Get Mystery Box with random crypto!

ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።

የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የቴሌግራም ቻናል አርማ dereje1678 — ደረጀ እና የድንግል ማርያም ልጆች ግሩፕ ቻናል።
የሰርጥ አድራሻ: @dereje1678
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 81

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-03-02 09:06:55 ነገር ግን የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቃል ባትሰማ፥ ዛሬም ያዘዝሁህን ሥርዓቱንና ትእዛዙን ሁሉ ባትጠብቅ ባታደርግም፥ እነዚህ መርገሞች ሁሉ ይመጡብሃል ያገኙህማል።

በከተማ ርጉም ትሆናለህ፥ በእርሻም ርጉም ትሆናለህ።

እንቅብህና ቡሃቃህ ርጉም ይሆናል።

የሆድህ ፍሬ፥ የምድርህም ፍሬ፥ የላምህም ርቢ፥ የበግህም ርቢ ርጉም ይሆናል።

አንተ በመግባትህ ርጉም ትሆናለህ፥ በመውጣትህም ርጉም ትሆናለህ።

እኔን ስለ ተውኸኝ፥ ስለ ሥራህ ክፋት፥ እስክትጠፋ ፈጥነህም እስክታልቅ ድረስ በምትሠራው ሥራ ሁሉ እግዚአብሔር መርገምን፥ ሽሽትን፥ ተግሣጽን ይሰድድብሃል።

እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ ከምትገባባት ምድር እስኪያጠፋህ ድረስ ቸነፈርን ያጣብቅብሃል።

እግዚአብሔር በክሳት፥ በንዳድም፥ በጥብሳትም፥ በትኲሳትም፥ በድርቅም፥ በዋግም፥ በአረማሞም ይመታሃል፤ እስክትጠፋም ድረስ ያሳድዱሃል።

በራስህም ላይ ሰማይ ናስ ይሆንብሃል፥ ከእግርህም በታች ምድሪቱ ብረት ትሆንብሃለች።

እግዚአብሔር የምድርህን ዝናብ ትቢያና አፈር ያደርጋል፤ እስክትጠፋ ድረስ ከሰማይ ይወርድብሃል።

እግዚአብሔር ከጠላቶችህ ፊት የተመታህ ያደርግሃል በአንድ መንገድ ትወጣባቸዋለህ፥ በሰባት መንገድ ከእነርሱ ትሸሻለህ ለምድርም መንግሥታት ሁሉ ድንጋጤ ትሆናለህ።

ሬሳህ ለሰማይ ወፎች ሁሉ ለምድርም አራዊት መብል ይሆናል፥ የሚያስፈራቸውም የለም።

እግዚአብሔር ፈውስ በሌለው በግብፅ ቍስል በእባጭም በቋቁቻም በችፌም ይመታሃል።

እግዚአብሔር በዕብደት፥ በዕውርነት፥ በድንጋጤም ይመታሃል።

በቀትርም ጊዜ ዕውር በጨለማ እንደሚርመሰመስ ትርመሰመሳለህ፥ መንገድህም የቀና አይሆንም፤ በዘመንህም ሁሉ የተጨነቅህ የተዘረፍህም ትሆናለህ፥ የሚያድንህም የለም።

ሚስት ታጫለህ፥ ሌላም ሰው ከእርስዋ ጋር ይተኛል፤ ቤት ትሠራለህ፥ አትቀመጥበትም፤ ወይን ትተክላለህ፥ ከእርሱም አትበላም።

በሬህ በፊትህ ይታረዳል፥ ከእርሱም አትበላም፤ አህያህ ከእጅህ በግድ ይወሰዳል፥ ወደ አንተም አይመለስም፤ በግህ ለጠላቶችህ ትሰጣለች፥ የሚያድንህም አታገኝም።

ወንዶችና ሴቶች ልጆችህ ለሌላ ሕዝብ ይሰጣሉ፥ ዓይኖችህም ያያሉ፥ ሁልጊዜም ስለ እነርሱ ሲባክኑ ያልቃሉ፤ በእጅህም ኃይል ምንም አይገኝም።

የምድርህን ፍሬ ድካምህንም ሁሉ የማታውቀው ሕዝብ ይበላዋል፤ አንተም ሁልጊዜ የተጨነቅህ የተገፋህም ትሆናለህ።

ዓይኖችህም ከሚያዩት የተነሣ ዕብድ ትሆናለህ።

እግዚአብሔር ፈውስ በሌለው በክፉ ቍስል ጕልበትህንና ጭንህን ከእግርህ ጫማ እስከ አናትህ ድረስ ይመታሃል።

እግዚአብሔርም አንተን በአንተም ላይ የምታነግሠውን ንጉሥ አንተና አባቶችህ ወዳላወቃችኋቸው ሕዝብ ይወስድሃል፤ በዚያም ሌሎችን የእንጨትና የድንጋይ አማልክት ታመልካለህ።

እግዚአብሔርም በሚያገባህ በአሕዛብ መካከል ሁሉ ድንጋጤ ምሳሌም ተረትም ትሆናለህ።

እጅግ ዘር ወደ እርሻ ታወጣለህ፤ አንበጣም ይበላዋልና ጥቂት ትሰበስባለህ።

ወይን ትተክላለህ ታበጀውማለህ፤ ትልም ይበላዋልና ከእርሱ ምንም አትሰበስብም፥ የወይን ጠጁንም አትጠጣም።

የወይራ ዛፍ በአገርህ ሁሉ ይሆንልሃል፤ ወይራህም ይረግፋልና ዘይቱን አትቀባም።

ወንዶችና ሴቶች ልጆች ይወለዱልሃል፤ በምርኮም ይሄዳሉና ለአንተ አይሆኑልህም።

ዛፍህን ሁሉ የምድርህንም ፍሬ ኩብኩባ ይወርሰዋል።

በአንተ መካከል ያለ መጻተኛ በአንተ ላይ ከፍ ከፍ ይላል፥ አንተም ዝቅ ዝቅ ትላለህ።

እርሱ ያበድርሃል፥ አንተ ግን አታበድረውም፤ እርሱ ራስ ይሆናል፥ አንተም ጅራት ትሆናለህ።

ዘዳግም 28፥15-48
2 views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 20:49:53 በክፉዎች፡ላይ፡አትቅና፥ዐመፃንም፡በሚያደርጉ፡ላይ፡አትቅና፤እንደ፡ሣር፡ፈጥነው፡ይደርቃሉና፥እንደ፡ለመለመ፡ቅጠልም፡ይረግፋሉና።በእግዚአብሔር፡ታመን፥መልካምንም፡አድርግ፥በምድርም፡ተቀመጥ፥ታምነኽም፡ተሰማራ።
በእግዚአብሔር፡ደስ፡ይበልኽ፥የልብኽንም፡መሻት፡ይሰጥኻል።መንገድኽን፡ለእግዚአብሔር፡ዐደራ፡ስጥ፥በርሱም፡ታመን፥ርሱም፡ያደርግልኻል።ጽድቅኽን፡እንደ፡ብርሃን፡ፍርድኽንም፡እንደ፡ቀትር፡ያመጣል።
ለእግዚአብሔር፡ተገዛ፥ተስፋም አድርገው።መንገድም፡በቀናችለትና፡ጥመትን፡በሚያደርግ፡ሰው፡አትቅና።ከቍጣ፡ራቅ፥መዓትንም፡ተው፤እንዳትበድል፡አትቅና።
ክፉ፡አድራጊዎች፡ይጠፋሉና፤እግዚአብሔርን፡ተስፋ፡የሚያደርጉ፡ግን፡እነርሱ፡ምድርን፡ይወርሳሉ።ገና፡ጥቂት፥ኀጢአተኛም፡አይኖርም፤ትፈልገዋለኽ፡ቦታውንም፡አታገኝም።
ገሮች፡ግን፡ምድርን፡ይወርሳሉ፥በብዙም፡ሰላም፡ደስ፡ይላቸዋል።ኀጢአተኛ፡ጻድቁን፡ይመለካከተዋል፥ጥርሱንም፡በርሱ፡ላይ፡ያንገጫግጫል።እግዚአብሔር፡ይሥቅበታል፥ቀኑ፡እንደሚደርስ፡አይቷልና።
ኀጢአተኛዎች፡ሰይፋቸውን መዘዙ፥ቀስታቸውንም፡ገተሩ፡ድኻውንና፡ችግረኛውን፡ይጥሉ፡ዘንድ፡ልበ፡
ቅኖችንም፡ይወጉ፡ዘንድ፤ሰይፋቸው፡ወደ፡ልባቸው፡ይግባ፥ቀስታቸውም፡ይሰበር።
ለጻድቅ፡ያለው፡ጥቂት፡ከብዙ፡ከኀጢአተኛዎች፡ሀብት፡ይበልጣል።የኃጥኣን፡ክንድ፡ትሰበራለችና፤እግዚአብሔር፡ግን፡ጻድቃንን፡ይደግፋቸዋል።የንጹሓንን፡መንገድ፡እግዚአብሔር፡ያውቃል፥ርስታቸውም፡ለዘለዓለም፡ነው፤በክፉ፡ዘመንም፡አያፍሩም፡በራብ፡ዘመንም፡ይጠግባሉ።ኃጥኣን፡ግን፡ይጠፋሉ፥የእግዚአብሔር፡ጠላቶች፡በከበሩና፡ከፍ፡ከፍ፡ባሉ፡ጊዜ፡እንደ፡ጢስ፡ይጠፋሉ።
ኀጢአተኛ፡ይበደራል፡አይከፍልምም፤ጻድቅ፡ግን፡ይራራል፡ይሰጣልም።ርሱን፡የሚባርኩት፡ምድርን፡ይወርሳሉና፤የሚረግሙት፡ግን፡ይጠፋሉ።የሰው፡አካኼድ፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ይጸናል፥መንገዱንም፡ይወዳ፟ል።
ቢወድቅም፡ለድንጋፄ አይጣልም፥እግዚአብሔር፡እጁን፡ይዞ፡ይደግፈዋልና።ጐለመስኹ፡አረጀኹም፤ጻድቅ፡ሲጣል፥ዘሩም፡እኽል፡ሲለምን፡አላየኹም።
ዅልጊዜ፡ይራራል፡ያበድርማል፥ዘሩም፡በበረከት፡ይኖራል።ከክፉ፡ሽሽ፥መልካምንም፡አድርግ፤ለዘለዓለምም፡ትኖራለኽ።
እግዚአብሔር፡ፍርዱን፡ይወዳ፟ልና፥ቅዱሳኑንም፡አይጥላቸውምና፤ለዘለዓለምም፡ይጠብቃቸዋል፡ለንጹሓንም፡
ይበቀልላቸዋል፤የኃጥኣን፡ዘር፡ግን፡ይጠፋል።
ጻድቃን፡ምድርን፡ይወርሳሉ፥በርሷም፡ለዘለዓለም፡ይኖራሉ።የጻድቅ፡አፍ፡ጥበብን፡ያስተምራል፥አንደበቱም፡ፍርድን፡ይናገራል።
የአምላኩ፡ሕግ፡በልቡ፡ውስጥ፡ነው፥በርምጃውም፡አይሰናከልም።
ኀጢአተኛ፡ጻድቁን፡ይመለከተዋል፥ሊገድለውም፡ይወዳ፟ል።እግዚአብሔር፡ግን፡በእጁ፡አይተወውም፥በተፋረደውም፡ጊዜ፡አያሸንፈውም።እግዚአብሔርን፡ደጅ፡ጥና፥መንገዱንም፡ጠብቅ፥ምድርንም፡ትወርስ፡ዘንድ፡ከፍ፡ከፍ፡ያደርግኻል፤ኀጢአተኛዎችም፡ሲጠፉ፡ታያለኽ።ኃጥኣን፡ከፍ፡ከፍ፡ብሎ፡እንደ፡ሊባኖስ፡ዝግባም፡ለምልሞ፡አየኹት።
ብመለስ፡ግን፡ዐጣኹት፤ፈለግኹት፡ቦታውንም፡አላገኘኹም።ቅንነትን፡ጠብቅ፥ጽድቅንም፡እይ፤ለሰላም፡ሰው፡ቅሬታ፡አለውና።በደለኛዎች፡በአንድነት፡ይጠፋሉ።የኀጢአተኛዎች፡ቅሬታ፡ይጠፋል።የጻድቃን፡መድኀኒታቸው፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ነው፤በመከራቸውም፡ጊዜ፡መጠጊያቸው፡ርሱ፡ነው።እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፥ያድናቸዋልም፥ከኀጢአተኛዎችም፡እጅ፡ያወጣቸዋል፥ያድናቸዋል፥በርሱ፡ታምነዋልና።

መዝሙር 36
3 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 18:36:03
3 views15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 07:27:23
‛‛በዚያም፡ ዘመን፡ ስለሕዝብኽ፡ ልጆች፡ የሚቆመው፡ ታላቁ፡ አለቃ፡ ሚካኤል፡ ይነሣል፤ ሕዝብም፡ ከኾነ፡ ዠምሮ፡ እስከዚያ፡ ዘመን፡ ድረስ፡ እንደ፡ ርሱ፡ ያለ፡ ያልኾነ፡ የመከራ፡ ዘመን፡ ይኾናል፤ በዚያም፡ ዘመን፡ በመጽሐፉ፡ ተጽፎ፡ የተገኘው፡ ሕዝብኽ፡ ዅሉ፡ እያንዳንዱ፡ ይድናል። በምድርም፡ ትቢያ፡ ውስጥ፡ ካንቀላፉቱ፡ ብዙዎች፡ ይነቃሉ፤ እኩሌቶቹ፡ ወደዘለዓለም፡ ሕይወት፥ እኩሌቶቹም፡ ወደ፡ ዕፍረትና፡ ወደዘለዓለም፡ ጕስቍልና። ጥበበኛዎቹም፡ እንደሰማይ፡ ጸዳል፥ ብዙ፡ ሰዎችንም፡ ወደ፡ ጽድቅ፡ የሚመልሱ፡ እንደ፡ ከዋክብት፡ ለዘለዓለም፡ ይደምቃሉ። ዳንኤል፡ ሆይ፥ አንተ፡ ግን፡ እስከ፡ ፍጻሜ፡ ዘመን፡ ድረስ፡ ቃሉን፡ ዝጋ፥ መጽሐፉንም፡ ዐትም፤ ብዙ፡ ሰዎች፡ ይመረምራሉ፥ ዕውቀትም፡ ይበዛል።’’

ትንቢተ ዳንኤል 12፥1—4
1 view04:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:02:21
3 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:02:21 አለቃ አያሌው ፦ እንደታሰረ ነው፡፡ ማንም አይፈታውም ቤተ ክርስቲያን እስከ አልተመለሰች ድረስ አይፈታም፡፡ ቤተ ክርስቲያን ተመልሳ ሲኖዶሱ የክርስቶስ ተጠሪ ከአልኾነ ምንጊዜም አይፈታም፡፡ የክርስቶስ የኾኑ ጳጳሳት ከሌሉ አሁን የአሉትም አይኾኑም ይኼንን ይወቁት፡፡ ለዚህ መድኃኒቱ ምእመናን ተሰብስበው ካህናቱንም አስገድደው”እሺ” ያሏቸውን በውድ”እምቢ” ያሏቸውን በግድ ለይተው አስወጥተው አባ ጳውሎስን አውግዘው ራሳቸውን አስተካክለው ከአልቆሙ በስተቀር ቤተ ክርስቲያን አሁን የለችም፡፡

እንዲህ በመላ ደግሞ አትመለስም፡፡ አባ ጳውሎስ ድንገት ቢሞቱ እኔም ድንገት ብሞት ያሉ ጳጳሳት ያሉት ካህናት ተመልሰው ተክተው የሚሠሩት ምንም ዋጋ የለውም፡፡ ፍርድ ሳይፈረድ አጥፊውና አልሚው ሳይለይ በምንም ዓይነት የሚደረገው ነገር ኸሉ ዋጋ የለ ውም፡፡ ለዚህ ነው ዓመት ሙሉ የጮኹት፡፡ ነገሩ ጥብቅና ከባድ ስለኾነ ነው፡፡ ሰውማ ቢኖረን እኮ በኹለትና በሦስት ስንኳ ይኾን ነበር፡፡

ሌላው ቀርቶ አባ ጳውሎስ ቢሞቱ ስንኳ ሌላ ጳጳስ ለመ ሾም እነዚኽ በዚያ ሕግ ላይ የፈረሙ ኹሉ የመሾም መብት ስለ ሌላቸው የአልፈረመ ጳጳስ ሦስት ከሌለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ሌላ ፓትር ያርክ መሾም አትችልም፡፡ ይኼንን ይወቁ፡፡ እንደገና ወደ ግብፅ መሔድ ነው፡፡ የእኔ አቤቱታ ሥርዓቱ ይስተካከል፡፡ ወደ ነበረበት ይመለስ ነው፡፡ ከተመለሰ ተመልሷል፡፡ ውግዘት የለም፡፡ ከአል ተመለሰ ግን ውግዘቱን ማንም ሊፈታው አይችልም፡፡ እንዴ!! ክር አይደል፡፡ ሽቦ አይደል ገመድ አይደል፡፡

የዲማዉ ጊወርጊስ የእምነቱ ገበሬ
ሊቀ ሊቃዉት አለቃ አያሌዉ
3 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:02:20 ራሳቸው (አባ ጳውሎስ) በጉባኤ እንደተናገሩት በገጠር ያሉ ድኾች አብያተ ክርስቲያናት የሚረዱበት አጥተው በሙታን ሴቶች ቀሚስ እየተቀደሰ ይኽን የሚሰሙ ምእመናንን ናቸው ዝም ብለው የሚያጨበጭቡ፡፡ ደግሞስ በቤተ ክርስቲያን ላይ ደም እየፈሰሰ ደም አፍሳሽ ቅዱስ ነው እንዴ? ደም አፍሳሽ ቅዱስ ነው? ይኼንን የአዲስ አበባ ሕዝብ ዐይኑ አይቶ የለምን? ሰምቶስ የለምን? ከዚኽ ነው ቅዳሴ የሚያገኘው?

ጥያቄ ፦ ሰው በቤተ ክርስቲያን ተገኝቶ አስቀድሶ ሥጋ ወደሙን ለመ ቀበል ለምን ተከለከለ?

አለቃ አያሌው ፦ እኔ አልከለከልኩም፡፡ የሚያቀብላችሁ ከአገኛችሁ ቅዳሴ የሚቀድስ ቄስ ጳጳስ ከአላችሁ እኔ አልከለከልኩም የላችሁም እንጂ፡፡

ጥያቄ ፦ የጌታ ሥጋ ወደሙን በካህናት አባቶች እጅ አትቀበሉ፡፡ የፓትር ያርኩ ተባባሪዎች ናቸው ለምን ተባለ?

አለቃ አያሌው ፦ ሥልጣነ ክህነት የላቸውም እኮ ነው እያልኩ ያለሁት፡፡ የፓትርያርኩ ተባባሪ የኾነ ኹሉ ሥልጣነ ተክህኖ የለውም፡፡ ምክንያቱም ሚያዝያ 3ዐ ቀን 1988 ዓ. ም. የወጣው ሕግ ሲኖዶሱ የፈረ መብት ሕግ እስከዛሬ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የምትሠራባቸውን ደንቦችንና ሕጐችን አሻሻሎ የሚመራና ለሲኖዶሱ ተጠሪ የነበረው ፓትርያርክ በመንፈስ ቅዱስ ፈንታ መሪ እንዲኾን አመራር ሰጪ እንዲኾን ፈቅዶ ቤተ ክርስቲያንንና አባላቷን የፓትርያርክ አባ ጳውሎስ ተጠሪ እንዲኾኑ አድርጓል፡፡

ከዚያ ጊዜ ወዲህ ጳጳሳትም ቀሳውስትም ራሳቸውን ሽረው የአባ ጳውሎስ ፍጡራን ስለኾኑ አባ ጳውሎስ ደግሞ ሥልጣነ ክህነት የመስጠት መብት ስለሌላቸው አሁን ዛሬ የሚቀድሱ የሚያወድሱ ካህናት ቄሶችም ጳጳሳትም የሉንም፡፡ ስለዚህ ከአሏችሁ አልቃወምም፡፡

ጥያቄ ፦ የእናንተ የሃይማኖት አባቶች ፍቅር መጥፋት ለመናፍቃን በር አይከፍትም ወይ? ዛሬ ዛሬ መናፍቃን”…በእነርሱ በኩል ፍቅር ጠፍቷል፡፡ እንደምታይዋቸው አንዱ አንዱን እየወገዘ ነው ያሉት” እያሉ ይሣለቁብናል፡፡ በእርስዎ በኩል ይኼን እንዴት ያዩታል?

አለቃ አያሌው ፦ ፍቅር እኮ አልጠፋም፡፡ ግን በእግዚአ ብሔር ቀልድ የለም፡፡ በእግዚአብሔር አድማ የለም፡፡ አድማ እኮ ነው፡፡ ምን አጣላን? ምንም ፀብ የለንም፡፡

ጥያቄ ፦ ይኸ ውግዘት የተላለፈው ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው? ወይስ ለአዲስ አበባ ከተማ ብቻ?

አለቃ አያሌው ፦ ለኢትዮጵያውያን በሙሉ ነው፡፡ በዓለም ላሉ ኢትዮጵያውያን በሙሉ፡፡

ጥያቄ ፦ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ መስቀልን በካህን አባቶች እጅ አትሳለሙ ለምን ተባለ?

አለቃ አያሌው ፦ መስቀል ብቻውን መባረኪያ አይኾንም፡፡ ታዲያ ለምን አንጥረኛው አይባርክበትም፡፡ ነጋዴው ለምን አይባርክበትም? ለምንድን ነው? መስቀሉ ዕኩል ነው፡፡ የሠራው አንጥረኛው ነው፡፡ የሸጠውም ነጋዴው ነው፡፡ ቄሱ ብቻ ስለያዘው መባረኪያ የሚኾነው ለምንድን ነው? የመባረክ ሥልጣን ያለው ቄሱ ብቻ ስለኾነ ነው፡፡ ያ ቄስ ደግሞ እግዚአብሔርን ከካደ በረከት የለውም ማለት ነው፡፡ በትንቢተ ሚልኪያስ”እናንተ ካህናት ስሜን አርክሳችኋልና እኔም በረከቴን ከእናንተ ወስጃለሁ፡፡” ይላል፡፡

ጥያቄ ፦ ውግዘት ከተላለፈ ወዲህ ብዙ እናት አባቶች እኀት ወንድሞች ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩ አሉ፡፡ እነዚኽ ሰዎች እንደተወገዙ ነው የሞቱት ወይስ ተፈትተው? ይኼንንም ቢያብራሩልን?

አለቃ አያሌው ፦ ትእዛዜን አክብረው ከኾነ ተፈትተዋል፡፡ ከአላከበሩ ግን እስረኞች ናቸው፡፡

ጥያቄ ይኼን ውግዘት በግል ጋዜጣ ከማስተላለፍዎ በፊት ለምን በእየቤተ ክርስቲያኑ ተገኝተው ለምእመኑ አላስተላለፉም?

አለቃ አያሌው ፦ እኔማ ታግጃለሁ፡፡ ስለታገድኩ እኮ ነው በግል ጋዜጣ ለመተንፈስ የበቃሁት እንጂ ይኽንንማ ዕድል ከአገኘኹ ለምን በጋዜጣ እናገራለሁ፡፡ በመድረክ ላይ ነበር የምናገረው፡፡ ጥር 24 ቀን 1988 ዓ.ም. በጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፉ መበላሸቱን ተናግሬአለሁ፡፡ ከዚያ ቀደም ብሎም አንድ ዓመት ሙሉ ሲኖዶሱ እንዲያየው በደብዳቤም በቃልም ተናግሬያለሁ እምቢ ስላሉ እንደጌታ ቃል ነው ያወገዝኩኝ፡፡ ከዚያ ውጪ አልሔ ድኹም፡፡ «መጀመሪያ ጠይቅ፡፡”እምቢ” ሲሉ ለቤተ ክርስቲያን ንገር ከዚያ በኋላ አውግዝ…» ነው ያለ፡፡ እንዳዘዘኝ ነው ያደረግኹት፡፡

ጥያቄ ፦ ይኸ ውግዘት እስከመቼ ነው የሚቆየው? ለምን?

አለቃ አያሌው ፦ እስከተፈታ ድረስ፡፡ ነገሩ ውሳኔ ከአላገኘ ያው ነው፡፡ አርዮስ ተፈቷልን? መቅዶንዮስስ ተፈቷልን? ንስጥሮስስ ተፈቷልን? አሁንም በዚህ ዓለም ብቻ አይደለም፡፡ በውዲያኛውም ዓለም ውጉዛን እሱራን ናቸው፡፡ በሥልጣነ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እሱራን ውጉዛን ይኹኑ፡፡

ጥያቄ ፦ አባ ጰውሎስ”የግል ጋዜጣ ገዝታችሁ አታንብቡ” ብለው አውግዘዋል፡፡ የእርስዎ ውግዘት የተላለፈው ደግሞ በግል ጋዜጣ ነው ይኼ ሊጋጭ አይችልም ወይ?

አለቃ አያሌው ፦ ምን ያጋጨዋል? እሳቸውም እንደ ዐመፁ ናቸው፡፡ እኔም ከእግዚአብሔር ጋራ እንደቆምኩ ነኝ፡፡ ምን ይጋጫል? መጀመሪያ ጸባቸው የማይኾን ኾኖ ወጡ፡፡ ከወጡ በኋላ የሚያደርጉት ነገር የላቸውም፡፡ እውነት ከኾነ ውግዘቱን ለማ ገድ ከመሞከር ወይም”የግል ጋዜጣ አታንብቡ” ብሎ ከማስገደድ የሊ ቃውንት ጉባኤን ከማገድ ሲኖዶሱን ከማፍረስ ይልቅ የሊቃውንት ጉባ ኤውም እንዳለ ሲኖዶሱም እንዳለ እኔን አቅርበው መጠየቅ ነበረባቸው እውነቱ ይኼ ነው፡፡

ጥያቄ ፦ ካህናት ለምን ይወገዛሉ? አጥፊው ሌላ ነው፡፡ ደግሞም ከሥራ ቢፈናቀሉ ችግር ላይ ይወድቃሉ፡፡

አለቃ አያሌው ፦ከቤተ ክህነት የሚያገኙት ገንዘብ የለም ለልብሳችን ለምግባችን ብለው ሊመካኙ አይችሉም፡፡ ደግሞ ከዚህ ነፃ ካልወጡ ካህናት አይደሉም፡፡ ጌታ ራሱ አንድ ባሪያ ለኹለት ጌታ መገዛት እንደማይችል እናንተም «…ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ ልት ገዙ አትችሉም…» ነው ያለው፡፡ ይኽንን ሲያብራራ ነገሩን በዚህ ብቻ ሳይወስን ምክንያቶቹ ገንዘብ ፈለጋ የሚሰዱን ልብስና ምግብ ስለኾኑ «ምን እንበላለን? ምን እንለብሳለን? ብላችሁ አታመካኙ፡፡ ወፎችን አበቦችን እዩ» ብሎ በገንዘብ ምክንያት ከእሱ እንዳንለይ አዝዟል ከዚህ በላይ ከአልኼድን ስንኳን ካህንነቱ ምእመንነቱም አይኾንም፡፡

ካህናትማ ከዚህ በላይ መሔድ አለብን፡፡ አንድ በጐቹን ለመጠበቅ የተሰየመ እረኛ ዐቅሙ እስከ ፈቀደ ድረስ ከአራዊት ጋራ ተከላክሎ በጐቹን ማዳን አለበት፡፡ እሱ መሞት አለበት እንጂ እነሱን አሳ ልፎ መስጠት የለበትም፡፡ ስንኳን ለጥቅም ብሎ አሳልፎ ሊሰጣቸው ስለሕይወቱም አሳልፎ ሊሰጥላቸው ነው የታዘዘው፡፡ ጌታ ራሱ”ስለበጐቼ ራሴን እለውጣለሁ” ነው ያለው፡፡ ይኽንንም ለሐዋርያቱ ለካ ህናቱ ሊያስተላልፍ”ራሱን ለወንድሙ ለውጥ አድርጐ ከመስጠት የበለጠ ፍቅር ምን አለ?” ብሎ ነው እንድንቀበለው የአዘዘን፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሰዎች የኾንን ኹሉ አስተማሪዎች የኾንን ኹሉ ስንኳን በምግብ በልብስ ልናመካኝ ይቅርና ስለምእመናን ራሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ተጠይቀናል፡፡

ጥያቄ ፦ ከኹለት አንዳችሁ ከዚህ ዓለም በሞት ብትለዩ ወግዘቱ እንደታሠረ ይቀራልን? ወይስ ይፈታል?
2 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 20:02:20 ውግዘት ማለት ምን ማለት ነው?

አለቃ አያሌው ፦ በቤተ ክርስቲያን ሥርዐት ውስጥ አንድ ሰው ከቤተ ክርስቲያን ሥርዐት ውጪ ከኼደ ስንኳን መሪ ኾኖ በምእመንነት ያለም ቢኾን ሕጉን ከተላለፈ ይወገዛል፡፡ ሃይማኖትን የተላለፈ ብቻ አይደለም፡፡ ሥርዓትንም ቢኾን የተላለፈ ያው ነው፡፡ስንኳን ይኽንን ያህል የቤተ ክርስቲያንን ሥርዐት የአፋለሰ ቀርቶ አንዱ ከአንዱ ጋራ ተጣልቶ”አልታረቅም” ቢል እንኳን ይወገዛል፡፡

ጌታችን”አንድ ሰው ቢበድል መጀመሪያ ብቻህን ኹለተኛ ሰው ጨምረህ ንገረው፡፡ እምቢ ቢል ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እምቢ ቢል እንደአረመኔ እንደቀራጭ ይኹን ነው” ያለ፡፡ ይኼ ውግዘት ነው፡፡ ከዚያ አያይዞ ሲናገርም”በምድር ያሰራችሁት በሰማይ የታሰረ ይኾናል፡፡ በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይኾናል” ብሏል፡፡ ይኽ የቤተ ክርስቲያን መሣሪያ ውግዘት ነው፡፡

ጥያቄ ፦ አንድ ሰው ተወገዘ ሲባል ምን ምን ሲሠራ ነው?

አለቃ አያሌው ፦ ከቤተ ክርስቲያን ሕግ ውጪ የኾኑ ነገሮችን ኹሉ ከአደረገ ይወገዛል፡፡ ትምህርተ ሃይማኖትን ከአፋለሰ ሥር ዐትን ከጣሰ ሕግን ከአፈረሰ ሃይማኖት ከአጠፋ በሰውም በእግዚአብሔርም ላይ በደል ከአደረሰና ተመክሮ ተነግሮ እምቢ ካለ ይወገዛል፡፡ ማውገዝ ማለት መለየት ማለት ነው፡፡

ስንኳን በመንፈሳዊ ሕይወት በሥጋዊ ሕይወትም ድሮ አባቶች እንዲህ ያደርጉ ነበር፡፡ እንዲህ ባይኾን የኒቅያ፣ የቊስጥን ጥንያ የኤፌሶን ጉባኤያት አያስፈልጉም ነበር፡፡ እነአርዮስ እነ መቅዶ ንዮስ እነንስጥሮስ ተወግዘው አይለዩም ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ለዕብ ራውያን በጻፈው መልዕክቱ”በሙሴ ሕግ የአጠፋ ሰው በኹለት በሦስት ሰው ፊት ከተወቀሰ ይቀጣል” ይላል፡፡ ግን በወልደ እግዚአብሔር ደም ቃል ኪዳን የተጋባና የተቀበለውን ቅድስና የአረከሰ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የአዋረደ ቢኖር እንዴት አይቀጣም?

አሁንም ቅዱስ ጳውሎስ”እኔ በሥጋ ከእናንተ ጋራ ባልኖር በመንፈሴ ከእናንተ ጋራ ነኝ፡፡ አንዲህ ያለውን ሰው ዝም ብላችሁ መመልከት አይገባችሁም፡፡ ስለዚህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተሰብስባችሁ አውግዙት ለዩት፡፡ ለሰይጣንም ሰጡት” ነው የሚል፡፡ እኔም ያወገዝኩት ከላይ በተጠቀሰው መሠረት ነው፡፡ 1 ቆሮ = 5፤5፡፡

ጥያቄ ፦ በፖትርያርኩና በእርስዎ መኻል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ለምን አልተቻለም?

አለቃ አያሌው ፦ አይቻልም፡፡ አልተቻለምም፡፡ ምክንያቱም እሳቸው (አባ ጳውሎስ) ሲመለሱ ነው የሚፈታ፡፡ ወይም ከመኻላችን ዳኛ ሲኖር ነው የሚፈታ፡፡ በመኻላችን ጉባኤ የሚጠራ ንጉሥ የለም ዛሬ፡፡ አርዮስ ሲወገዝ የኒቅያን ጉባኤ ቈስጠንጢኖስ፤ መቅዶንዮስ ሲወገዝ አርቃድዮስ፤ ንስጥሮስ ሲወገዝ ቴዎዶስዮስ የተባሉ ነገሥታት ነበሩ፡፡ በኢትዮጵያም ነገሥታቱ በነበሩበት ጊዜ በእየጊዜው የተደጋገመ ጉባኤ ተደርጓል፡፡

በዓፄ ፋሲል ጊዜ በካቶሊክና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማንያን መኻል ጉባኤ ተደርጐ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አፈ ጉባዔ እጨጌ በትረ ጊዮርጊስ ስለረቱ ካቶሊካውያኑ መረታታቸውን አምነው ተቀብለው ከአገር እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል በዓፄ ዮሐንስ ዘመነ መንግሥት በቦሩ ሜዳ ጸጐችና ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት እንዲከራከሩ ተደርጐ ጸጐች ስለተረቱ ተፈርዶባቸው ተቀጥተዋል፡፡

ንጉሥ ቢኖር ይኽንን ጉባኤ ጠርቶ ሊፈታው ይችል ነበር፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የበላይ ጠባቂ ንጉሠ ነገሥቱ ነበርና፡፡ ዛሬ ንጉሥ ንገሥት የለም፡፡ ያለው መንግሥት”በሃይማኖት ጉዳይ አያ ገባኝም” አለ፡፡ ይኽንን ምክንያት አድርገው ፖትርያርኩ አባ ጳውሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን ረገጡ፡፡ ክብሯንም አጐደፉ፡፡

ጥያቄ ፦ ፖትርያርኩ ቢያጠፋ ወይም ሃይማኖት ቢያፋልሱ ራሳቸው በሠሩት ሥራ ይቀጣሉ እንጂ ካህናት አባቶች ተባባሪዎች ናቸው ተብለው ለምን ይወገዛሉ?

አለቃ አያሌው ፦ ፓትርያርኩ ሲያጠፋ የምትሾምም የምትሽርም ቤተ ክርስቲያን ናት፡፡ ፓትርያርኩ እኮ በጦር ጕልበት አይደለም የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን መንበር የወረሱት፡፡ በልዩ ሥልጣናቸውም አይደለም፡፡ ልዩ መብትም የላቸውም፡፡ የወራሽነት መብትም የላቸውም፡፡ ተመርጠው ነው የተሾሙት፡፡ ሲሾሙም ደግሞ ምለው ነው፡፡ የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓትና እምነት ሊጠብቁ ነው፡፡ ከአልጠበቁ መሻር አለባቸው፡፡ ከአልሻሯቸው ይወቀሳሉ ይከሰሳሉ፡፡ አብረዋቸው ይሻራሉ፡፡

ጥያቄ ፦ቤተ ክርስቲያናችን ኹል ጊዜ ስለ ፍቅር እያስተማረች በእርስዎና በፖትርያርኩ መኻል ለምን ፍቅር ጠፋ?

አለቃ አያሌው ፦ በእኔና በእርሳቸው መኻል አይደለም ፍቅር የጠፋው፡፡ በቤተ ክርስቲያንና በእሳቸው መኻል ነው፡፡ እኔና እርሳቸው አሁንም አልተጣላንም፡፡ አልበደሉኝም አልበደልኳቸውም የግል ቂም የለኝም፡፡ ፀባችን በቤተ ክርስቲያን ምክንያት ነው፡፡ በእግዚአብሔር ላይ ደግሞ መታረቅም መተባበርም አይቻልም፡፡ ሄሮድስና ጲላጦስ ሞክረውት ነበረ፡፡ አልተደረገም፡፡ በእግዚአብሔር ላይ መዋዋል በእግዚአብሔር ላይ ወዳጅነት መፍጠር አይቻልም፡፡

ይኼማ ቢኾን ኖሮ ጌታ”በሰው ፊት ያመነብኝን በሰማይ አባቴ ፊት አምንበታለሁ፡፡ በሰው ፊት የአፈረብኝን በሰማይ አባቴ ፊት አፍርበታለሁ፡፡” ለምን ይል ነበረ? ጌታ”እኔ ሰይፍን እንጂ ሰላምን አላመጣሁም፡፡ አባትን ከልጁ እናትን ከልጇ ቤተሰብእን ከቤተሰብኡ ልለያይ ነው የመጣሁ” ነው ያለ፡፡ ታዲያ ይኽ ባይኾን ኖሮ በዓለም ምን ፀብ ይኖር ነበረ? በዓለም ምን ሰማዕታት ይገኙ ነበረ? ለምን ይሞቱ ነበር? ለምን ደማቸውን ያፈሱ ነበር? በእግዚአብሔር ላይ ውለታ መዋዋልና ፍቅር መፍጠር አይቻልም፡፡


ጥያቄ ፦ ምእመኑስ ለምን በቤተ ክርስቲያን ተገኝቶ እንዳያስቀድስ ታገደ?

አለቃ አያሌው ፦ እስኪ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ዐሥርን እዩት፡፡”…በጐቼ ቃሌን ያውቃሉ፡፡ እኔ በስማቸው እጠራቸዋለሁ፡፡ ይከተሉኛል፡፡ ሌላውን ግን አያውቁትም፡፡ ስለዚህ ቃሉን አይሰሙትም፡፡ አይከተሉትምም” ነው ያለ፡፡ ከክርስቶስ ውጪ የኾነ እረኛ የለንም፡፡ ከክርስቶስ ውጪ የኾነ ፖትርያርክ የለንም፡፡ ከሌለን ደግሞ ምእመናንን ሊሰሙት ሊቀበሉትና ሊከተሉት አይገባም ማንን ነው የሚያስቀድሱት? ዲያብሎስ ይቀድሳል እንዴ? አይቀድስም እኮ፡፡ ይኽንን አታውቁም? ቅዱሳን መላዕክት ናቸው እንጂ የሚቀድሱ ዲያብሎስ እኮ አይቀድስም፡፡”ቅዱስ” ብሎ የእግዚአብሔርን ቃል አይጠራም፡፡

እነዚህ እግዚአብሔርን የካዱ መቀደስ አይችሉም፡፡ በእነርሱ ድምፅ ማስቀደስ አይቻልም፡፡ የቅዳሴ ተባባሪ መኾንም አንችልም፡፡

ስለዚህ ምእመናንን ከእዚኽ መታቀብ አለባቸው፡፡ ምእመናን ናቸው ወንጀለኞች እንግዲያውስ፡፡ አንደኛ ከብበው እያጨበጨቡ ኹለተኛ ሲወጡ ሲገቡ እጅ እያነሡ፡፡ ቁጭ ብድግ እያሉ፡፡ ሦስተኛ ገንዘባቸውን እየሰበሰቡ እየሰጡ ቤተ ክርስቲያንን ለጣዖት አምልኮ ማጠናከሪያ ያደረጓት ምእመናን ራሳቸው ናቸው፡፡ ስምንት መቶ ሺ ብር የፈጀ መኪና የተገዛው በምእመናንን ገንዘብ ነው፡፡ ምዝበራ ነው፡፡ አንድ ሚሊዮን ተኩል የፈጀ ግብዣ የተጋበዘው ከቤተ ክርስቲያን በተፈጸመ ምዝበራ ነው፡፡ ምእመናን እጃቸውን ቢሰበስቡ የሰበካ ጉባኤ አደራውን ቢጠብቅ ኖሮ እንዲህ አይደረግም ነበር፡፡
3 views17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 07:18:53
«...መላው አገሬ የኢትዮጵያ ልጆች፣ የተዋህዶ እምነት ልጆች፣ የድንግል ልጆች፣ የገብርኤል የሚካኤል አንበሶች፣ የኡራኤል፣ የሩፋኤል አርበኞች፣ ባጠቃላይ ቅን የዋህ የሆንከው ኢትዮጵያዊ በሙሉ ፣ ባለህበት ፀንተህ ቁም ! ቅድስናህን ጠብቅ ! አትደንግጥ፣ አትፍራ እራስህን ለፈጣሪ ስጥ፣ ለታላቅ አገልግሎት እራስህን አዘጋጅ ! እስከዛሬ ከሰራኸው ጥፋት በምህረቱ ሽሮ በቸርነቱ ያሰራህን፣ የኢትዮጵያ አምላክ አስብ፣ አመስግን፡፡ ዝርዝር መመሪያዎችን በጥንቃቄ አንብብ፣ አስተውለህም አድርግ፡፡ እግዚአብሄር ለክብሩ መርጦሃልና እራስህን በቅድስናና በትህትና አንጽ፣ ከክፋትም ሁሉ ራቅ፡፡»

ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3 ገፅ 38 (ሙሉ pdf ገፅ 72) ላይ የተወሰደ!
2 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 07:18:53
የኃጢአተኛ ፉከራ አጭር መሆኑን
የዝንጉዎችም ደስታ ቅጽበት መሆኑን አታውቁምን?
ከፍታው ወደ ሰማይ ቢወጣ፥
ራሱም እስከ ደመና ቢደርስ፥
እንደ ፋንድያ ለዘላለም ይጠፋል፤
ያዩትም። ወዴት ነው? ይላሉ።

መጽሃፈ ኢዮብ 20፥5-7
2 views04:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ