Get Mystery Box with random crypto!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የቴሌግራም ቻናል አርማ behlateabew — ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
የሰርጥ አድራሻ: @behlateabew
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.08K
የሰርጥ መግለጫ

የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ
"የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነው እኛ አማልክት ዘበጸጋ እንሆን ዘንድ ነው።"
ቅዱስ አትናቴዎስ
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆
https://t.me/joinchat/AAAAAESAiVPCib48ZxL1Pw

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2023-03-10 16:57:08 "እኔን በጣም እያሳሰበኝ ያለው እና አጥብቄ የምጸልይበት ጉዳይ ቢኖር አጠቃላይ የሚዲያ ጉዳይ፣ ይዘቱ እና በአማኞች ነፍስ ላይ የሚያሳድረው ተጽእኖ ነው። ምክንያቱም ዲያብሎስ አምላክ ላይ በትክክል ውጊያ የከፈተበት ቦታ ሚዲያ ነውና።"

/16ኛው የሩሲያ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ፖፕ ቄርሎስ/

ፖፕ ቄርሎስ በኮሚኒዝም ዘመን እና ከእርሱም በኋላ ከፍተኛ መቀለጃ እና መሳለቂያ ሆና የነበረችውን ቤተ ክርስቲያናቸው ወደ ከፍታ ለመውሰድ እና የጠፉ ልጆቿን መልሳ ለመሰብሰብ እንድትችል በቤተ ክህነታቸው ላይ ከፍተኛ የሆነ የመዋቅር እና የአሠራር ለውጥ በማምጣት ይታወቃሉ። ከዚህ ሁሉ በላይ በዓለም ጭምር የሚደነቁበት ግን በሚዲያ አጠቃቀም ላይ ባመጡት አዲስ ስትራቴጂ ነው። መዋቅር እና አሠራር ከመዘርጋታቸውም በፊት ስለዚህ ሁኔታ ታላላቅ ንግግሮችን አድርገው ነበር። ከላይ የጠቀስኩትም የዚሁ ንግግራቸው አካል ነበር።
ፖፕ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያናቸው የትልልቅ ሚዲያ ተቋማት ባለቤት መሆን ያለባት መሆኑንም ሲያስረዱ እንዲህ ብለው ነበር።

"ዐለማዊ ጋዜጠኞች ትንሣኤንና ልደትን ጠብቀው ኦርቶዶክስን የሚጠሩበት ወቅት አልፏል። ዛሬ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ በየጋዜጣው ገጾች ፣ በሬዴዮኖች፣ በቴሌቪዥን ፕሮግራሞች፣ በየኢንተርኔቱም ይወጣል። ልክ ነው ይህ ደስ ያሰኛል። ሆኖም ትልቅ ኃላፊነት እንደሚጠብቀን እና ለሚዲዮች በመተባበር ስለራሳችን ለመናገር በንቃት መሳተፍ እንዳለብን የሚጣራ ነው። ገለልተኛ ሆነን ከቆምን ጋዜጠኞች ስለቤተ ክርስቲያናችን እና ስለ እምነታችን ራሳቸው የመሰላቸውን ምስል ፈጥረው ለማኅበረሰቡ ያሰራጫሉ። ያለ እኛ ተሳትፎ ከሆነ ይህ እነርሱ የሚፈጥሩት ምስል አንድ ገጽ ይሆናል፣ ከባሰም የተጣመመ እና ሐሰተኛ ሊሆን ይችላል"

እኒህ አባት ሌላም ጊዜ "እኛ ስለቤተ ክርስቲያናችን እና ስለ እምነታችን ትክክለኛውን እና ተገቢውን የማንናገር ከሆነ ሌሎች ስለ እኛ የሚናገሩት እውነት ተደርጎ ይወሰዳል" ብለዋል።

በዚህ ዘመን ስለ ሚዲያ አስፈላጊነት ማስረዳት የሚያስፈልግ ላይሆን ይችላል። ልማታችንም ጥፋታችንም ከእርሱ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ መሆኑ ግልጽ ከሆነ ከራርሟልና።

የእኛ ቤተ ክርስቲያንም ዘግይታም ቢሆን የሚዲያውን ዳዴ ጀምራዋለች። ይህ ውጤታማ የሚሆነውና እንደሌሎቹ ለላቀ ግብ የሚደርሰው ግን ሁላችንም የድርሻችን ስንወጣ ነው።

አንድ መክሊቱን እንደቀበራት ክፉ አገልጋይ እንዳንወቀስ ከፈለግን ያችኑ መክሊት ለተገቢው አካል እንስጥ። ጌታ ክፉውን ባሪያ "ካልዘራህበት የምታጭድ ካልበተንህበት የምትሰበስብ መሆንህን ስለማውቅ" (በፈለግኸው አድረህ ትሠራለህ ብዬ ነው) ብዬ ነው ብሎ ሲያመካኝ እንደዚያ ብለህ ካሰብክ ለዚያ አድሮበት ይሠራል ላልከው ሰው ለምን አልሰጠኸውም ሲል የፈረደበት እንዳይደርስብን የሚሠሩትን እድናግዝ በታላቅ ትሕትና እጠይቃለሁ።

ወዳጄ ገንዘብ ጥየቃው በዛ፣ ሰሞኑን ለቦረና እና ለመቄዶንያ፣ ለተፈናቃዮች እና ለችግረኞች፣ ለአጥቢያዬ ሕንፃ ግንባታ እና ነፍስ አባቴ ለጠየቀኝ፣ ለገዳም እና ... አሁን ደግሞ ለሚዲያ፤ አልበዛም ወይ እያልክ አትቁጠር አደራህን። ይልቁንም የምሰጠው አታሳጣኝ ፣ የሚለመንላቸው ውስጥ ከመሆን አድነኝ እያልህ የተቻለህን ብቻ አድርግ እንጂ እንዳታማርር። እንኳን እኛ እርሱ ከሰጠን ላይ የምንሰጠው ይቅርና ስለምንጠይቀው እና ስለሚሰጠን ብቻ ሳይሆን ሳንጠይቀውም ስለሚያደርግልን ነገር እግዚአብሔርም እኛን አላማረረምና ሳንማረር የተቻለንን እናድርግ።
889 views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 16:57:05
808 views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 11:23:24 "ድንግል ሆይ እኔ ግን ልጅሽን በማምለክ በባሕርይ አባቱም በአብ በባሕርይ ሕይወቱም በመንፈስ ቅዱስ አምኜ ደስ እሰኛለሁ ለሦስትነቱ አንድ ስግደት እየሰገድሁ እመካበታለሁ እንዲህ ስል፡፡ አምላኬ ነው አመሰግነዋለሁ ያባቶቼም አምላክ ነው አከብረዋለሁ አገነዋለሁ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ፡፡ እግዚአብሔር ፀብ ክርክርን ይሰብራል፡፡ ስሙም እግዚአብሔር ነው፡፡ ደግሞ እንዲህእላለሁ (ዘፀአት ፲፭፣ ፪፣ ፫) እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማነው፡፡ ይህንንም የመለኮት ሰይፍ ተቀብዬ የሰይጣንን ራሱን እቆርጠዋለሁ፡፡ ይህንንም የሃይማኖት በትር ተመርኩዤ የእባቡን (የዲያብሎስን) ራሱን እቀጠቅጠዋለሁ፡፡ የምስጋናውንም ጽዋ ከጽርሐ አርአያም ቀድቼ ከቤትሽ አፈሳለሁ፡፡ ከትንቢት ቃል ጋራ እንዲህ እላለሁ፡፡ ከሞት ደጅ ከፍ ከፍ የሚያደርገኝ በጽዮን ልጅ ደጅ ምስጋናውን ሁሉ እናገር ዘንድ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ እላለሁ፡፡ በጽዮን ምስጋና ላንተ ይገባል በኢየሩሳሌም ጸሎት ላንተ ነው፡፡"

(አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - አርጋኖን)
598 views08:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 09:08:18
"እግዚአብሔር ወሰን በሌለው ፍቅሩ ሰውን ይወደዋል፥ስለወደደውም በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረው፡፡"
ቅዱስ ሄሬኔዎስ
516 viewsedited  06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 10:00:46
824 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 08:55:02 ‹‹በከመ ይቤ እግዚእነ በነቢይ ጊሥዋ ለቤተ ክርስቲያን እስመ ኵሉ ዘጌሠ ኀቤሃ ተአሥዮ ፍሥሐ።››

"ጌታችን በነቢዩ አድሮ እንደተናገረው ቤተ ክርስቲያንን ገሥግሡባት፤ ማልዱባት ወደ እርሷ የገሠገሠውን ደስታ ትሰጠዋለችና"
       ቅዱስ ያሬድ
850 views05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 23:47:41
ለመቄዶንያ በጎፈንድሚ አግዙ
https://gofund.me/216b39ce


ኮሜዲያን እሸቱ በአሁኑ ሰዓት ለመቄዶኒያ የ1 ሚልየን ዶላር ዘመቻ ይዟል። በቀጥታ ስርጭትም ከጓዶቹ ጋር እየታገለ ነው።

በ7979 አጭር ቁጥር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ላይ ሁላችንም እያዋጣን አቅሜ ደካሞችን እርዳ
213 viewsedited  20:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-05 20:28:55
475 views17:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 18:47:56 " በመከራችን ሁሉ እግዚአብሔር የትዕግስት ፍፃሜ ይሰጠን ዘንድ ስለነፍሳችን ትዕግስት እንማልዳለን። "
በእንተ ቅድሳት
409 views15:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 11:47:44
"እስመ ገቢረ ተአምራት ወመንክራት ኢይክል አድኅኖ እምኩነኔ ገሃነም፦

ተአምራትና መንክራት ማድረግ ከገሃነም ፍርድ አያድንም።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
268 views08:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ