Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 25

2022-11-01 12:20:18
#NEW
4.3K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-01 10:36:33
#NEW
5.0K views07:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:24:13
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራር ጽ/ቤት በመደበኛው መርሃ ግብር በመጀመሪያ ዲግሪና ሁለኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን የምዝገባ ቀን አሳወቋል። በዚህም መሰረት ህዳር 08-09 ቀን 2015 ዓ.ም መሆኑን የገለፀ ሲሆን ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማያስተናግድ መሆኑንም አሳስቧል።

ከታች ያስቀመጥናቸው የዩኒቨርሲቲያችን ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር አድራሻዎች ናቸው። ተራ በተራ ሊንኮቹን እየተጫናችሁ ትወዳጁን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን


ዌብሳይት www.dmu.edu.et

ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia

እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"

ከእኛ ጋር ሰለሆናችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው!
9.0K viewsedited  09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:20:44 "የዞናችን ትምህርት ስብራቶችና የመዉጫ መንገዶች" በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር መድረክ ተደረገ
==============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ ጥቅምት 19/2015 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ) የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ እና የምስ/ጎጃም ዞን ትምህርት መመሪያ በጋራ በመተባበር የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊዎች ፣ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ፣ ምክትል ፕሬዚደንቶችና ልዩ ልዩ የስራ ኃላፊዎች ፣ የምስ/ጎ ዞን የብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ የምስ/ጎ ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የወረዳ አስተዳዳሪዎች፣ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊዎች ፣ ሱፐር ቨይዘሮች ፣ ርዕሳነ መምህራን ፣ በየደረጃው የሚገኙ የመምህራን ማህበር ስራ አስፈፃሚዎች እና የትምህርት ባለሙያዎችን ያካተተ ውይይት ጥቅምት 18 ቀን 2015 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ አዳራሽ ውስጥ ተካሂዷል።

የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የምስ/ጎጃም ዞን ትም/መመሪያ ሀላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ በመልዕክታቸው እንደገለፁት የምስ/ጎጃም ዞን የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች በተለይ የተወሰኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ያሳዩት ህገ_ወጥ ስነ_ምግባር ዞኑን ጥላሸት የቀባና ትዝብት ላይ የጣለ ተግባር ነው። ለአብነት ደጀን፡ እናርጅ እናዉጋ እና የሸበል በረታ የተወሰኑ ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ጥለው ሂደዋል። በተጨማሪም አንዳንድ ተፈታኞኝ ጎበዝ ተማሪዎችን በማስፈራራት ለመኮረጅ በመሞክሩም በዪኒቨርስቲው አመራሮች እና በፈታኞች ጥረት እደከሸፈ ገልጸዋል። ሀሳባቸዉን ሲያጠቃልሉም በዞኑ በፈተናው ውቅት ችግሮች ቢፈጠሩም የተፈጠሩ ችግሮችን ቶሎ መፍትሄ በመስጠት ፈተናው ተጠናቅቋል ብለዋል።

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምስ/ጎጃም ዞን የብልጽግና ፖርቲ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ዋለ አባተ ደግሞ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈጠሩት ችግሮች የትምህርት ስርዓታችን ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ቁልጭ አድርጎ ያሳዬ ነዉ ያሉ ሲሆን የተፈጠረዉን ስብራት በዘለቄታዊነት ለመፍታት በየደረጃው ያሉት ባለድርሻ አካላት የተሰጣቸውን ሃላፊነት በአግባቡ ሊውጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

የደ/ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚደንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) በበኩላቸው የደ/ማርቆስ ዩኒቨርስቲ አመራሮች እና የግቢው ማህበረሰብ ተፈታኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ያደረግነው ቅድመ ዝግጅት ጠንካራ አንደነበር ገልጸዉ የተወሰኑ ተፈታኞች ያሳዩት ስነምግባር የጎደለው ድርጊት ግን እንዳሳዘናቸውና ገልፀዋል። እነዚህ ስነ ምግባር የጎደላቸው ተማሪዎች እረብሻና ግርግር በመፍጠር ፈተናውን ለማስተጎጓል ቢሞክሩም የዪኒቨርስቲው አመራር ችግሩን በመቆጣጠር ሌሎች ተፈታኞች ተረጋግተዉ እንዲፈተኑ ከፍተኛ እርብርብ በማድረግ ፈተናዉ እንዲጠናቀቅ ሆኗል ብለዋል።

የአማራ ክልል ትም/ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ሙላዉ አበበ በዚህ ወሳኝ ስዓት እንደዚህ ያለ ውይይት እንዲዘጋጅ የተባበሩትን የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያንና የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲን አመስግነው በክልሉ ፈተናው ከተሰጠባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መቅደላ አምባ ፣ በደ/ማ እና በደብረ ታቦር ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የተፈጠረው ነገር የሚያስቆጭና ወደራሳችን ብቻ እንድንመለከት የሚያደርግ ነገር መሆኑን ጠቁመዋል።

በምክክር መድረኩ ላይ "Paradymshift in Education" በሚል ርዕሰ ቁልፍ መልዕክት ያስተላለፉት በመቅደላ አምባ ዩኒቨርስቲ በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የመካነ ሰላም ካምፓስ ዋና ዳይሬክተር ሽበሺ አለባቸው (ዶ/ር ) ሲሆኑ በመልከዕክታቸውም የተሰበረው አሁናዊ የተማሪዎቻችን ሁኔታ የሚያሳየው በህፃናት ላይ ስራዎችን ባለመስራታችን የመጣ ችግር መሆኑን ገልፀው ይሄ ችግር እንዲቀለበስ ካስፈለገ ህፃናት ላይ ትኩረት ሰጥተን መስራት እንደሚገባን በአንክሮት አብራርተዋል።

"የምስ/ጎጃም ዞን ትምህርት ስብራቶች እና የመዉጫ መንገዶች" በሚል የምስ/ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ ሃላፊ አቶ ጌታሁን ፈንቴ ሰፊ ይዘት ያለው ፅሑፍ ያቀረቡ ሲሆን በትምህርት ጥራት ላይ ያንዥበቡና ጥላ ያጠሉ ሳንካዎችን በዝርዝር ለታዳሚውቹ አቅርበዋል።

በሌላ በኩል የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አፈጻጸም ግብረ መልስና ትዝብት በሚል የደ/ማ ዩኒቨርስቲ አካደሚክ ጉዳዮች ኤክዚኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር በለጠ ያዕቆብ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ለማስፈፀም ከመነሻ እስከ ፍፃሜ ያደረገውን እንቅስቃሴና በመፈተናው ሂደትም ወቅት የገጠሙ ችግሮችን በዝርዝር አቅርበዋል።

በባ/ዳር ዩኒቨርሲቲ መምህር ፣ ተመራማሪና ደራሲ እንዲሁም በአሁኑ ስዓት በክልላችን እየገጠሙን ያሉ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅፋቶችን ለመቀልበስ በሚያስችል መልኩ ማህበረሰብን እያነቁ የሚገኙት የሻምበል አጉማሴ (ዶ/ር) "ታላቅ ህዝብን ወደ ቀደመ ክብሩ መመለሻ የትምህርት አብርሆት" በሚል ርዕስ ፅሑፍ አቅርበዋል። ባቀረቡት ፅሑፍም በክልላችን ብሎም በሀገራችን እየተስተዋሉ ያሉ መዛነፎች ፣ መንስኤዎችና መፍትሄዎችን በተጨባጭ ምሳሌዎችና ማብራሪያዎች አስደግፈው ታዳሚዎችን በሚያዝናና እና ቁምነገር በሚያስጨብጥ መልኩ አቅርበዋል።

በቀረቡት የመወያያ ፅሑፎች ላይም ሰፊ ውይይቶችና አስተያየቶች ከታዳሚዎቹ የተሰጡ ሲሆን በትምህርት ጥራት ላይ የገጠመን ፈተና ከባድ መሆኑን እና ይህንን ችግርም ለመፍታት መገፋፋትን በመተው በጋራ መስራት እንደሚገባም በሁሉም የውይይቱ ታዳሚዎች ዘንድ መግባባት ላይ ተደርሷል።

በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ ወረዳዎች፣ከተማ አስተዳደሮችና ትምህርት ጽ/ቤቶች እውቅና በመስጠት እና ዶክተር ሻምበል አጉማሴን ደግሞ ልዩ ተሸላሚ በማድረግ የውይይቱ ፍፃሜ ሆኗል።
5.9K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:20:37
5.2K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:20:33
5.0K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 12:20:27
5.7K views09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 14:48:37
#አስቸኳይ_ማስታወቂያ_ለሁሉም_እንዲደርስ_እንድታጋሩልን_እንጠይቃለን!
የኮሌጅ ወይም የዩኒቨርሲቲ ምሩቅና የፈጠራ ሀሳብ ያላችሁ ሴት አመልካቾችን ይመለከታል!
9.6K views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 06:35:59 የ70 ዓመት ዕድሜ ባለፀጋዋ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ገቡ

================
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፣ መስከረም 29/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) ስማቸው ወ/ሮ አቡኔ ወንዴ ታምር ይባላሉ። በምስራቅ ጎጃም ዞን በደብረ ኤሊያስ ወረዳ ተወለዱ ። ቤተሰቦቻቸው ገና በ7 አመት ዕድሜያቸው ባል እንዳጋቧቸው ይናገራሉ። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን ( ከ1-6ኛ ክፍል ) ከአጎታቸው ጋር ወደ መተሃራ ከተማ በመሄድ ተምረው በከፍተኛ ውጤት ማጠናቀቃቸውን ያስረዳሉ።

በወቅቱ ሲያስተምራቸው የነበሩት አጎታቸው በድንገተኛ ሁኔታ ከዚህ ዓለም በሞት እንደተለዬ የሚናገሩት ወ/ሮ አቡኔ የአጎታቸውን ሞት ተከትሎ ወደ ትውልድ ቀያቸው ቢመለሱም ቤተሰቦቻቸውም እርሳቸውን ለማስተማር የሚያስችል አቅም እንዳልነበራቸውና በዚህም የተነሳ የሚወዱትን የትምህርት ዓለም ለበርካታ አመታት አቋርጠው መቆየታቸውን ገልፀዋል። ገና በለጋነት ዕድሜያቸው ህይወት ፊቷን እንዳዞረችባቸው የሚናገሩት ወ/ሮ አቡኔ በየሰዎች ቤት እንጀራ በመጋገር፣ ደረቆት በመቁላት እና የተለያዩ የቀን ስራዎችን በመስራት ኑሮን እንደነገሩ ሲገፉ መቆየታቸውንም ይጠቁማሉ።

ሆኖም ለትምህርት በነበራቸው ጥልቅ ፍላጎት የተነሳ ለበርካታ አመታት አቋርጠውት የቆዩትን ትምህርት ካቆሙበት ለመቀጠል እድሉን እንዳገኙና በዚህ ዓመትም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለመውሰድ ወደ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እንደገቡ አስረድተዋል።

ትምህርትን እድሜ እንደማይገድበውና ወጣቶችም ዓላማቸውን ለማሳካት ከአልባሌ ቦታዎች ራሳቸውን አቅበው ትምህርታቸው ላይ ብቻ እንዲያተኩሩም መክረዋል።

ያቋረጡትን ትምህርት እንደገና በጀመሩበት ወቅት ብዙ የስነ ልቦና ጫና የሚያሳድሩ ነገሮች ደርሰውብኛል የሚሉት ወ/ሮ አቡኔ የደብረ ኤሊያስ ወረዳ አመራሮችና አሰሪዎቻቸው እያበረታቷቸው እዚህ ለመድረስ እንደቻሉ በመግለፅ እስካሁን ከጎናቸው ሆነው ላበረታቷቸው ሁሉ ምስጋናቸውንም አስተላልፈዋል።

ለተጨማሪ መረጃዎች



ዌብሳይት www.dmu.edu.et

ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

ቲዊተር https://twitter.com/dmu_ethiopia

እንስታግራም https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

ሊንክድኢን https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/

"የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!"

ከእኛ ጋር ሰለሆናችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው!
3.2K viewsedited  03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 06:35:49
3.0K views03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ