Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-09-23 10:01:12
3.1K views07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 14:48:37
7.0K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 14:48:32
#NEW
6.6K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 10:07:19 የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት
=================

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፦ ጳጉሜን 5/2014 ዓ.ም ( ደማዩ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)

ለሁሉም የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ እና ለመላው የሀገራችን ህዝብ በሙሉ እንኳን ለ2015 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በዓሉ የሰላም፣የጤናና የደስታ እንዲሆን እየተመኘሁ ይህን የዘመን መለወጫ በዓል ስናከብር ለዘመናት ተጠብቀው የቆዩትን የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና ያለንን ለሌሎች የማካፈል መልካም እሴቶቻችንን በመተግበር በጦርነት የተጎዱና የተፈናቀሉ ወገኖቻችንን በማሰብና በመደገፍ እንድናሳልፍ ለማሳሰብ እወዳለሁ፡፡

በተጨማሪም አሁን ያለው የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታና የሰላም እጦት አሳሳቢ መሆኑን ተገንዝበን መለያየት ለጠላት ምቹ ሁኔታን ስለሚፈጥር ሁላችንም አንድ በመሆን የሀገራችንን ሰላም የምንመልስበት ዘመን እንዲሆንልን በመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ ስም ልባዊ ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡

ታፈረ መላኩ ዶ/ር
የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት

"የእውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ"

ከታች ያስቀመጥናቸው የዩኒቨርሲቲያችን ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር አድራሻዎቻችን ናቸው። ተራ በተራ ሊንኮቹን እየተጫናችሁ ትወዳጁን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን



ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

ዌብሳይት: www.dmu.edu.et

ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia

እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/
2.8K viewsedited  07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 10:07:14
2.4K views07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 09:12:14 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ #የ2014 ዓ.ም የስራ ዓመት መገባደድን #የ2015 ዓ.ም የስራ ዘመን መተካትን አስመልክቶ ውይይት ተካሄደ

==============

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፦ (ደማዩ ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)

እንደ ዩኒቨርሲቲ 2014 ዓ.ም እንዴት አለፈ? ምን ጥንካሬዎች ነበሩን? ምን እጥረቶች ነበሩ? በ2015 የስራ ዘመንስ ምን እናስባለን? በሚሉትና ሌሎችም ወሳኝ የውይይት ነጥቦች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

ይህ ውይይት በዩኒቨርሲቲያችን ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት እና በሊቀ ማርቆስ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ በጋራ ትብብር የተዘጋጀ ልዩ የምክክርና የውይይት መርሃ ግብር ሲሆን በውይይቱ ላይም ሞላልኝ ታምሩ (ዶ/ር ) የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ምክትል ፕሬዚደንት ፣ እሱባለው መኩ (ዶ/ር ) የፕሬዚደንት ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ድርቧ ደበበ (ዶ/ር ) የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ፣ መልካሙ በዛብህ (ዶ/ር ) የምርምርና ቴክኖሎጅ ሽግግር ዳይሬክተር ፣ አበበ በላይ (ዶ/ር ) የፕሮጀክት ቀረፃና ትብብር ዳይሬክተር ፣ ደምሳቸው ሽታሁን (ረ/ፕ ) የማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክተር እና እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍል ኃላፊዎች፣ መምህራንና ባለሙያዎች በውይይቱ ተሳታፊ ሆነዋል።

ይህ ልዩ ዝግጅት ሰኞ ምሽት ከ2:30 - 3:00 ባለው ጊዜ ውስጥ በአሚኮ ቴሌቪዥን የሊቀ ማርቆስ የቴሌቪሽን ፕሮግራም የሚቀርብ በመሆኑ መሉ ዝግጀቱን እንድትከታተሉ በአክብሮት እናሳሰባለን።

"የእውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ"

ከታች ያስቀመጥናቸው የዩኒቨርሲቲያችን ትክክለኛ የማህበራዊ ትስስር አድራሻዎቻችን ናቸው። ተራ በተራ ሊንኮቹን እየተጫናችሁ ትወዳጁን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን



ዩቲዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

ዌብሳይት: www.dmu.edu.et

ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia

እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/
2.7K viewsedited  06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 09:06:22
2.5K views06:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 06:14:48 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ በክረምት ሲሰጥ የነበረዉ STEM Outrich መርሃ ግብር ተጠናቀቀ

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፡- ጳጉሜ 2/በ2014 ዓ.ም ( ደ.ማ .ዩ. ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) የደብረ ማርቆስዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በ2014 ዓ.ም በክረምቱ ፕሮግራም (Summer Out rich) በተመረጡ ትምህርት አይነቶች ኬሚስትሪ፣ፊዚክስ ባዮሎጅ፣እንግሊዘኛ እና አይ.ሲቲ ከ13/10/2014 ዓ.ም አስከ 30/11/2014 ዓ.ም ሲሰጥ የነበረዉ የማጠናከሪያ ትምህርት የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተካሂዷል፡፡

የፕሮግራሙ አስተባባሪ ወ/ሮ ሳምራዊት ደሴ እንደገለጹት በክረምቱ መርሃ ግብር (Summer Out rich) ማጠናከሪያ ትምህርቱን የወሰዱት 44 ሴት፣ 163 ወንድ በአጠቃላይ 207 ተማሪዎች ሲሆኑ 14 መምህራን የማጠናከሪያ ትምህርቱን ሰጠዋል፡፡

የዚህ መርሃ ግብር ዓላማ ክህሎትና አቅም ያላቸዉን ተማሪዎች በመለየት ያላቸዉን እዉቀትና ክህሎት አዉጥተዉ የሚጠቀሙበትን መንገድ በማመቻቸት እራሳቸዉንና ሀገራቸዉን እንዲጠቅሙ ለማድረግ ያለመ ነዉ፡፡ ለዚህ ደግሞ ልምድ ያላቸዉን ሰዎች ከተለያዩ የሙያ መስኮች በማምጣት ያላቸዉን ልምድ እንዲያካፉሏቸዉ ተደርጓል፡፡

የዚህ ዓመት STEM Outrich መርሃ ግብር ተጠቃሚዎች የ10ኛና 11ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆኑ የፈጠራ ስራዎቻቸዉን እንዲያዳብሩ የታገዙት አንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን ጭምር ነዉ፡፡ በተጨማሪም በበጋዉ ፕሮግራም በአይ ሲቲ ስልጠና ሲሰጣቸዉ የነበሩት ልጆች እንዲካተቱ ተደርገዋል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይ የታቀፉት ተማሪዎች ከምስ/ጎጃም ዞን ከተለያዩ ወረዳዎች በሳይንስ ትምህርቶች ከፍተኛ ዉጤት ያላቸዉ ተማሪዎች ሲሆኑ የተሰጣቸዉ የማጠናከሪያ ትምህርት ተግባር ተኮር በመሆኑ የተለያዩ ፋብሪካዎችንና ወርክሾፖችን እንዲጎበኙ ተደርገዋል። በተሰጣቸዉ ተግባር ተኮር ትምህርት ክህሎቶቻቸውን በማዳበር የተለያዩ ድህረ ገጾችንና የፈጠራ ስራዎችን መስራት ችለዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለመርሃ ግብሩ ያደረገዉ እገዛ ለ207 ተማሪዎች ዶርም እና ምግብ የቻለ ሲሆን በተጨማሪ ለመምህራን፣ የቤተ ሙከራ ባለሙያዎች ፣ ለአስተባባሪዎች ደግሞ የበጀትና የቁሳቁስ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ለፕሮግራሙ መሳካት ከዩኒቨርስቲዉ በተጨማሪ STEM Synergy የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት የበጀት ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን ድጋፍ አድርጓል፡፡

በመጨረሻም በመርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፎ ለነበራቸዉ አካላት ሰርተፊኬት ከተሰጠ በኋላ ለተማሪዎች ምክርና የማጠቃለያ መልዕከት ተላልፎ የመርሃ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል፡፡
4.6K viewsedited  03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 06:14:28
4.4K views03:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 20:36:45 የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው ማህበረሰብ ኤፍ ኤም 97.7 ሬዲዮ ጣቢያ የተመሰረተበትን 6ኛ አመት ክብረ በዓል አከበረ
=================
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ ነሐሴ 28/2014 ዓ.ም (ደ.ማ.ዩ. ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) "የጥበብና_ማህበረሰብ_ድምፅ" በሚል መሪ ቃል የሚመራው የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው ማህበረሰብ ኤፍ ኤም 97.7 ሬዲዮ ጣቢያ ጥሪ የተደረገላቸው የፌደራል፣ የክልል ፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ ከፍተኛ ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች እንዲሁም ሬዲዮ ጣቢያው ተደራሽ ከሆነባቸው አካባቢዎች የተጋበዙ የሀይማኖት አባቶች፣ ወጣቶችና ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ከፍሎች በተገኙበት 6ኛ አመት የምስረታ ክብረ በዓሉን በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሐዲስ ዓለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ አከበረ።

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና የአካባቢው ማህበረሰብ ኤፍ ኤም 97.7 ሬዲዮ ጣቢያ የቦርድ ሰብሳቢና የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚደንት ዶር. ታፈረ መላኩ በመግቢያ ንግግራቸው ይህ የማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ በሌሎች ዋና ዋና የመገናኛ አውታሮች ሽፋን የማይሰጣቸውና ትኩረት የተነፈጉ የማህበረሰብ ጉዳዮችን ሽፋን በመስጠት በጉልህ የሚጠቀስ ሬዲዮ መሆኑን ጠቅሰው አሁን እያከናወነ ካለው ይበልጥ ለማህበረሰባችን ተደራሽ ለማድረግ ብዙ ስራዎች እንደሚጠበቁ ገልፀዋል።

በሌላ በኩል የሬዲዮ ጣቢያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ሞላ በበኩላቸው የሬዲዮ ጣቢያውን አጠቃላይ የስራ ክንውን አጭር ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሪፖርታቸውም ሬዲዮው ተመርቆ ስራ የጀመረው ሰኔ 23 ቀን 2008 ዓ.ም ሲሆን በወቅቱም በ 1 ዳይሬክተር ፣ በ 1 የይዘት ማናጀር፣ በ 5 ሪፖርተሮች እና በ 1 የቴክኒክ ባለሙያ እንዲሁም በ 1 ድጋፍ ሰጭ ቋሚ ቅጥር ሰራተኞች ሰራ መጀመሩን ገልፀዋል።

የሬዲዮ ጣቢያው ተደራሽነቱን ለማስፋትና የፕሮግራሞቹንም ጥራት ለማስጠበቅ ከሰው ሀይል አንፃር አሁን ላይ 15 ሪፖርተሮች፣ 3 ኤዲተሮች ፣ 4 የቴክኒክ ባለሙያዎች፣ 1 የድጋፍ ሰጭ ሰራተኛ እና 1 ስራ አስኪያጅ በአጠቃላይ 24 ቋሚ ቅጥር ሰራተኞች እና 10 የበጎ ፈቃድ አገልጋዮች ያሉ ሲሆን የአየር ስዓታቸውንም በፊት ከነበረው በቀን የ6 ስዓታት የአር ጊዜ ወደ 11 ስዓት ከፍ ማድረጋቸውን ዳይሬክተሯ አክለው ገልፀዋል።
የስርጭት አድማስ ከማስፋት አንፃርም ከባለ 1 ኪሎ ዋት ወደ ባለ 2 ኪሎ ዋት ለማሳደግ በሂደት ላይ እንደሚገኙም ተገልጿል።

በቀረበው የስራ ክንውን ሪፖርት ላይ ከታዳሚዎች ሀሳብና አሰተያየት የተሰነዘሩ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄዎችና ሀሳብችም ተገቢ ምላሽና ማብራሪያዎችም ተሰጥተዋል።

በመጨረሻም ለሬዲዮ ጣቢያው ስራ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ ልዩ ልዩ አካላት የእውቅናና ምስጋና ስነ ስርዓት ተደርጓል።
1.3K viewsedited  17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ