወይም ለማዳመጥ ወደላይ ታገኙታላችሁ ሙሉውን አንብቡ አድምጡ ።
በኋላ አልሰማውም ነበር ማለት ከተጠያቂነት ከእግዚአብሔር ፍርድ አያድንም
(ስማ የአዳም ዘር ከአብርሀሙ ሥላሴ የመጣብህን ፍርድ ከመጠረግህ ከመደምደምህ በፊት አድምጥ ንስኃ ግባ )

አስተዋይ ልቦና ይስጠን !!!

3 viewsedited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 09:15:39
3 views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 09:15:39 በጻድቁ አቡነ ተክለ-ሃይማኖት ስም ቤተክርስቲያን ብታንጽ ተክለ-
ሃይማኖትን ለማምለክ አይደለም እግዚአብሔርን እንጂ !!! ስለዚህ የትም
ቤተክርስቲያን ብንሄድ የምናመልከው እግዚአብሐየርን እንጂ መታሰቢያ
የተደረገለትን ቅዱስ አይደለም፡፡ ስለዚህ ተክለ-ሃይማኖት ፣ ገብረ-
መንፈስ ቅዱስ ፣ ቅዱስ ሚካኤል………እየተባለ መሰየሙ ለመታሰቢያቸው
ነው፡፡ ይህንን በማሰብ ቤተክርስቲያናችን ከአንድ እስከ ሠላሳ ያሉትን
ቀናት በቅዱሳን ስም በመሰየምና መታሰቢያቸውን በማድረግ ለዘመናት
ስትዘክራቸው ኖራለች ወደ ፊትም እስከ ዕለተ ምጽአት ድረስ
ታስባቸዋለች፡፡
+++ መታሰቢያቸውንም የምታደርገው ቅዱሳን የተወለዱበትን ፣
ያረፉበትን እና ተአምራት ያደረጉበትን ቀናት መሰረት በማድረግ ነው፡፡
በቅዱሳን ጸሎትና ምልጃ እንተማመናለን!!! ጸሎታቸው ድውይን
ይፈውሳል!!! ቃልኪዳናቸው መንግሥተ ሰማያትን ያወርሳሷል!!! ቅዱሳንን
እንድናከብርና እንድናስባቸው ለረዳን ለቅዱሳን አምላክ ክብርና ምስጋና
ይሁን አሜን፡፡

ምንጭ: የተለያዩ በርካታ ድርሳናት ገድላት እንዲሁም ደህረ ገጾች። በዘሪሁን እሸቱ ተዘጋጀ 05/07/2009 ዓ.ም
21 21 21
ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት
የሲኦል ደጆች አይችሏትም
ቤተክርስቲያን አትታደስም!
የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም
እንማልዳለን!
(መጽሐፈ ሚስጢር)
የእግዚአብሔር ቸርነት፣ የድንግል ማርያም አማላጅነት፣ የቅዱሳን
መላእክት ተራዳኢነት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የቅዱሳን ሐዋርያት፣
የቅዱሳን አበው መነኮሳት፣ የቅዱሳት አንስት፣ የደናግላንና የቅዱሳን ሁሉ
ምልጃና ቃል-ኪዳናቸው ባለንበት ከሁላችን ጋር ይሁን!!!
†† † † ††
ለአባ ሕርያቆስ ፤
ለቅዱስ ኤፍሬም ፤
ለቅዱስ ያሬድ ፤
ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
ለአባ ይስሀቅ
የተገለጸች እመቤታችን እኛንም በበረከት እና በረድኤት ትጎብኘን ፤
ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ዘንድ ታማልደን ፤ አሜን!!!
†† † † ††
ከዋክብት የሚያመሰግኑት
በስማቸውም የሚጠራቸው:
የፀጋው ብዛት የማይታወቅ
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ለሐዋሪያት
እንዲሁም ለቀደሙ አባቶቻችን ምሥጢሩን እንደገለጽክላቸው ለእኛም
ግለጽልን። አሜን አሜን አሜን!!!
3 views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-16 09:15:39 ያለ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም

ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዢ።

በእመቤታችን ቅድሰተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ሰም የተሰየሙ
አድባራትና ገዳማት

በሺ ከሚቆጠሩ በእመቤታችን ስም ከሚጠሩ አድባራትነና ገዳማት 112 የሚደርሱ ከተለያዩ ድርሳናትና ገድላት መጽሐፍት እንዲሁም ድህረ ገጾችን በመዳሰስና በመፈለግ ያገኘሁት ነውና ያንብቡት: በእርሶም አካባቢ የሚገኙ በእመቤታችን ስም የሚጠሩ አቢያተክርስቲያናት ካሉ ኮሜንት ያድርጉና ያስተዋውቁ...መልካም ንባብ።
°
1. ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ፅዮን ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም
2. ርእሰ አድባራት ወገዳማት ዳግሚት ጽዮን አዲስ ዓለም ማርያም
3. ግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም
4. ጻድቃኔ ማርያም ገዳም
5. እንጦጦ ማርያም
6. ከሳ ማርያም
7. ክራ ማርያም
8. ቦሌ ማርያም
9. ገነተ ማርያም
10. ገንዘ ማርያም
11. አገረ ማርያም
12. ገበዘ ማርያም
13. ደረፎ ማርያም
14. ጀበራ ማርያም
15. እንዳ ማርያም
16. ጩጊ ማርያም
17 እያሆ ማርያም
18. ጉንዶ ማርያም
19 ደብረ ማርያም
20. አዋሽ ማርያም
21. ጀበራ ማርያም
22. ዳባት ማርያም
23. ጋሬሮ ማርያም
24. ዶርዜ ማርያም
25. ዳየር ማርያም
26. አኖማ ማርያም
27. አምባ ማርያም
28. ቡራዮ ማርያም
29. ሰቅላየ ማርያም
30. አዳዲ ማርያም
31. ዋሸራ ማርያም
32. ሌድሆ ማርያም
33. አጉንታ ማርያም
34. ማኅደረ ማርያም
35. ዠመዱ ማርያም
36. አሸተን ማርያም
37. ከንፈረ ማርያም
38. መስኖ ማርያም
39. ጎራንዳ ማርያም
40. ውቕሮ ማርያም
41. ጎርጎራ ማርያም
42. ይዶንጋ ማርያም
43. ወንበር ማርያም
44. ጭራሮ ማርያም
45. ተድባበ ማርያም ዕርስ አድባራት ወገዳማት
46. አዱላላ ማርያም
47. ጉሬዛም ማርያም
48. ደራስጌ ማርያም
49. መናገሻ ማርያም
50. ብርብር ማርያም
51. ምንዝሮ ማርያም
52. አትሮንስ ማርያም
53. መርጡለ ማርያም
54 አዘዞ ሎዛ ማርያም
55. ጎንደሮች ማርያም
56. ኩክ የለሽ ማርያም
57. ሾላ ማርያም ገዳም
58. ጮለሚት ማርያም
59. ደብረ ሲና ማርያም
60 ጅብ አስራ ማርያም
61. ጣራገዳም ማርያም
62. የአስግዲት ማርያም
63. ቀፀባ ማርያም ገዳም
64. ደብረ እንቁ ማርያም
65. ፈላሻ ጭቃ ማርያም
66. ደብረወርቅ ማርያም
67. እሳቷ ፅዮን ማርያም
68. ግምጃ ቤት ማርያም
69. ቁልቋል በር ማርያም
70. አዝዋ ማርያም ገዳም
71. ኦቶና ቅድስት ማርያም
72. አይሰድ ማርያም ገዳም
73. ድንጋይ ደበሎ ማርያም
74. ሻኪሶ ቅድስት ማርያም
75. ቂልጦ ቅድስት ማርያም
76. ኮረሜ ቅድስት ማርያም
77. ዕጣኖ ቅድስት ማርያም
78. ዳንግላ ቅድስት ማርያም
79. በልበሊት ማርያም ገዳም
80. ወይ ብላ ቅድስት ማርያም
81. አጤ ዋሻ ቅድስት ማርያም
82. ደብረ ወርቅ ማርያም ገዳም
83. አራት ኪሎ ቅድስት ማርያም
84. ብርጭቆ ፍኖተ ሎዛ ማርያም
85. ብርጊዳ ቅድስት ማርያም ገዳም
86. ደብረ ብርሃን ቅድስት ማርያም
87. ኢባንቱ ህንዴ ቅድስት ማርያም
88. አብችክሊ ጽርሐ ጽዮን ማርያም
89. ቆቦ ደ/ፅ/ቅ/ ማርያም ካቴድራል
90. ጉንዳጉንዶ ቅድስት ማርያም ገዳም
91. አረርቲ ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም
92. ዱብቲ ደብረ ፀሐይ ቅድሰት ማርያም
93. ዝዋይ ሐይቅ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም
94. አሰላ ደብረ ምፅላል ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን
95. ወልቂጤ ደብረ ፅዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን
96. ሉማሜ ሳአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን
97. ሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን
98. ደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን
99.የግዮን ( ወሊሶ ) ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ድንግል ማርያም ገዳም
100. ዚጉዳ ኪዳነ ምህረት
101. እንጦጦ ኪዳነምህረት
102. አንጎለላ ኪዳነ ምህረት
103. እንዶዳም ኪዳነ ምህረት
104. ቃሊቲ ቁስቋም ማርያም
105. ዑራ ኪዳነ ምህረት ገዳም
106. ሽሮ ሜዳ ቁስቋም ማርያም
107. ዶይናና የቤሌ ኪዳነምህረት
108. ቃሊቲ ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን
109. የሰዲ ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን
110. ደብረ ፀሐይ ቁስቋም ማርያም ገዳም
111. ቆጠር ገድራ ቅድስት ኪዳነምህረት ገዳም
112. የአደሬ ደብር ሰዋስው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ገዳምን

‹‹አቢያተ ክርስቲያናት ለምን በቅዱሳን ስም ተሰየሙ?
ይህች ተዋህዶ ሃይማኖት ፈርዶባት ከተቃዋሚዎች ጥያቄ አርፋ
አታውቅም :: ፈሪሳዊነትን የተጣቡ መናፍቃን በቅዱሳን ክብርና
አማላጅነት ላይ ያላቸው ጥያቄ ሳይቆም ስለምን በድንግል ማርያም ፣
በቅዱስ ሚካኤል ፣ በቅዱስ ገብርኤል ፣ በተክለ ሃይማኖት እና በሌሎች
ቅዱሳን ስም አቢያተ ክርስቲያናትን ትሰይማላችሁ? ስለምንስ በቅዱሳን
ስም መታሰቢያ ታደርጋላችሁ? በማለት ይጠይቃሉ፡፡ አስተውላችሁ ከሆነ
በአራቱም ወንጌላዊያን ክታብ ላይ አይሁድና ፈሪሳውያን ጌታችን
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተለያዩ መስቀለኛ ጥያቄዎች ይፈትኑት
ነበር፡፡ ፈሪሳውያን እንደውም የጥያቄ ሰዎች መሆናቸው ይነገርላቸዋል፡፡
ጌታችንን የማይጠይቁበት ርዕሰ ጉዳይ አልነበረምና፡፡ ምን አልባትም
ፈሪሳውያን የጥያቄ ሰዎች ብቻም አልነበሩም ምልክትንም የሚፈልጉ
እንጂ :: ይህንንም ጉዳይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ አስተውሎት ነበርና
“መቼም አይሁድ ምልክትን ይሻሉ የግሪክ ሰዎችም ጥበብን ይፈልጋሉ”
1ኛ ቆሮ 1÷22 በማለት ተናግሯል፡፡ አይሁድ ወደተለያዩ የማደናገሪያ
ጥያቄዎች የገቡበት ዋነኛ ምክንያት በጌታችን ላይ አንዳች እንከን
ባለማግኘታቸው ነው ፡፡ ዛሬ ደግሞ ተረፈ አይሁድ የሆኑ ተቃዋሚዎች
(መናፍቃን) በዚህች ጥርጥር በሌለባት አማናዊት እምነታችን ላይ
እንከን ቢያጡ አንድ ሺህ አንድ ጥያቄዎችን ይዘው ተነሡ :: መነሻቸው
ቅናት ይሁን ምን ባናውቅም ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ስለምን
አቢያተ ክርስቲያናትን በቅዱሳን ስም ሰየመች ብለው ሲያርጎሞጉሙ
እንሰማለን፡፡
21
+++ ስለምን አብያተ ክርስትያናት በቅዱሳን ስም ተሰየሙ ለሚለው
ጥያቄ ለመመለስ የነቢዩ የኢሳያስን ቃል መመልከት ብቻ በቂ
ነው፡፡“እግዚአብሔር ሰንበቴን ለሚጠብቁ ደስ የሚያሰኝንም ነገር
ለሚመርጡ ቃል ኪዳኔንም ለሚይዙ ጃንደረቦች እንዲህ ይላል በቤቴና
በቅጽሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ይልቅ የሚበልጥ (መታሰቢያ
ስምን) ለዘለዓለም እሰጣቸዋለሁ” ይላል ኢሳ 56÷4::
+++ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንም ይህንን መጽሐፍ
ቅዱሳዊ ቃል መሠረት በማድረግ በቅዱሳን ስም አብያተ ክርስትያናትን
አንጻ መታሰቢያቸውን ታደርጋለች፡፡ ነገር ግን በማናቸውም ቅዱሳን ስም
አምልኮ አትፈጽምም!!! ዛሬ መናፍቃን በደመ ነፍስ እነደሚናገሩት አብያተ
ክርስቲያናት በቅዱሳን ስም የተሰየሙት ሊመለኩ እይደለም!!! ለምሳሌ
4 views06:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 21:15:16
3 views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 21:15:16 ንስሐ የገባ ኃጢአተኛ ሰውም ቢሆንና ይህቺን ጸሎት ቢጸልይ ሺህ ነፍሳትን ከሲዖል አወጣለታለሁ።
✧†✧
ጻድቁ እስትንፋሰ ክርስቶስ በእጅጉ የሚታወቁበት አንድ ትልቅ ቃል ኪዳን አላቸው፡፡

በአምላክ ልቡና የሚገኝ፣ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ልቡና የሚገኝ፣ በቅዱስ ሚካኤልና በቅዱስ ገብርኤል ልቡና የሚገኝ እንደ መልክአ መድኃኔዓለም ያለች እጅግ አስገራሚ ጸሎት አለቻቸው።

እርሷን ጸሎት በጸለዩ ጊዜ እልፍ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጣሉ፡፡

ጸሎቷም የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሎቹ የተቀበሉትን ጸዋትዎ መከራዎች ሁሉ ታዘክራለች፡፡ በእያንዳንዱ ክፍልም የጸሎት ማሳረጊያ አቡነ ዘበሰማያት ይደግማሉ፡፡

ንስሓ የገባ ኃጢአተኛ ሰው እንኳን ቢሆን ይህችን የአቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስን ጸሎት በጸለየ ጊዜ ሺህ ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ጌታችን በማይታበል ቃሉ ለአባታችን ነግሯቸዋል፡፡

እያንዳንዱን የመድኃኔዓለምን የሰውነት ክፍሎች በሙሉ እየጠቀሰች መከራዎቹን የምታዘክረውን ይህቺን በአምላክ ልቡና ያለች ግሩም የሆነች ጸሎት "ነፍሳትን ከሲኦል አታወጣም" ብሎ የሚጠራጠር ቢኖር መንግስተ ሰማያትን አያያትም፡፡
◦◆◦◆◦
የካቲት 9 | አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ የመነኰሱበት ዕለት ነው፨
◆◦◆
3 views18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 16:00:21
4 views13:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ