Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 27

2022-10-04 21:32:37 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለተለያዩ ትምህርት ክፍሎች የመፅሐፍ ስጦታ ተበረከተላቸው
==============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 24/2015 ዓ/ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) አቶ በሃይሉ ሽፈራው ይባላሉ ፤ በሀገረ በአሜሪካ የሶስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ሲሆን 250 መፅሐፍትን በወንድማቸው በአቶ ሶሎሞን ሺፈራው አማካኝነት ለዩኒቨርሲቲያችን የማህበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ አስረክበዋል።

በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የማህበራዊ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አማረ ሰውነትን ጨምሮ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን ይህ የመፅሐፍ ስጦታ እንዲገኝ ያስተባበሩት ደግሞ በዩኒቨርሲቲያችን የጋዜጠኝነትና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህር ዶ/ር ሃይማኖት ጌታቸው መሆናቸው ተገልጿል።

የተበረከቱት ሐፅሐፍትም በተለይም ለአማርኛ፣ ለጋዜጠኝነትና ተግባቦት ፣ ለቲያትር ጥበባት እና ለፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት ክፍሎች ማጣቀሻነት እንደሚያገለግሉ ተነግሯል።

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!
382 viewsedited  18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-04 21:32:29
389 views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 08:21:39
#NEW
2.9K views05:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 21:03:56
#ቡሬ_ካምፓስ እንዲፈተኑ የተመደቡ ወረዳዎችና ት/ቤቶች ዝርዝር
3.8K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 19:35:35
4.0K views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 19:35:02 በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመስከረም 30 ጀምሮ የሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የተፈታኞች መብትና ግዴታዎች
--------------
#የተፈታኝ_መብቶች፡
➭ ከፈተና ጥያቄ ውጪ ማንኛውንም ያልተረዳውን ነገር ጠይቆ የመረዳት መብት አላቸው።
➭ በየኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ምግብ፣ የህክምና አገልግሎት፣ የማደሪያ ክፍል፣ ፍራሽና ትራስ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ያለውን የቤተ መጽሐፍት፣ የመጸዳጃ ቤቶች፣ የሻወር፣ የካፍቴሪያዎች፣ የሚኒ ሱፐር ማርኬቶች፣ የተለያዩ ሱቆች፣ የመናፈሻና መዝናኛ አገልግሎቶችን የመጠቀም መብት አላቸው።
➭ የኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ የጋራ የደህንነት ጥበቃ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ በፈተና ሰዓት መፈተኛ ክፍል ገብቶ ብርሃናማ የመፈተኛ ቦታ፣ ወንበር፣ መጻፊያ ጠረጴዛ የማግኘት መብት አላቸው።
➭ ፈተና ከመጀመሩ አንድ ቀን ቀድሞ ስለፈተናው ገለጻ (ኦሬንቴሽን) የማግኘት መብት አላቸው።
#የተፈታኝ_ግዴታዎች፡
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት #ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን/ዕቃዎችን መያዝ የለበትም።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት።
➤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት።
➤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት።
#ለተፈታኞች_የተፈቀዱ_ነገሮች፦
➣ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማር እና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበሩ ማስተወሻ ደብተር ፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት
➣ እንደ አስፈላጊነቱ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንዱች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)
 ገንዘብ (ብር)
➣ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ
➣ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)
#ለተፈታኞች_የተከለከሉ_ነገሮች፦
⮕ ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውንም ዓይነት ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው።
⮕ ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ /ቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይ-ፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፕዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ጃኬት እና ሌሎች ማንኛቸውም ፎቶ፣ ምስል እና ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም አደንዛዥ እጾች (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሓኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት፣ ህክምና መስጫ መርፌ) መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር፣ አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡ (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀር)
⮕ ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው፡፡ ⮕ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡
⮕ በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
⮕ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ መሆኑን እያሳስብን በተጨማሪም ትምህርት ሚኒስቴር በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢና ጤና ሳይንስ ካምፓስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና እንዲወስዱ የተመደቡልንን ወረዳዎችና ትምህርት ቤቶችንም ከታች አስቀምጠናል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
3.8K views16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-01 19:34:20
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር #የ12ኛ_ክፍል ፈተና የሚሰጥበትን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጓል!
3.5K views16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 10:17:30 የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህራን፣ ሰራተኞችና ተማሪዎች በግፍ ለተገደለች እናት ልጆች ድጋፍ አደረጉ
===============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ መስከረም 20/2015 ዓ.ም (የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) በደብረ ማርቆስ ከተማ ቀበሌ 05 ልዩ ቦታው ግሪን ፓርክ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በቅርቡ አንድ ግለሰብ የ11 ልጆቹን እናት በአሰቃቂ ሁኔታ እንደገደለ ልጆቹንም ያለአሳዳጊና ተንከባካቢ እንዳስቀራቸው ይታወሳል።

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህራንናሰራተኞች እንዲሁም ተማሪዎች ለሟች ልጆች የምስራቅ ጎጃም ዞንና የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ልዩ ልዩ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረጉ ፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበር ፕሬዚዳንት ዳሞት አንተነህ ዶ/ር እንደተናገሩት የመምህራን ማህበሩን አባላት ከተማሪዎች ህብረት ጋር በማቀናጀትና ኮሚቴዎችን ካዋቀርን በኃላ ገንዘቡን ከመምህራንና ሰራተኞች በተጨማሪም ከክረምት ተማሪዎች እንዳሰባሰቡት ተናግረዋል ፡፡ 2 ኩንታል ጤፍ ከደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መንቆረር አግሮ ኢንዲስትሪ ኢንተር ፕራይዝ ድጋፍ እንደተደረገ ገልፀዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ህብረት ምክትል ፕሬዚዳንት ተማሪ ጌጤነህ ሸገን እንደገለጹት የተማሪዎች ህብረት የተዋቀረው በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን ለማገልገል ቢሆንም እንዲህ አይነት አሰቃቂ ሁኔታዎች ሲፈፀሙና የውጩ ማህበረሰብ የእኛን እርዳታ ሲፈልጉ ህብረቱ ይህን አሳዛኝ ክስተት በመገንዘብ የግቢውን ተማሪዎች በማስተባበር ድጋፍ ማድረግ ተገቢ በመሆኑ 40 ሺህ 2 መቶ ብር እንዲሰበሰብ ተደርጓል ብለዋል፡፡ ገንዘቡም ለሟች ልጆች ተሰጥቷል።

የእርዳታ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል እና በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የግብርናና ተፈጥሮ ሀብት ትምህርት ክፍል መምህር ተዋበ ህብስቱ በበኩላቸው ይህንን ድጋፍ ለማድረግ ያነሳሳን የተፈጠረው ክስተት እጅግ ልብ የሚሰብርና አሳዛኝ በመሆኑ ሰብአዊነት ተሰምቶን ሲሆን የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መንቆረር አግሮ ኢንዲስትሪ ኢንተር ፕራይዝ ከደረቅ ምግብ ጀምሮ ለወደፊቱ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተናግረዋል።
በተጨማሪም በተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር በኩልም የዘይትና ሽሮ እንዲሁም በርበሬ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም የደብረ ማርቆስ ከተማ ከንቲባ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ተመስገን ተድላ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ድርጊቱ ከተፈጸመ ጀምሮ እያደረገ ያለው ድጋፍ ለብዙዎቻችን አስተማሪና አርያነት ያለው ተግባር መሆኑን ጠቅሰው ከመማር ማስተማር ስራው በተጨማሪ ለውጩ ማህበረሰብ አርያ የሆነ ስራ መሆኑን ተናግረዋል ። ድጋፉ ዛሬ ብቻ የተጀመረ አለመሆኑንም ጨምረው ገልፀው ይህ አይነት ማህበራዊ ችግሮች ሲያጋጥሙ ዩኒቨርሲቲው ለአካባቢው ማህበረሰብ ቀድሞ የሚደርስ ተቋም መሆኑንም አክለዋል፡፡

================

ከታች ያስቀመጥናቸው የዩኒቨርሲቲያችን ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር አድራሻዎች ናቸው። ተራ በተራ ሊንኮቹን እየተጫናችሁ ትወዳጁን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን

ዌብሳይት www.dmu.edu.et

ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia

እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"
4.9K viewsedited  07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 10:17:00
4.5K views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:37:27 A discussion was held based on the two research papers presented, and various questions and important comments were given by the participating guests.

The President of Debremarkos University Tafere Melakun (PhD) and the President of Development Bank of Ethiopia Honorable Yohannes Ayaleu (PhD) made the concluding speech of the program.

In their speech, they both promised that they will work together to make the project grow into a comprehensive integrated project by providing professional and financial support.
896 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ