Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 28

2022-09-26 10:37:27 The launch program of a project designed to adapt "Enset" for food in the Amhara region was held at Debremarkos University.
===============
Debre Markos University: 24, September 2022 (Directorate of Public Relations and Communication) Debre Markos University and the Development Bank of Ethiopia jointly held a launch program for a project designed to adapt "Enset" for food in the Amhara region.

The President of Debremarkos University Tafere Melaku (PhD) who gave the welcome speech at the program expressed his appreciation for the fact that the Development Bank of Ethiopia accepted the idea and decided to work with the Universiy with full intention of fulfilling social responsibilities.

He added that the project is a pioneer in the field and pointed out that even though "Enset" is a plant that has lived for a long time with us in our region, we do not use it except for baking bread, but it is a food security for more than twenty million people in the Southern part of our country.

He thanked the team of the project who made this project a reality by supporting the idea with research to ensure the food security of our community by bringing the experience of South Ethiopia region to Gojjam in Amara region. He has also promised to provide all the necessary support until the project is completed.

Finally, he conveyed his message that all of our university as well as the outside community should shoulder the responsibility of the project in a sincere spirit so that it can be completed in a better way as this project will be of great benefit to ensure food security for our zone specifically and for our region largely.

President of the Development Bank Ethiopia, Honorable Yohannes Ayalew (PhD) attended the project launch program to adapt "Enset" for food in the Amhara region and delivered a message.

In his message, the fact that the project is being launched at a time when the country is struggling to ensure food security makes its significance greater. He added that when the project is completed, its role in protecting the ecosystem of the region is significant.

He also mentioned that the "Enset" plant is blessed with many good natural qualities and is preferred over other plants to ensure food security.

According to studies, "Enset" is the main source of food for more than 20 million citizens in Ethiopia.

Therefore, the purpose of this project is to enable farmers to produce more dried "Enset" or "Kocho" in the Amhara region to reduce drought and hunger by implementing this project to adapt it for food and to enable farmers to get more income by offering it to the market in addition to using it for food.

He stated that the Development Bank of Ethiopia encourages agricultural researches and innovative ideas related to the development of the country, especially food self-sufficiency.

A teacher and researcher from Wachamo University, Daniel Menor, presented his research paper titled " 'Enset' Productivity and Adaptation".

He explained in his article that "Enset" is a plant that can grow in both lowland and highland climates and has many benefits. Some of its uses include traditional medicine, industrial resources, food, and maintaining soil fertility.

He concluded his article by pointing out that the "Enset" plant has an irreplaceable role in ensuring food security as it can withstand climate change in different conditions and can remain without water for several times.

In this program, the concept of the project titled "Adapting 'Enset' for food in the Amhara region " was presented in detail by the project team.

As we understand from the article presented by Mr. Bawoke Tiruneh, a teacher and researcher of Debre Markos University and the proponent of this project, the project will be implemented in the next 10 years under the ownership of Debre Markos University. The Development Bank of Ethiopia on its own part has provided a financial support of 2 million birr for the project's one-year implementation budget.
835 views07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:36:26 እንሰትን በአማራ ክልል ለምግብነት ለማላመድ የተቀረፀ ፕሮጀክት ማስጀመሪያ መርሐ ግብር በደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ
===============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ መስከረም 14/2015 ዓ.ም (የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ጋር በመተባበር በአማራ ክልል እንሰትን ለምግብነት ለማላመድ የተቀረፀ ፕሮጀክት ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚደንትን ጨምሮ ከተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች ስራ አስኪያጆችና ባለሙያዎች፣ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት እና ም/ፕሬዚደንቶች እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍል ኃላፊዎችና መምህራን፣ ጥሪ የተደረገላቸው የዞንና የወረዳ የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተካሄደ ።

በዚህ መርሐ ግብር ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ታፈረ መላኩ በሀገራችን ሀሳብን ፋይናንስ ማድረግ ባልተለመደበት ሁኔታ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ግን ሃሳባችን ተቀብሎ ማህበራዊ ኃላፊነታችንን እንወጣለን በማለት በሙሉ ፍላጎት ከእኛ ጋር ለመስራት በመወሰናቸው አድናቆታቸውን ገልፀዋል።

አክለውም ፕሮጀክቱ በዘርፉ ፋና ወጊ እንደሆነ ገልፀው እንሰት በክልላችን አብሮን የኖረ ተክል ቢሆንም ከዳቦ ከመጋገሪያነት ውጭ ሳንጠቀምበት ኑረናል ፤ በአንፃራዊነት በደቡቡ የሀገራችን ክፍል ከ20 ሚሊዮን በላይ ለሚሆን ህዝብ የምግብ ዋስትና እንደሆነ ጠቁመዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ያለውን ተሞክሮ ወደ አማራ ክልል ጎጃም በማምጣት እንሰትን (ቆጮን) ለምግብነት በማላመድ የማህበረሰባችንን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ አለብን በሚል ሃሳቡን በምርምር በማስደገፍ ወደ መሬት አውርደው ፕሮጀክቱ እውን እንዲሆን ላደረጉት የፕሮጀክቱ አባላት ምስጋና አቅርበዋል። ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድረስም አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

በመጨረሻም ይህ ፕሮጀክት ለዞናችን ብሎም ለክልላችን ህዝብ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ስለሆነ በተሻለ መንገድ እንዲጠናቀቅ የዩኒቨርሲቲያችንም ሆነ የውጪው ማህበረሰብ ፕሮጀክቱ የእኔ ነው በሚል የቅንነት መንፈስ ሃላፊነታቸውን በጋራ እንዲወጡም መልክታቸውን አስተላልፏል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ክቡር ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) በዚህ መርሐ ግብር ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በንግግራቸውም ፕሮጀክቱ ሀገራችን ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ደፋ ቀና በምትልበት ወቅት የተጀመረ በመሆኑ ፋይዳው የጎላ እንደሚሆን አንስተዋል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የክልሉን ስነ-ምህዳር ከመጠበቅ አንፃርም የሚኖረው ሚና ጉልህ እንደሚሆን ገልፀዋል።

የእንሰት ተክል በርካታ መልካም የተፈጥሮ ባህርያትን የታደለ በመሆኑ ከሌሎች ተክሎች ይልቅ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ተመራጭ እንደሆነም ጠቅሰዋል ።

ጥናቶች እንደሚያሳዩት እንሰት በኢትዮጵያ ውስጥ ከ20 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ዋነኛ ምግብ ምንጭ ነው። በመሆኑም የዚህ ፕሮጀክት ዓላማ በአማራ ክልል በተለይ ድርቅንና እርሃብን ለመቀነስ እንሰትን ለምግብነት የማላመድ ፕሮጀክት በመተግበር አርሶ አደሮች የደረቀ ቆጮን በብዛት እንዲያመርቱ እና ለምግብነት ከማዋል ጎን ለጎንም ለገበያ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኙ ማስቻል መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ሀገርን ለማልማትና በተለይም በምግብ ራስን ከማስቻል ጋር ተያያዥነት ያላቸውን የግብርና ምርምሮች እና የፈጠራ ሀሳቦች እንደሚያበረታታ ገልፀዋል።

ከዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የመጡት መምህር እና በእንሰት ላይ መርምር ያደረጉት ተመራማሪ ዳንኤል መኖር "የእንሰት ምርታማነትና ማላመድ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፉ አቅርበዋል።

ባቀረቡት ፅሑፍ እንደገለጹት እንሰት በቆላማውም በደጋማውም የአየር ንብረት ክልል ውስጥ መብቀል የሚችል ተክል መሆኑንና ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታዎችም እንዳሉት አስረድተዋል። ከጠቀሜታዎቹም ውስጥ እንስት ለባህላዊ መድሀኒትነት፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓትነት፣ ለምግብነት ፣ ለቃጫ መስሪያነት፣ የአፈር ለምነትን ለመጠበቅ የሚሉት ጥቂቶቹ እንደሆኑ አብራርተዋል።

የእንሰት ተክል የአየር ንብረት ለዉጥን በተለያየ ሁኔታ በመቋቋም ያለዉሃ ለበርካታ ጊዜያት መቆየት በመቻሉ ከተመረተ በኋላ እስከ 7 አመት ሳይበላሽ መቆየት ስለሚችል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የማይተካ ሚና እንዳለው በማስገንዘብ ፅሑፋቸውን አጠቃለዋል።

በመርሃ ግብሩ "እንሰትን" በአማራ ክልል ለምግብነት ማላመድ በሚል ርዕስ የተቀረፀው ፕሮጀክ ንድፈ ሃሳብ በዝርዝር ቀርቧል።

የፕሮጀክቱ ሀሳብ አፍላቂ መምህርና ተመራማሪ አቶ ባወቀ ጥሩነህ ካቀረቡት ፅሑፍ እንደተረዳነው ፕሮጀክቱ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ባለቤትነት በቀጣዮቹ 10 አመታት ውስጥ እንደሚተገበርና የኢትዮጵያ ልማት ባንክም የፕሮጀክቱን የአንድ አመት ትግበራ ማስጀመሪያ በጀት የ2 ሚሊዬን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ነው።

በቀረቡት ሁለት ጥናታዊ ፅሑፎች ላይም ውይይት የተደረገ ሲሆን ጥያቄዎችና ጠቃሚ አስተያየቶችም ከተሳታፊ እንግዶች ተሰጥተዋል።

በመርሐ ግብሩ የማጠቃሊያ ንግግር ያደረጉት የደብረማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ታፈረ መላኩን (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚደንት ክቡር ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) ሲሆኑ በንግግራቸው ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሮጀክቱን ሙያዊና የፋይናንስ ድጋፍ በማድረግ ወደ ሁለገብ የተቀናጀ ፕሮጀክትነት እንዲያድግ ለማድረግ በጋራ እንደሚሰሩ ገልፀዋል።
734 views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:36:13
695 views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:36:11
699 views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 10:36:04
822 views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 16:54:26
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊያንና የዩኒቨርሲቲያችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ
2.1K views13:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 12:01:04
#NEW
2.7K views09:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 11:56:33 ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለፀ

==============

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፦ መስከረም 12/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)
ትምህርት ሚኒስተር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ መመሪያ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡ ዩኒቨርሲቲያችንም ይህንን መመሪያ በመቀበል ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ልዩ ልዩ ግብረ ኅይሎችን በማዋቀር በሙሉ አቅሙ እየሰራ ይገኛል፡፡

በዩኒቨርሲቲያችን የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ይኼይስ አረጉ (ዶ/ር) ዩኒቨርሲቲው በዋናው ግቢ፣ በቡሬ እና በጤና ካምፓስ ከ36 ሺህ በላይ ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ላለፉት ሁለት ሳምንታት ቅድመ ዝግጅት ሲያደረግ እንደቆዬ ገልፀው የሚመጡት የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች እስካሁን ዩኒቨርሲቲው ከሚያስተናግዳቸው መደበኛ ተማሪዎች በሶስት እጥፍ የጨመረ በመሆኑ ሙሉ አቅማችንን ተጠቅመን ግቢዎቻችንን ለፈተና ምቹ ለማድረግ እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ ፈተናው በሁለት ዙር የሚሰጥ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከ26 እስከ 28/01/2015 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲው የሚገቡ ሲሆን በ29 አጠቃላይ ገለፃና ማብራሪያ እንደሚሰጣቸውና ከ30 እስከ 02/02/2015 ዓ.ም ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል፡፡ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ ኤሌክትሮኒክስ ነክ መሳሪያዎችን ይዘው እንዳይገቡ የተከለከለ ሲሆን አስፈላጊ መረጃዎችንም ወደፊት በሁሉም ሚዲያዎች ስለሚገለፁ ተፈታኝ ተማሪዎች መረጃዎችን በቅርበት በመከታተል ማክበርና መጠበቅ ያለባቸውን ነገር በመከታተል ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ይሄይስ አረጉ (ዶ/ር) አሳስበዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲያችን አካዳሚክ ጉዳዮች ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር በለጠ ያዕቆብ (ዶ/ር) ተፈታኝ ተማሪዎችን ያለ ምንም እንከን ለማስፈተን ትምህርት ሚኒስተር በላከው መመሪያ መሰረት አንድ ዋና የፈተና አስፈፃሚ ግብረ ኃይል በማቋቋም በአስተዳደርና በአካዳሚክ የተከፋፈሉ ኮሚቴዎች ተዋቅረው የመፈተኛ ክፍል፣ የምኝታ ክፍል፣ የምግብ አገልግሎት፣ ልዩ ልዩ ጥገናና የፅዳት ኮሚቴዎች ተቋቁመው በስፋት እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ፈታኝ መምህራንን በተመለከተም ከዋናው እና ቡሬ ካምፓስ 539 ፈታኝ ፣ 36 አንባቢ እና 17 ቆጣሪ ተመልምለው የስም ዝርዝራቸው ለትምህርት ሚኒስቴር መላካቸውን ተናግረዋል፡፡

የፀጥታውን ዘርፍ በተመለከተም ተማሪዎች ያለምንም የፀጥታ ስጋት እንዲፈተኑና ንብረቶች እንዳይበላሹ ለማድረግ እንደተዘጋጁና የደህንነት ካሜራዎችን በጥንቃቄ ለመጠቀም ባለሙያዎችን ከወትሮው በተለየ አደራጅተው እየሰሩ መሆናቸውን በዩኒቨርሲቲያችን ፀጥታና ደህንነት ዳይሬክተር ኮማንደር እሱባለው አላምር ገልፀዋል፡፡

በዩኒቨርሲቲው የምግብ ዝግጅትና መስተንግዶ አገልግሎት ቡድን መሪ አቶ ይታየው አለም በበኩላቸው የምግብ ቤት ግብአት ሊሆኑ የሚችሉ ቁሳቁሶች ከተለዩ በኋላ በግዥ፣ በጥገናና በውሰት የሚሟሉትን ለይተን በየዘርፋቸው እያሟላን ነው ብለዋል፡፡

የተማሪዎች አገልግሎት የመኝታ ክፍል አስተባባሪ አበቡ ዋለ ተማሪዎች ብዛት ያላቸው በመሆኑ የመኝታ ክፍል እጥረት ቢያጋጥመንም ክፍሎችን አመቻችተን ጥገና የሚያስፈልጋቸውንና በግዥ የሚሟሉትን የመኝታ ቁሳቁሶች ማዘጋጀታቸውን ገልፀው ተማሪዎች ሲመጡ አንሶላ፣ ትራስ ልብስ፣ ብርድልብስና ሌሎች ልብሶች ይዘው መምጣት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
2.9K viewsedited  08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 11:56:19
2.6K views08:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ