Get Mystery Box with random crypto!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @behlateabew
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.08K
የሰርጥ መግለጫ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ
"የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነው እኛ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ ነው።"
ቅዱስ አትናቴዎስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/joinchat/AAAAAESAiVPCib48ZxL1Pw

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-14 09:38:59
642 views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 09:37:00 "ጥበብ ግን መድኃኒታችን ነው።በሥጋው መሥዋዕትነት ያዳነን ፣ በደሙም ፈሳሽነት የተወዳጀን፣ለመንግሥቱም የመረጠን፣ ለዘለዓለሙ።"
ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ
614 viewsedited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 10:12:13 ".... ዐይኖችን በሚፈጥር ፊት ምራቃቸውን ተፉበት። ዳግመኛም ፊቱን በጥፊ መቱት። ኪሩቤል ፊቱን ከማየት የተነሣ በእሳት አክናፍ የሚሠወሩት ያልበደላቸውን እሱን አይሁድ ፊቱን ጸፉት፤ ፊቱ እንደ መንፈስ ቅዱስ፣ እንደ አባቱ ሲሆን በሥጋው ፊቱን ጸፉት፤ ከፊቱ ግርማ የተነሣ ፍጥረቱ ሁሉ የሚርዱለት፣ የሚንቀጠቀጡለት የፈጣሪያቸውን ፊቱን ጸፉት። መዠመሪያ በመመታቱና የሾኽ አክሊል በመሸዳጀቱ ራሱ የቆሰለ ከመሆኑ በላይ የያዘውን በትር ከእጁ ተቀብለው ራሱን መቱት።
ነገር ግን የሾኽ አክሊልን በመቀዳጀቱ በምድራችን ላይ የበቀሉትን አሜከላና እሾኽ እርግማንን አጠፋልን። ራሱንም በዘንግ በመመታቱ የታላቁን እባብ ሰባቱን እራሶቹን ዐሥሩ ቀንዶቹን አጠፋልን።"

         የኅሙስ ድርሳነ ማኅየዊ
539 views07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 08:08:57
"ትህትና ሰይጣን ሊመስለው የማይችለው ብቸኛ ነገር ነው።" ቅዱስ ዮሐንስ ዘክላይማክስ

እንኳን አደረሳችሁ
165 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 07:17:43
"ክርስቶስ ይሁዳን በዚህ ኃላፊነት በሚጠይቅ ቦታ ላይ <ሌባ> የሆነን ሰው ለምን አስቀመጠው?ቢሉ ቤተ ክርስቲያን በዘመኗ ሙዳየ ምጽዋት በሚዘርፉ ሌቦች እንደምትሰቃይ ለማስተማር ነው።ሙዳየ ምጽዋት የመዝረፍ ልምድ ያለበት ሰው ደግሞ ስለ ገንዘብ ሲል ጌታውን አሳልፎ ለመስጠት አያመነታም ።"
ቅዱስ አውግስጢኖስ በዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜ ላይ የተናገረው።
242 views04:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 23:05:03 "የሰይጣንን ኃይል ያደከምክ እውነተኛ ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ በሦስት ሰዓት በጵላጦስ ፊት ለቆሙ እግሮችህ እጅ እየነሳሁ ምስጋና አቀርብልሃለሀ።"
መልክዓ ሕማማት
430 views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 15:58:52 ጌታችን እምላካችን ራርቶ ይቅር ይለን ዘንድ
ልመናችንን ተቀብሎ ይህችን ሳምንት በደህናና
በሰላም ያስፈፅመን ዘንድ የትንሣኤውንም
ብርሃን በፍጹም ደስታ ያሳየን ዘንድ ኃጢኣታችንንም ያስተስርይልን ዘንድ፤ ለሀገራችን ኢትዮጵያም ፍጹም ሰላሙን ይሠጣት ዘንድ ጸልዩ።
695 views12:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 09:45:17 በነጋም ጊዜ ጌታችን ኢየሱስን ይገድሉት ዘንድ የካህናቱ አለቆች ጸሐፊዎችና መምራን ተማከሩ። ከሥር ቤት አውጥተው በጽኑ ገመድና ሰንሰለት አስረው ወደሚፈረድበት አደባባይ ወሰዱት። ከቀያፋ ቤት እስከ ፍርድ አደባባይ ድረስ መቶ ሠላሳ ሦስት ጊዜ በተነጠፈ ድንጊያ ላይ ጎተቱት።
ያለርኅራኄ መቱት። ብዙ በደበደቡትም ጊዜ ፈጽሞ ከምድር ላይም ወደቀ። ዳግመኛም እየደበደቡ ከፊታቸው አቆሙት። እሱ ግን መቆም የማይቻለው ስለሆነ ወደቀ። እየደበደቡም በእውነት ክርስቶስ አንተ እንደ ሆንክ ገልጸህ ንገረን አሉት።

ድርሳነ ማኅየዊ ዘረቡዕ
243 views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 07:07:47 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በስምዖን ዘለምጽ ቤት የአልባስጥሮስ ሽቶ ይዛ መጥታ ከክርስቶስ እግር ሥር ተደፍታ በዕንባዋ ንስሐ ስለገባችው ሴት እንዲህ አለ

ኃጢአተኛዋ ሴት እያለቀሰችና ደረቷን እየመታች እንደዚህ አሰበች

፨ ነፍሴ ሆይ "እንግዲህ ሰው እንደመጣለት በሚናገረው ቃል ሁሉ በፍርድ ዕለት ይፈረድበታል "ላለው ዓለምን ሁሉ ለሚዳኘው ምን ትመልሺለታለሽ?

፨ ነፍሴ ሆይ ከእውነት ፈራጁ ትዕዛዝ ሲመጠብሽ ለቅሶና ጥርስ ማፋጨት ወደ ሚሆንበት ትሉ ወደ ማያንቀላፋበት ውርጩ ወደ ማይሞቅበት እሳቱ ወደ ማይጠፋበት ወደ ጨለማ ዳርቻ ሲወስዱሽ እንዴት ትሆኛለሽ ?

፨ ነፍሴ ሆይ በዚህች ሰዓት የሚረዳሽ ማን ነው ንስሐ በሌለበት ነፍስ ሁሉ በተናቀችና በተጣለች ጣርና ጩኸት ባለበት ጊዜ ማን ይለምንልሻል ?

፨ ነፍሴ ሆይ በዚህ በሚያልፍ ዓለም ነገር ይልቁንም ለኃጢአት ሥራ የሚያፈቅሩሽ የሚጠቅሙሽ ይመስልሻል ?

፨ ዓይኖቼ ሆይ የሞት ጥላ ሲሸፍናችሁ ኩል ይጠቅማችኃልን ? አፌ ሆይ መራራ የሞት ጽዋ ስትጠጪ ይህ በየአይነቱ ምግብ ይጠቅምሻልን? ብዙ ጎረምሶች የደለልኩበት ምላሴ ሆይ ሞት ዝም ሲያሰኝ እንዴት ትሆናለህ ዓለምን ሁሉ ለሚዳኘው ምን ልትመልስለት ትችላለህ ?

፨ በቀለም ዓይነትና በቀለበቶች ታጌጡ የነበራችሁ እጆቼ ሆይ የሞት ልብስ የተንደላቀቅህ ሥጋ ሆይ በክብር ንጉሥና የሥራህን ክፋት ሊሰሙ በቆሙት ስፍር ቁጥር በሌላቸው መንፈሳውያን መላእክት ፊት ራቁትኸን ስትቆም እንዴት ትሆናለህ ?

፨ ነፍሴ ሆይ በዚያ በአስፈሪ አደባባይ የሚረዳሽ አለን እዚያ የትል ምግብ የዚኸ ዓለም ምግብ ይጠቅምሻልን ሁል ጊዜ ወደ ዝሙት የምትሮጡ እግሮቼ ሆይ ሞት ሲያሥራችሁ እንዴት ትሆናላችሁ ልታመልጡ ትፈልጋላችሁ ግን አይቻላችሁም

ነፍሴ ሆይ በዚህ ዓለም ያገኘሽው ድሎት ምን ይጠቅምሻል ?

መዳኛ እንዴት እንደምታገኘ ግን አላወቀችም ሆኖም የሰውን ልብ የሚያውቅ የጴጥሮስን መራራ ለቅሶ የተቀበለ ንስሐውን ተቀብሎ ወደ ክብሩ ያስገባው የቀራጩ ጩኸትም ያልተሠወረው እግዚአብሔር በንጹሕ ልቦና በብሩሕ ሕሊና ወደ እርሱ እንደተመለሰች አወቀ

/ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ዘስሙን ቅድስት/
412 viewsedited  04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 05:04:15
+++"ስለ እኛ የታመመውን ምን አንደበት ይናገረዋል?!"+++

እጅግ ጥልቅ የጸሎት ሕይወት የነበረው፣ አካሉ አልቆ በአጥንቶቹ እስኪቆም ድረስ የሚጾመው ተሐራሚው ቅዱስ አባ ጳጉሚስ ከእለታት በአንዱ ቀን ይህን ተመለከተ፡፡ ቅዱሱ ዓርብ ዓርብ የጌታችንን ሕማማት እያሰበ ከእንባ ጋር አብዝቶ ይሰግድ ነበር፡፡ ከዓይኑ የሚወርደው እንባ ከሰውነቱ ወዝ ጋር እየተቀላቀለ ወደ መሬት በመውረዱ ምክንያት የሚሰግድበትን ቦታ አረጠበው፡፡ አባ ጳኩሚስም ይህን ወደ ጌታው እያመለከተ "ይኸው አንተን አገኝ ብዬ እንዲህ እደክማለሁ" ሲል ተናገረ፡፡ በዚህ ጊዜም መድኃኒታችን ለአባ ጳጉሚስ ተገልጦ "እኔም እንጂ ላንተ ብዬ እንዲህ ሆኜ ተሰቅያለሁ" በማለት በእለተ ዓርብ እንደ ተሰቀለ ሆኖ የተወጋ ጎኑን፣ የፈሰሰ ደሙን አሳየው፡፡ ቅዱሱም የጌታው ሕማም ከሕሊናው በላይ ሆኖበት ወድቆ ምሕረትን ለምኗል፡፡

+++++++++++++

ሕሊናቸው የክርስቶስን ሕማም ከማሰብ አቁሞ የማያውቀው አባ መብዓ ጽዮን መድኃኔዓለምን :- ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ፡፡ ስለ ራሴ ፈጽሞ አለቅስ ዘንድ›› ሲሉ ለመኑት፡፡ ጌታም ‹‹መከራ መስቀሌን ለማየት ትፈቅዳለህን?›› ብሎ ጠየቃቸው። ጻድቁ አባ መባዓ ጽዮንም ‹‹አዎ! አይ ዘንድ እወዳለሁ›› አሉት። ያን ጊዜም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እጆቹና እግሮቹ ተቸንክረው ታየ፣ በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል ደፍቶ ነበር። እንዲህ ሆኖ በሮም አደባባይ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንደታየው ታያቸው። ይህን የመድኃኔዓለም መከራ የተመለከቱ የጻድቁ ዓይኖችም ፈዝዘው እስኪጠፉ ድረስ ትኩስ እንባዎችን ሲያዘንቡ ኖረዋል።

‹‹ኃይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ›› - ‹‹ኃይሌና መጠጊያዬ እርሱ ጌታዬ ነው!››

ዲያቆን አቤል ካሳሁን
selam@dnabel.com
446 views02:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ