Get Mystery Box with random crypto!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @behlateabew
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.08K
የሰርጥ መግለጫ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ
"የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነው እኛ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ ነው።"
ቅዱስ አትናቴዎስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/joinchat/AAAAAESAiVPCib48ZxL1Pw

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 40

2022-07-11 21:07:59
1.9K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 18:53:54 “....#ኑ፥ በእግዚአብሔር ብርሃን #እንሂድ።”
— ኢሳይያስ 2፥5
2.6K views15:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:39:47 ሰኔ 30 የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት ልደቱ ነው

በዚህች ቀን የጌታን መንገድ ጠራጊው፤ ሐዋርያው፤ ነብዩ ሰማዕቱ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ቀኑ ነው፤ መስከረም 2 አንገቱ የተቆረጠበት ነው ሚያዚያ 15 እረፍቱ ነው፤ አንገቱ ከተቆረጠ በኋላ የተቆረጠች አንገቱ ክንፍ አውጥታ ለ15 ዓመት በሳውዲ አረቢያና አካባቢው ወንጌልን ሰብካለች፤ የካቲት 30 ቀን የዮሐንስ ራስ የተገለጸችበት ቀን ነው። ከነዚህ አራት በዓላት ሁለቱን ቤተክርስቲያን ታቦተ ህጉን አውጥታ በደማቁ ታከብረዋለች እነዚህም ሰኔ 30 ልደቱና መስከረም ሁለት አንገቱ የተቆረጠበትን ቀን ነው።

ጨካኝ ሄሮድስ የቤተልሔም ህጻናትን ሲጨፈጭፍ መጥምቁ ዮሐንስ ከእናቱ ከቅድስት ኤልሳቤጥ ጋር ወደ ሲና በርሃ ተሰደደ፤ ኤልሳቤጥ በጣም አርጅታ ነበር ያን በረሃ ታዲያ እንዴት ቻለችው ያውም ልጅ አዝላ ልጅ ተሸክማ ረዳት ሳይኖራት ብቻዋን፤ አባቱ ዘካርያስ በምኩራብ በመሰዊያው ፊት ልጅህን አምጣ ብለው አንገቱን ቆርጠው ገደሉት። ኤልሳቤጥም ሲና በርሃ ላይ ሞተች ህጻኑ ዮሐንስ ብቻውን ቀረ፤ የእናቱን በድነ ስጋ አቅፎ አለቀሰ፤ሁሉን ቻይ ሁሉን የሚያይ፤ ሁሉን የሚመረምር ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን እናቴ ሆይ ዘመድሽ ኤልሳቤጥ በበርሃ አርፋለች እንቀብራት ዘንድ እንሂድ አላት ደመና ጠቅሰው ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትለው ሄደዋል ገንዘውም ቀብረዋታል፤ ከዚህ በኋላ እመቤታችን ልጄ ወዳጄ ሆይ ዮሐንስን ይዘነው እንሂድ አለችው የለም እናቴ፤ እርሱ እዚው ይቆያል መንገዴን ጠራጊ ነው፤ ኑሮው በዚሁ በርሃ ነው፤ ጊዜው ሲደርስ ወደ ዮርዳኖስ ይመጣል ያጠምቀኝማል ያኔ አንድነቴ ሶስትነቴ ይገለጣል አላት፤ ትተውት ተመለሱ።

ከመሞቷ በፊት እናቱ ያሰፋችለትን የግመል ቆዳ አገልድሞ አንቦጣ የሚባል ቅጠልና የበርሃ ማር እየበላ በበርሃ ኖረ 30 ዓመት ከ 6 ወር ሲሆነው፤ “የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ” እያለ ከበርሃ ወጣ ሉቃ 3፥3። "እውነት እላችኋለሁ፥ ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሣም፤" ማቴ 11፥11። ይህ የጌታችን ምስክርነት ነው።

ከበዓሉ በረከት ያሳትፈን።
3.2K views04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 07:39:38
2.2K views04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 06:41:08
"የማያልፍ መከራ ገሃነም ብቻ ነው፤ የማያልፍ ደስታ ክርስቶስ ብቻ ነው። ሰይጣን መከራ እየጨመረ፤ እግዚአብሔርም ክብር እየጨመረ ሩጫው ይቀጥላል።"

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን
3.4K views03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 21:04:39
2.9K views18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 12:02:33
4.1K views09:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 04:56:33 የሰኔ ፲፪ በዐላት ዐርኬ ከነትርጕሙ

፩ ፤ አፎምያ ።

ሰላም ፡ ለአፎምያ ፡ ዘሞዐቶ ፡ ለመስቴማ ።
በቃለ ፡ ትምይንት ፡ ሶበ ፡ ተቃወማ ።
በዛቲ ፡ ዕለት ፡ በከመ ፡ ዐደማ ።
ሥዕሎ ፡ ለሚካኤል ፡ እንዘ ፡ ታነብር ፡ በፍጽማ ።
ውስተ ፡ ዘለዐለም ፡ ዕረፍት ፡ ፈለሰት ፡ እምፃማ ።

ትርጕም፦

ሰላም ለአፎምያ ሰይጣንን ላሸነፈችው፤
በሽንገላ ቢቃወማት አሳፍራ ለላከችው።
ሚካኤል በቀጠራት በዛሬው ቀን በከበረው፣
ሥዕሉን ከደረቷ እንደ ያዘች ሳትነጥለው፣
የዐለምን ከንቱ ድካም በዕረፍቷ አለፈችው።

፪ ፤ ዮስጦስ ።

ሰላም ፡ ለዮስጦስ ፡ ማርቆስ ፡ ዘአጥመቆ ።
ምስለ ፡ አቡሁ ፡ ወእሙ ፡ በአስተላጽቆ ።
ረሢኦ ፡ በንጽሕ ፡ ወበቅድስና ፡ ልሂቆ ።
በዛቲ ፡ ዕለት ፡ ዘአልቦ ፡ ናፍቆ ።
በድሮ ፡ ፈጸመ ፡ ወሠለጠ ፡ ፃሕቆ ።

ትርጕም፦

ሰላም ለዮስጦስ ማርቆስ ላጠመቀው፤
ከአባቱና ከእናቱ ጋር በክርስቶስ ላሳመነው።
ንጽሕና ቅድስናን አስተባብሮ እስከ እርጅናው፣
ሩጫውን አጠናቆ ከድካሙ እፎይ ያለው፣
ሚካኤል በዋለባት በዛሬዋ ልዩ ቀን ነው።

፫ ፤ ቄርሎስ ።

ሰላም ፡ ዕብል ፡ ለቄርሎስ ፡ ሊቅ ።
ጵጵስናሁ ፡ ዘኮነ ፡ በትንቢተ ፡ ብእሲ ፡ ጻድቅ ።
ለዝ ፡ ማእምር ፡ እምስብሐተ ፡ ዐለም ፡ ርሑቅ ።
በውኂዘ ፡ ቃሉ ፡ ለምለሙ ፡ አዕፁቅ ።
ወበትምህርቱ ፡ ነበሩ ፡ ወልህቁ ፡ ደቂቅ ።

ትርጕም፦

ሰላም እላለኹ ለቄርሎስ ለምሁሩ ለኾነው ሊቅ፤
ለጵጵስና ለበቃው ትንቢቱ ደርሶ በአንድ ጻድቅ።
በዚኽ ምሁር ታላቅ ጳጳስ ከውዳሴ ከንቱ የሚርቅ፣
በቃሉ ፈሳሽነት ለመለመ የዛፎች ዐፅቅ፤
በትምህርቱም ተለወጡ ከልሂቅ እስከ ደቂቅ።

፬ ፤ ላሊበላ ።

ሰላም ፡ ለላሊበላ ፡ ሐናፄ ፡ መቅደስ ፡ በጥበብ ።
በዕብን ፡ ይቡስ ፡ እንበለ ፡ መሬት ፡ ርጡብ ።
ነሢኦ ፡ መባሕተ ፡ እምእግዚአብሔር ፡ አብ ።
በዘይትአመር ፡ ሎቱ ፡ ምስፍና ፡ ወምግብ ።
ወዝንቱ ፡ መዐር ፡ ተድላ ፡ ነገሥት ፡ ወሕዝብ ።
በዕለተ ፡ ተወልደ ፡ ተውህቦ ፡ ተዐግተ ፡ በንህብ ።

ትርጕም፦

ሰላም ለላሊበላ መቅደስን የሠራ በጥበብ፤
በደረቅ ድንጋይ ብቻ ሳያስነካ አፈር ርጥብ።
ሀብተ መንግሥቱ ታውቆለት ሹመቱ ከእግዚአብሔር አብ፣
ሀገርን እንዲያስተዳድር ሰው እንዲመራ ያለ ጠብ፣
ምልክት ይኾነው ዘንድ በሥልጣኑ እንዲመግብ፣
ይኼ መዐር የነገሥታት ደስታቸው የኹሉም ሕዝብ፣
ገና ሲወለድ ተሰጠው ተከቦ በነጭ ንብ።

ምንጭ፥ የሰኔ ፲፪ ቀን ስንክሳር፣
ትርጕም፦ ኤፍሬም የኔሰው።
4.8K views01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 04:56:30
እንኳን አደረሳችሁ
3.2K views01:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 13:26:59
4.7K views10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ