2023-04-08 12:55:07
አሁን በክርስቶስ ልትድን የምትችለው ነፍስ ክርስቶስን ከማመን በላይ ከፍ ብላ በማደግ ክርስቶስን መምሰል አለባት። ይህም ሦስት ነገሮችን አጠቃሎ ማለትም፦ ሥጋን ፣ነፍስንና መንፈስን በመጠበቅና በመቀደስ ቅዱስ የሆነ ኑሮ ስንኖር እግዚአብሔርን ስንመስል መዳናችን ተጠብቆ እውን ይሆናል።ይህም በሀይማኖት ጸንቶ መኖር በሚል ተገልጧል።
"የደቀ መዛሙርትን ልብ እያጸኑ በሃይማኖትም ጸንተው እንዲኖሩ እየመከሩና። ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል እያሉ(ሐዋ 14:21-22) ተብሎ ተጽፏል።
ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ክርስቶስ የመሠረታት ሐዋርያት ያስፋፏት ናትና ቅዱሳን ሐዋርያት በመልእክታቸው እንዲህ ብለውናል።
"ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል" እያሉ የእውነትን ወንጌል ሰበኩ። ከዚህ መልእክት አንጻር፦
የሐዋርያት ቃል ሲብራራ "ድኛለሁ ተፈውሻለሁ ዘና በል" የሚል ወንጌል አለመኖሩ ነው።The Lord Jesus opened heaven, not closed hell (ጌታ ኢየሱስ ገነትን ከፈተ እንጂ ሲኦልን አልዘጋም)። ከአዳም የኃጢአት ውጤት ያዳነን ብቸኛው አዳኝ እርሱ ቢሆንም ክርስቶስ መስቀሌን ተሸከመልኝ ብለን የምንተወው መስቀል የለም።
"የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ_ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።" ብሎናል። (1ኛ ጴጥ 2:21) የተወልን ፍለጋው Living in struggle and carrying the cross(መስቀሉን መሸከም በተጋድሎ መኖር) ነው። ስለዚህ "በጠበበው በር ለመግባት ተጋደሉ፤ እላችኋለሁና፥ ብዙዎች ሊገቡ ይፈልጋሉ አይችሉምም" ብሎ እውነቱን ነግሮናል።(ሉቃ 13:24) ባለው ቃል መሠረት ድህነትን መጠበቅ ማሳደግና መጋደል መስቀሉንም መሸከም ግድ ነው።
ስለዚህ ለመዳን አራት ነገሮችን መያዝ ግድ ይልሃል
በሥርዓተ አምልኮ መጽናትና መሳተፍ ይህም
ምስጢራትን መፈጸም(መጠመቅ ሜሮን
ቁርባን መቀበል)
መንፈሳዊ ተጋድሎ(ጾም ጸሎት ስግደት)።
መልካም ስራ (ትህትና ፍቅር ምጽዋት)
ያስፈልግሃል።
በአጠቃላይ ያለ ክርስቶስ ኦርቶዶክስን ማሰብ መኪና ያለነዳጅ ያለምንም ኃይል መብረሩን ያቁም እንደማለት ነው። ክርስቶስን “እኛ ራሳችን ሰምተነዋልና፤ እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ሆነ እናውቃለንና” (ዮሐ4፥42) እንደተባለ እኛም እንዲሁ እንላለን።
እምነታችን በሐዋርያው እንደተገለጸው ይህ ነው። “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።” — ሐዋርያት 4፥12 ጌታችንን አምላካችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የተቀበልንው መዳን በእርሱ የሆነ አዳኝ መድኃኒት ስለሆነ ነው። እኛስ ኢየሱስ በተባለ በ ክርስቶስ ስም አምነናል አውቀናል በእርሱ እንኖራለን ደግሞም እንድናለን ድነንማል።
በተረፈ ጠቀለል አድርጌ ስመልስ ስለመጽሐፍ ቅዱስ ላነሳሽው።፦ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የእምነት አስተምህሮ መሠረቶች 3 ናቸው።
1, ዶግማ= (የማይሻር የማይሻሻል የመጽሐፍ ቅዱስ ሙሉ መልእክት ሲሆን ለድርድር የማይቀርብ ጽኑ መሠረት ነው)
2, ቀኖና = (ቤተክርስቲያን እየተጠበቀች እዚህ የደረሠችበት የአባቶች ሲኖዶሳዊ ውሳኔዎች)
3, ትውፊት = (በቅብብሎሽ ሲወርድ ሲወራረድ የመጣ የዶግማ መጠበቂያ አጥር)
የትውፊት ትክክለኛነት 3 መመዘኛዎች
, ማንኛውም ትውፊት የመጽሐፍ ቅዱስን ሐሳብ ተጻርሮ ወይም ተቃርኖ ከተገኘ በምንም ዓይነት ሁኔታ ተቀባይነት የለውም።
, ማንኛውም ትውፊት እርስ በእርሱ ተጣርሶ ከተገኘ በጭራሽ ተቀባይነት የለውም።
, ማንኛውም ትውፊት የሌሎች አኃት አብያተ
ክርስቲያናትን አስተምህሮ ተቃርኖ ከተገኘ
ተቀባይነት የለውም።
ትውፊት እነደየ ሁኔታው ሊሻሻል ይችላል። ትውፊትን የማሻሻል ሥልጣን ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ ብቻ ሲሆን የሕዝብ አስተያየትን መነሻ በማድረግ የሊቃውንት ጉባኤ መርምሮ የውሳኔ ሐሳብ ሲያቀርብለት ሙሉ ለሙሉ ወይም በከፊል ሊያሻሽለው ይችላል።
ትውፊት እንዲሻሻል የሚያደርጉ 3 ገፊ ምክንያቶች
, ከሕዝብ ንቃተ ኅሊና ጋር መጣጣም ካልቻለ
የአካባቢ ሁኔታ ቢቀየር (enviromental change) ለምሳሌ ለመጾም የማያስችል የአየር ሁኔታ ቢፈጠር
የፖለቲካ ሁኔታ በተቃራኒዎች በብልጫ ሲመራና እንደ ቀድሞው ለመገልገል አስቸጋሪ ሲሆን
በዝርዝር ለማሳየት ያህል እስኪ ዶግማ ምንድን ነው? ቀኖና ትውፊትስ?
ዶግማ በዓለም አቀፍ ጉባኤያት (ecumenical councils) የጸደቀ የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እምነት ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያን ከአበው የተቀበለችውን እምነት የምትገልጥባቸው አስተምህሮዎች ደግሞ doctrines ይባላሉ፡፡ ለምሳሌ፡- “ኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክ ነው” ይህ ዶግማ ነው፤ “ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ናት” ይህም እንደዚሁ፡፡ የክርስቶስን አምላክነት ለማይቀበሉ አርዮሳውያን፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ አትናቴዎስ ዘእስክንድርያን አስተምህሮ (doctrine) ተከትላ መልስ ሰጥታለች፤ ስትሰጥም ትኖራለች፡፡ ድንግል ማርያምን ወላዲተ አምላክ (Theotokos) ብለው ለመቀበል ለሚቸገሩ ንስጥሮሳውያን ደግሞ፣ እንዴት ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም “ወላዲተ አምላክ” እንደምትባል የምንገልጥበት ወይም የምናስተምርበት ዶክትሪን፣ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ያስተማረው ትምህርት ነው፡፡
እነዚህ አስተምህሮዎች በዓለም አቀፍ ጉባኤያት የተወሰኑ ሲሆን፣ ውሳኔያቱን ከተጨማሪ ጉዳዮች ጋር የቤተ ክርስቲያን አበው በቀኖናት (canons) አጽድቀዋቸዋል፡፡ ለምሳሌ እንደ አውሮጳውያኑ አቆጣጠር በ325 ዓመተ እግዚእ (AD) የተጠራው ጉባኤ ኒቅያ 20 ቀኖናት አሉት፡፡ እነዚህንና ሌሎቹን ዓለም አቀፋዊና ብሔራዊ ውሳኔያት፣ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ከርስቲያን Holy Canons (ቅዱሳት ቀኖናት) በማለት ትጠራቸዋለች፡፡ ስለዚህ እነዚህ ቅዱሳት ቀኖናት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በዓለም አቀፍ ጉባኤያተ አበው የጸደቁና የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ የሚያንጸባርቁ (ከዶግማዋ ጋር የሚስማሙ እንጂ፣ የማይጋጩ) ናቸው፡፡
“ቀኖናት ይሻሻላሉ/ ይለወጣሉ” ሲባል “እንደ ቀኖናው ዓይነት ይወሰናል፤ የሚለወጥና የማይለወጥ አለ”፡፡ ለምሳሌ የክርስቶስን የባህርይ አምላክነት ወይም የመለኮትና ትስብእትን ተዋሕዶ አስመልክቶ ቅዱሳን አባቶቻችን የወሰኗቸው ቀኖናት Dogmatic Canons ስለሆኑ ማንም ተነሥቶ ሊለውጣቸው አይችልም፡፡ Practical የሆኑ ጉዳዮችን በሚመለከቱ ቀኖናት ላይ ግን፣ በሐዋርያት መናብርት የተሾሙ አበው ወይም የእነርሱ ተከታዮች (ተላውያነ አበው) የሆኑ የብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጉባዔ (ቅዱስ ሲኖዶስ) ማሻሻያ ማድረግ ይችላል፡፡ ማሻሻያ ከተደረገባቸው practical canons መካከል አንዱን ልጥቀስ፡፡ በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን፡- ቅስና መሾም የሚገባው ሰው 30 ዓመት የሞላው እነደሆነና ኤጲስቆጶስ ደግሞ በ50 ዓመቱ መሾም እንዳለበት የሚደነግግ ቀኖና ነበር፡፡ በሂደት ግን ቤተ ክርስቲያን ተምረውና በቅተው ለተገኙ ልጆቿ 30 ወይም 50 ዓመት ባይሞላቸውም የቅስና እና ጵጵስና መዓርግ ሰጥታለች፡፡
521 views09:55