Get Mystery Box with random crypto!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @behlateabew
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.08K
የሰርጥ መግለጫ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ
"የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነው እኛ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ ነው።"
ቅዱስ አትናቴዎስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/joinchat/AAAAAESAiVPCib48ZxL1Pw

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2023-04-18 05:39:02
360 views02:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 07:34:46 የትንሣኤ ሰኞ ፦ ማዕዶት

በዕብራይስጥ ፓሳሕ ይባላል ትርጉሙም መሸጋገሪያ ማለት ሲሆን አልፎ አልፎ ሔደ ማለት ነው። ይኸውም የእስራኤል ልጆች በግብፅ ሀገር ነውር የሌለበት የዓመት ጠቦት አርደው ደሙን የደጃፋቸውን መቃንና ጉበን በመርጨታቸው መልአከ ሞት ደሙ የተረጨበትን ቤት የበኩር ልጃቸውን እያለፈ ስለሄደ ነው። ዘፀአት 12 ፥ 1-13

አንድም፦ እስራኤል ዘስጋ የኤርትራን ባህር በደረቅ የመሻገራቸው ከግብፅ ወደ ከነዓን የመውጣታቸው ከባርነት የመላቀቃቸውን ወደ ነፃነት የመሸጋገራቸው መታሰቢያ ነው።

በሐዲስ ኪዳን ደግሞ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ብዙ ሺህ ነፍሳት ከሲዖል ወደ ገነት ተሻግረዋልና ይህ ዕለት ማዕዶት(መሻገር) ተባለ ።
1ኛ ጴጥሮስ 3 ፥19
821 views04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 09:55:57
566 views06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 09:52:42 ሞት ሆይ! መውጊያህ ወዴት አለ? ሲዖል፥ መቃብርም ሆይ! ድል መንሣትህ ይዞም ማስቀረትህ ወዴት አለ?
ክርስቶስ ተነሣ፤ ሞት ሆይ፥ አንተም ጠፋህ!
ክርስቶስ ተነሣ፣ አጋንንትም አዘኑ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መላእክትም ሐሴት አደረጉ!
ክርስቶስ ተነሣ፤ የሰው ሕይወትም ነጻ ወጣች!
ክርስቶስ ተነሣ፤ መቃብርም ባዶ ኾነች!
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ለአንቀላፉት ኹሉ በኵር ኾኖላቸዋልና፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
577 views06:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 06:34:12
664 views03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 06:24:06
“በክርስቲያን ሰንበት ዛሬ ደስታ ኾነ። ክርስቶስ ከሙታን ተነሥቷልና ለያት አከበራት ከኹሉም ከፍ ከፍ አደረጋት''
           ቅዱስ ያሬድ

እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን!
712 views03:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 06:18:46 ክርስቶስ ተንሥአ እምሙታን፥
ሞተ ወኬዶ ለሞት፥
ለእለ ውስተ መቃብር
ወሀበ ሕይወተ፡ ዘለዓለም ዕረፍተ።

ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፥
ሞቶ፡ ሞትን አጠፋው፤
በመቃብር ላሉትም፡
የዘለዓለም ዕረፍት የሚኾን ሕይወትን ሰጠ።
544 views03:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 05:57:33
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን
አሠሮ ለሰይጣን
አግዓዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዕዜሰ
ኮነ
ፍሥሐ ወሰላም
610 views02:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 22:52:25
"ከሙታን ተነሥቶ ሲኦልን ረግጦ በሞቱ ሞትን ደመሰሰው”
መጽሐፈ ኪዳን

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሰን!
213 viewsedited  19:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 07:38:53 አክፍሎትን ማን ጀመረው

የሰሙነ ሕማማት የመጨረሻው አክፍሎት ይባላል የበረታ ከሐሙስ ጀምሮ አብዛኛው ከዓርብ ጀምሮ እስከ ትንሣኤ ያከፍላል የአክፍሎት መሠረቱ ሐዋርያት ናቸው
በመጀመሪያ የጌታን ትንሣኤ ሳላይ እህል ውሃ አልቀምስም ያለው ያዕቆብ እኹ ለእግዚእነ ወይም የጌታ ወንድም በመባል የሚታወቀው የአረጋዊው የዮሴፍ ልጅ ከጌታ ጋር ያደገው ቅዱስ ያዕቆብ ነው

ይህ አባት ቅዱስ ያዕቆብ የጌታችንን መከራ የተመለከተ የእመቤታችንን ሐዘን በዐይኑ ያየ በመጀመሪያ ቅዱስ የሴፍ የልጆቹ እናት በሞት ተለይታ ነበረና አራት ወንዶች ሦስት ሴቶች ልጆች እናታቸው የሞተችባቸውን ልጆች ያሳድግ የነበረው ጻድቁ ዮሴፍ እናታቸውን በሞት የነጠቀ እግዚአብሔር እናት ከቤተ መቅደስ አመጣላቸው እመቤታችን እናታቸው ለሞተችባቸው እናት ኾና መሰጠቷ በኃላ በመስቀል እንታችን ለሞተችብን ለሔዋን ልጆች ለኛ እናት ኾና እንደምትሰጠን የሚያመለክት ነበር ከጻድቁ ዮሴፍ ልጆች ከአራቱ ይህ ቅዱስ ያዕቆብ ትንሣኤውን ሳላይ አልቀምስም በማለቱ ሁሉም ተከተሉት እኛም አንበላም ብለዋል እመቤታችን ናት የጀመረችው የሚባለው እሷ ከልደት እስከ ቀራንዮ በመከራ ነው የኖረችው ደግሞም የሐኬትን እንጀራ አትበላም ተብሎ ተጽፏል ከልጇ የመከራ ጽናት አልተለየችም በመስቀል ለቅዱስ ዮሐንስ እናትህ ናት ብሎ በዮሐንስ አንጻር ለኛ የተሰጠች ናትና ከዚያን ሰዓት ጀምሮ ደቀመዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት ምግቧም ሰማያዊ መና ነው ዐይኗም ማየት የለመደው ሥዕለ ኪሩብ ነው
ጆሮዋም መስማት የለመደው ትንቢተ ነቢያትን ቅዳሴ መላእክትን ነው
እግሯም የለመደው ወደ ቤተ መቅደስ መሄድ ነው
እጇም የለመደው ሐርና ወርቅ መፍተል መሶበወርቅ መስፋት ለተጠማ ውሻ ውሃ ቀድታ መስጠት ነበረ እመቤታችን ሰውነቷ በጾም አንደበቷ በትእግስት በጸሎት የታወቀ ስለኾነ እመቤታችን አክፍሎትን ጀመረችው መባሉ አያስደንቅም ታላቁ ሊቅ በረከታቸው ይደርብንና የኔታ ገብረ ሥላሴ ቅዱስ ያዕቆብ ወልደ ዮሴፍ እንደ ጾመ ሌሎችም እንደተከተሉት ተናግረዋል መጋቤ ብሉይ አለቃ ታየ በረከታቸው ይደርብንና እሳቸውም በተመሳሳይ የገለጹት ይንኑ ነው

ቅዱስ ያዕቆብ የጌታ ወንድም የተባለበት በቤተ የሴፍ አብረው ስላደጉ ነው ይህ ቅዱስ ያዕቆብ አብዝቶ በመቆም ይጸልይ ስለነበር እግሩን ያመው ነበረ በዚህ ምክንያት የኢየሩስ አሌም ኤጲስ ቆጶስ ኾነ የመጀመሪያውን የሐዋርያት ጉባኤ ሲኖዶስ በሊቀመንበርነት የመራው ይህ ቅዱስ ያዕቆብ የጌታ ወንድም የተባለው ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ባለ አምስት ምዕራፍ መልእክት የጻፈ እሱ በሌላም ይህ አባት በሶርያ ቤተክርስቲያን ጻድቁ ያዕቆብ በ60 ዓም የደረሰው የእመቤታችን ቅዳሴ ይገኛል The Anaphora Of St Mary The Liturgy Of St James The Just 60 (A D )ነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከሐዋርያት የቀጠለ ትምሕርት አሠረ ክህነት ያላት ተሰምቶ የማይጠገብ ትምህርት ሥርዓት ጸሎት ዜማ ወዘተ ከፈጣሪ የተሰጣት ብቸኛ በምድር ያለች ሰማያዊት የእግዚአብሔር መንግሥት ናት ለሁላችሁም መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ።
686 views04:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ