Get Mystery Box with random crypto!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @behlateabew
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.08K
የሰርጥ መግለጫ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ
"የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነው እኛ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ ነው።"
ቅዱስ አትናቴዎስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/joinchat/AAAAAESAiVPCib48ZxL1Pw

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-08 12:55:07 ይድረስ ለሶፍያ ሽባባው።

ከሁለት ቀናት በፊት "ይድረስ ለኦርቶዶክስ ጳጳሳትና መምህራን!!" በሚል በገጽሽ የለጠፍሽውን ልጥፍ ከነተሰጠው አስተያየት ጭምር አነበብኩት። በዋናነት ሐሳብሽ "እንደዚህ ናችሁና እንደዛ ብትሆኑ" የሚል ከፍረጃ ተነስቶ በጣም በጥንቃቄና በጥበብ የተጻፈ መሆኑን ጽሑፉ በራሱ ይናገራል። የመልእክትሽ ዋና ዓላማም "ይህንን አድርጉና ወደ ኦርቶዶክስ መልሱን!!" በሚል በመግቢያው ተገልጿል። በአጠቃላይ ጥንቃቄ ለተሞላው በጨዋ ደንብ ለቀረበ ሐሳብሽ አድናቆትና ምስጋና አለኝ።

ሰዎች ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የሚርቁበት ያልሽው ምክንያት ዘርዝረሻል። በስተመጨረሻም ይሁንልኝ ያልሽውን እርማት እንዲህ በማለት" የአለም ሁሉ መድሀኒት ለሆነው ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የሚገባውን ክብርና ምስጋና እውቅና ትስጥ ያኔ ወደ ኦርቶዶክስ ከሚመለሱት ቀዳሚዋ እኔ እሆናለሁ!" ሐሳብሽን ቋጭተሻል።

ይህን ምላሽ የምጽፍልሽ አንድ ታናሽ አገልጋይ የደብረሊባኖስ ገዳም መነኩሴ ስሆን የማገለግለውም በነገረመለኮት ዩኒቨርስቲ የአንጻራዊ ነገረመለኮትና የሥነ ልቡና መምህር ሆኜ ነው።

በቅድሚያ ጽሑፍሽ "ጉድለት" ወይም "ደካማ ጎን" ብሎ በፈረጀው እሳቤ ላይ የሚያጠነጥንና እንደመፍትሒ ጠቁሞ የሚቋጭነው። በዚህም የቤተክርስቲያኒቱን ጠናካራ ጎን ማንሳት አልተፈለገም አሊያም ዕውቅና መስጠትን ሳይሻ በአሉታዊ ጀምሮ በአሉታዊ ይጨርሳል። ከዚህም በመነሳት ለቤተክርስቲያኒቱ ያለው ምልከታ አንድ ጎን ብቻ መሆኑ ነው።

በቅድሚያ ግለሰቦች ፈጠሩት ላልሽው ችግር ቤተክርስቲያኒቱን ተጠያቂ አድርገሽ መፈረጅሽ አግባብ አይደለም። እንዳልሽው ችግሩ ካለ ግለሰቦች በየትኛው ሥፍራ ተመሳሳይ አካሔዶችን ሊከተሉ ይችላሉ። ነገር ግን እንደቤተክርስቲያን ከኃላፊነት አንጻር ተጠያቂ ለማድረግ በቅዱስ ሲኖዶስ ወስና የተቀበለችው ሐሳብ መሆን አለበት።

ለዛሬ በዋናነት መልስ የሚያስፈልገው የተዛባ ምልከታሽን ሰፋ አድርጌ በማየት ልቋጭ። በሐሳብስ በስተመጨረሻ በሰፈርሽው ሐሳብ " የአለም ሁሉ መድሀኒት ለሆነው ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የሚገባውን ክብርና ምስጋና እውቅና ትስጥ ያኔ ወደ ኦርቶዶክስ ከሚመለሱት ቀዳሚዋ እኔ እሆናለሁ!" ብለሻል። በዚህም ቤተክርስቲያኒቱን ከውጪና በጠላት አፍ ከሚነዛባት ሱሑት እሳቤ ተነስተሽ የግምትሽን ሐሳብ ከመሠንዘር በቀር ጠጋ ብለሽ ከውስጥ እንዳላወቅሻት ማሳያ ነው። ሐሳብሽን አንድ በአንድ ማየትና ለተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለሽን የተዛባ ምልከታ የሚያረጋግ ጠውን እሳቤ ላንቺም ስለምትናፍቂያት ቤተክርስቲያን ለማወቅና የተዛባውን ምልከታሽን ለማስተካከል የሚረዳሽን እውነት ባጭሩ ልግለጽ።

ስለኢየሱስ "የሚገባውን ክብርና እውቅና ትስጥ" ብለሻል። ይኽ አስተያየት ለተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አይገባትም። ስለኢየሱስ ክርስቶስ የሚገባውን ክብር በዓለም ላይ ከተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቀር ሌላ የሰጠና የሚሰጥ ያለ አይመስለኝም። እስኪ ከመጠሪያዋ ጀምሮ እንይ። መጠሪያዋ ተዋሕዶ ነው። ይህ ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው በመሆን ለዓለም ቤዛ መሆኑን የዓለም መድኃኒት መሆኑን የሚገልጽ ነው። የተመሠረተችው በእርሱ ነው። ዛሬም ሁለንተናዊ ሕይወቷ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ስሙንም ከዓመት እስከዓመት ሳታቋርጥ በኪዳን በቅዳሴ በሳህታት በማኅሌት እንዲህ እያለች ታመሠግነዋለች።
“ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ
ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብስተ ሕይወት ለዘይበልዖ፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ጽዋዐ መድኀኒት ለዘይሰትዮ፤
ኢየሱስ ክርስቶስ በግዐ መድኀኒት ለዘይሠውዖ ፤
ከመ ይባርኩነ ይፈኑ አርዳኦ፤
ለጸባኢነ ይጽብኦ ወልታሁ ነሢኦ”

ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠራው ስሙ ጣፋጭ ነው፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚበላው የሕይወት እንጀራ ነው፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠጣው የመድኃኒት ጽዋ ነው፤
ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚሠዋው የድኅነት በግ ነው፤
ይባርኩን ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን ይላክ፤
ጋሻውን አንሥቶ የሚጣላንን ይጣላው።"
እያለች በየእለቱ ቤተ ክርቲያን ስሙ መብል መጠጥዋ ፣ክብሯ ፣ መድመቂያዋ ፣ማንነትዋ እና ሁሉ ነገርዋ እርሱ እንደሆነ ትመሰክራለች። የትኛውም ቅዱስ ቢታሠብ የትኛውም ሰማእት ቢዘከር ኢየሱስ ክርስቶስን አክብሮ በመክበሩ ስለአርኣያነቱና በክርስቶስ ኢየሱስ ስላገኘው ሰማያዊ በረከት እንጂ ከክርስቶስ ተነጻጽሮ አይደለም።

ኢየሱስ ክርስቶስ ስትጠራው እንኳ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብላ ነው። በዚህም ጌትነቱን አዳኝነቱን አምላክነቱንና ክርስቶስነቱን ሳትመሰክር ስሙን አትጠራም። ይህም በዚህ ልክ ከብሮ የሚጠራ ሌላ የለምና ክብሩ ከፍ ያለ አቻም ሆነ ተመሳሳይ የሌለው መሆኑን ያሳያል። ካነሳሽው አይቀር ርስቶስ ኢየሱስን እንዴት እንደምታከብር በደንብ ማየት ከፈለግሽ ውሳጣዊ ዓይንሽን መክፈት ይኖርብሻል።

በዓመት የሚከበሩ በዋናነት የሚታወቁ ዘጠኝ ዐበይትና ዘጠኝ ንዑሳን በዓላት አሉ። ከዘጠኙ ዐመታዊ ዐበይት ወይም ዋና በዓላት መካከል 8 በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ተግባር መዘከሪያ ሲሆኑ አንዱ ብቻ ርደተ መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ በስሙ የተሰየመ መታሰቢያ ዕለት ነው። በዘጠኙ ትይዩ ዘጠኝ ንዑሳን በዓላት ሲኖሩ ዘጠኙም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የመስቀል ጉዞ መታሠቢያ ዕለታት ናቸው።

በዓመት ውስጥ 7 አጽዋማት ሲኖሩ 6 ቱ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራ ከአማኞች የሚሰጡ የምላሽ መንፈሳዊ ተግባራት ሲሆኑ አንዱ ስለእመቤታችን ክብር ለበረከት የሚጾም ነው።

በወር ውስጥ ረቡዕ በጌታየ በኢየሱስ ላይ ምክረ አይሁድ ስለተፈጸመበት አርብ ስለተሰቀለ እሑድ ሞትና መቃብርን ድል ነስቶ የተነሳባት የጌታ ቀን ሆና ስትታሠብ ወር በገባ በ06 ስሙ ኢየሱስ ተብሎ የተጠራበት በ10 ነገረ መስቀሉ የሚታሠብበት 27 እርጥብ መስቀል ተሸክሞ መንገላታቱ ና ስቃዩ የሚታሰብበት በ28 እግዚአብሔር ሰውን መታረቁ ክርስቶስ ወይም አማኑኤል በሚለው ስሙ የሚታሰብበት ሲሆን ወር በገባ በ29 ደግሞ ሰው ወደ አምላክነቱ ዙፉን ለመውጣት በመፈለግ የሠራውን ስሕተት፤ እግዚአብሔር ወደ ሰውነት በመውረድ ለማረም በከብት በረት ስለኛ ድህነት የሰው ሥጋ ተዋሕዶ በቤተልሄም በግዕዘ ሕጻናት ያለቀሰበት የልደቱ መታሠቢያ ዕለታት ናቸው። በዐጠቃላይ በወር ውስጥ ለ 17 ቀናት በዋናነት የሚታሠብ ሲሆን ከወር እስከወር ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ተብሎ በኪዳንና በመስዋት ይታሠባል።

በእርግጠኝነት በዚህ ልክ ክርስቶስን የሚያከብር የእምነት ተቋም ቢኖር ብቸኛዋ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ናት። ለመገመት ያህል አንቺ በምትሳተፊበት እምነት ቢታሠብ በወር ከ4 ቀናት እንደማይበልጥና እሱም በትርፍ ቀን ተብሎ እንጂ እንደተዋሕዶ የጌታ ቀን ተብሎ የተሰየመ ሰንበት ኖሮኣችሁ አይመስለኝም።

በሳምንት እንደዚሁ 3 ቀን ረቡዕ አርብና እሑድ ከላይ እንደገለጽኩት በተለየ የሥርዓተ አምልኮ ክንዋኔ ሲታሰብ ከሳምንት እስከሳምንት ኢየሱስ ክርስቶስ ተብሎ በኪዳን ቀስብሐተ ነግህ እና በመስዋእት ይታሠባል።

እነዚህ ሁሉ ተግባራት በስሙ መከናወናቸው ለአምልኮና ከነገረ ድህነት ጋር በጥብቅ የተቆራኘ መሠረት ስላላቸው ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል። “ስለዚህ፥ ወዳጆቼ ሆይ፥ ሁልጊዜ እንደ ታዘዛችሁ፥ በእናንተ ዘንድ በመኖሬ ብቻ ሳይሆን ይልቁን አሁን ስርቅ፥ በፍርሃትና በመንቀጥቀጥ የራሳችሁን መዳን ፈጽሙ፤”
— ፊልጵስዩስ 2፥12
402 views09:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 12:54:57
442 views09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 12:11:56
795 views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-06 07:20:24 ፍካሬ እንስሳት

ከመጋቤ ምሥጢር መሠረት ተሰማ

ክፍል ፩

በጎችና አራዊት/ርግቦችና ጭላት

በጎችና በግ መሰል እንስሳት ሁሉ ማለት የላይ ጥርስ የሌላቸውና ሣር በላ የሆኑ የለቀሙትንና የቃሙትን ምግብ እንደገና ከሆዳቸው ወደ አፋቸው መልሰው የሚያመነዥኩ ወይም የሚያመሰኩ እንስሳት ሁሉ ሌላውን ሥጋዊ ደማዊ ፍጥረት አይተናኰሉም። የሥጋዊውን ሥጋ አይበሉም። የደማዊውንም ደም አይጠጡም። በአጭር አነጋገር የዋሐንና ንጹሐን ናቸው። ባሕርያቸው ቢመረመር እንከን አይገኝባቸውም።

ሁሉም በበግ ውክልና ሥር ተጠቃለው በግ ተብለው የሚጠሩበት የአጠራር መልክ አላቸው። ከሁሉም እንስሳት በላይ በግ የዋህ ስለሆነ በየዋህነቱ ለእንስሳት በኵር ሆኖ ሁሉም በእርሱ ይታሰባሉ። በጥንቱም ዘመን ሌሎችም እንስሳት ለመሥዋዕትነት የሚፈለጉ ሆኖ ሳለ በቅድምና የሚፈለገውና የሚጠራው በግ ነበር። የታጋሽነቱም መረጃ በግ ሲታረድና ለጉዳት ሲዳረግ እንደ ፍየል የጩኸት ድምፅ አያሰማም። አምርሮ ከበረረም አይመለስም።

ከዚህም የተነሣ በትዕግሥቱና በየዋህነቱ ከበረረና ከደነበረ ወደ ኋላ የማይዞርና በቀጥታ ወደፊት የሚበር ፣ ከአውሬ ለመዳን የሚጥር ፣ እረኛውን አፍቃሪ በመሆኑ የበላውንም እንደገና በማመንዠኩ ሁኔታዎችንና ነገሮችን የማውጣትና የማውረድ ፣ የማሰላሰልና የማመዛዘን ችሎታ ያላቸው የጻድቃንና የቅዱሳን ሕዝበ ክርስቲያን ፤ “ወልድ ዋሕድ” የሚሉ ምዕመናን ምሳሌ ሆኗል።

ስለ በጎችና ጻድቃን ተመሳሳይነት ብዙ የሚያስተቹ ምሳሌዎች ቢኖሩም እንተወውና እንዲያው በጥቂቱ ጻድቃን መከራ የሚታገሡና ከዓለም መዘዘኛ ጣጣ ለማምለጥ ፊታቸውን ወደ ፈጣሪያቸው መልሰው ከሮጡ ወደ ኋላ ስለማይመለሱ ተመሳስለዋል ብለን እናሳርፍ።

ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ወደ ፊት እንዲገሠግሡ የሚያደርጋቸውም ሁኔታ፦

1ኛ. “ማንም ዕርፍ በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም።”ሉቃ. 9፥62

2ኛ. “በዚያም ቀን በሰገነት ያለ በቤቱ ያለውን ዕቃ ሊወስድ አይውረድ፥ እንዲሁም በእርሻ ያለ ወደ ኋላው አይመለስ። የሎጥን ሚስት አስቡአት።” ሉቃ. 17፥31 – 23  የሚለው የጌታችን የሕይወተ ኵሉ የኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ነው።

ርግቦችን በሚመለከት 

ርግቦች ተንኮል የሌለባቸውን ገሮቹንና የዋሆቹን አእዋፍ ሁሉ ይወክላሉ። በጎች በእንስሳት መሃል ያላቸውን ሥፍራ ሁሉ ርግቦች በደጋግ ወፎች መሃል አላቸው። 

- ርግቦች የሰላም መልእክተኞች ናቸው። ሰላምን የማብሠር የማረጋገጥ ምሳሌዎች ናቸው። (ዘፍ. 8፥8-12) 

- የውበትና የሥነ ምግባር ተምሳሌቶች ናቸው። (መኃ. 1፥15)

- የሐዘንም ምሳሌዎች ናቸው። (ኢሳ 59፥11) 

- የገርነትና የመንፈስ ቅዱስም ምሳሌዎች ናቸው። (ማቴ.3፥16 , 10፥16)

ጻድቃንም ማለት ሥላሴን “እኩል ትክክል ናቸው ፤ ሦስት አካላት አንድ መለኮት ነው። ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል እግዚአብሔር ቃል ያለ ዘርዐ ብእሲ የቅድስት ድንግል እናቱን ማኅተመ ድንግልና ሳይፈታና ሳይለውጥ በድንግልና ተጸንሶ በድንግልና ተወልዷል። ባሕርየ መለኮቱን ከባሕርየ ትስብእቱ አዋሕዷል። ፍጹም አምላክ ወሰብእ ነው። ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በአንዲት ክብርና ሥልጣን ይገዛል።

ስለኛ ተወልዷል፤ ተጠምቋል፤ ጾሟል፤ ወንጌልን ዞሮ አስተምሯል። ለቅዱሳኑ የክህነት ሥልጣንን ሰጥቷል። በመለኮቱ ሕያው ሲሆን በሥጋው ሞቶ ተቀብሯል። በሦስተኛውም ቀን መቃብሩ እንደተዘጋ መቃብር ክፈቱልኝ መግነዝ ፍቱልኝ ሳይል አሥነሽ ሳይሻና ሳይፈልግ ባባቱና በራሱ በመንፈስ ቅዱስም ኃይልና ሥልጣን ተነሥቷል። ከተነሣም በኋላ አርባ ቀን መጽሐፈ ኪዳንን አስተምሯል።

በአርባኛውም ቀን ቅዱሳን የሆኑ መቶ ሃያ ቤተሰቡ እያዩት እያናገራቸውና እየባረካቸው ቅዱሳን መላእክት አጅበውት መላእክትና እረኞች አጅበውት ቀድሞ በልደቱ እየተደሰቱ እንደተነጋገሩና እንደዘመሩ ሁሉ በዕርገቱም ሐዋርያቱና ቤተሰቡ (መቶ ሃያው ሁሉ) እየተነጋገሩና እየዘመሩ ቤተሰቡ ሸኝተውት መላእክት አጅበውት ቅዱስ መንፈሱን እንደሚልክላቸው ቃልኪዳን ሰጥቷቸው ዐርጓል።

በቃልኪዳኑም መሠት መንፈስ ቅዱስን በተነሣ በሃምሳኛው ቀን ባረገ ባሥረኛው ቀን ልኮላቸዋል። መንፈስ ቅዱስም ቅዱሳኑን በልዩ ልዩ  ቋንቋ አናግሯቸዋል። እነሱም እያስተማሩ እያጠመቁ ዲያቆናትና ቀሳውስትን ፣ ጳጳሳትን እየሾሙ ሲያስተምሩ ኖረው የታዘዙትን ከፈጸሙና አደራቸውን ከጠበቁ በኋላ በልዩ ልዩ አሟሟት አርፈዋል (ሞተዋል)። የአማላጅነትንና የፈራጅነትን ክብርና ሥልጣን በቃልኪዳን ስለሰጣቸው ያማልዳሉ። በምልጃቸው ያድናሉ። በነፍስ ሕያዋን ስለሆኑ አሁንም እስከ ዕለተ ምጽአት በዐፀደ ነፍስ ሆነው ያማልዳሉ።

ከእነሱም አስቀድሞ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ በነበሩ ቅዱሳን አበውና ነቢያት ቅዱሳንና ቅዱሳት ሁሉ ያማልዳሉ። የሰውና የፍጥረት ሁሉ ረዳቶችና ጠባቂዎች ቅዱሳን መላእክት ያማልዳሉ። ከሐዋርያትም በኋላ የተነሡ ቅዱሳንና ጻድቃን ሰማዕታት ያማልዳሉ። ከእነዚህም ሁሉ በላይ መልእልተ ፍጡራን የሆነችው ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ሞታ ነበር ተነሥታለች፤ ዐርጋለች፤ በአብና በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ቀኝ ተቀምጣለች። 

ቤዛዊተ ዓለም የምሕረት አማላጅ ከጭንቅ የምታድን የሰዎችና የመላእክት ፤እመቤታችን ናት።” ብለው የሚያምኑ ምዕመናን ሕዝበ ክርስቲያን ሁሉ በበጎችና በርግቦች ይመሰላሉ።እኛም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልጆች ሁሉ እነርሱን እንመስላለን።

ክፍል 2 ይቀጥላል....
295 viewsedited  04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 17:24:21
#"ሙሽሪት ቤተ ክርስቲያን ክርሰቶስን እንዲህ እያለች ታመሰግነዋለች የተተውኩና የተጣልኩ ሁኜ ሳለ አብርተህልኛል፤ ስለ እኔ ብለህ የርኩሳንን ምራቅ ታግሰሃል፤ ከትንሳኤህ ህይወት አገኘሁ፤ ፀጋንም አገኘሁ፤ልጆቼም ወደ እቅፌ ገቡ፤ በመስቀልህ አበራህልኝ፤ በመስቀልህም ዓለምን ሁሉ አዳንህ"
ቅዱስ ያሬድ
96 views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 09:54:12 "መድኀኔዓለም ክርስቶስ ሆይ
ክቡዱንና ግዙፉን ዕፀ መስቀል በመሸከም ምንኛ ድካምንና መከራን ልትታገስ ቻልክ። ለዚህ ረቂቅ ትህትናህ አንክሮ ይገባል።"

መልክዐ መድኀኔዓለም
439 views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 09:34:52 "ሕይወት መድኃኒት በሆነች ሕማሙ የዘላለም ድኅነትን ለዓለም ሰጠ።"

ግብረ ሕማማት
452 views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 06:09:04
ጌታችን ለወንበዴው «በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ» የሚል ልመና «እውነት እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ» ብሎ ወዲያውኑ መልሰ ሰጠ። በኃጢአተኞች ሰዎች ፊት የመሰከረለትን ወንበዴ በመላእክት ፊት እመሰክርልሃለሁ አለው።
በግራ ያለው ወንበዴ ሲሰድበው ዞሮ በቁጣ ሳያየው በትዕግሥት ሰምቶ ዝም ያለው ጌታ የቀኙ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ፣ ወደ እርሱ ዞሮ መለሰለት። «ከቁጣ የራቀ ምሕረቱ የበዛው» አምላክ ክፉ ሥራችንን ለማሰብ ሲዘገይ ማረኝ ስንለው ግን ለመማር ይፈጥናል።
«የራበው ሰው ለምግብ የጠማው ሰው ለመጠጥ እንደሚቸኩል ክርስቶስ ይቅር ለማለት ይቸኩላል»
ስለዚህ ወደ ወንበዴው ዞሮ « እውነት እልሃለሁ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ» ያለው ፤ ይህን ምሕረት ተስፋ አድርገን
«ጌታ ሆይ ወደ ቀኙ ወንበዴ ዘንበል ባለው ራስህ አጋንንት በኃጢያት በትር የመቱትን ራሴን ቀና አድርግልኝ» እያልን እንጸልያለን።

ከዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ሕማማት መጽሐፍ
ገጽ 354 የተቀነጨበ
655 views03:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-05 06:06:01 "የራበው ሰው ለምግብ የጠማው ሰው ለመጠጥ እንደሚቸኩል ክርስቶስ ይቅር ለማለት ይቸኩላል ።"

ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
533 views03:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 16:22:54
የመቄዶንያ የማህበራዊ ድረገጽ ላይክና ሼር ያድርጉ!!!

ፌስቡክ

https://www.facebook.com/100082057428173/posts/pfbid0LDHn2SwMU5qJvcqL5yTGFvFBhkjoH69NC1VQVPrtfEfRJqGvm6PPbcYQLAw55Tykl/?app=fbl

ተሌግራም
https://t.me/Mekedonia7979
376 views13:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ