Get Mystery Box with random crypto!

ወገኖች! Apostolic Succession (ሐዋርያዊ ሰንሰለትን) በመጠበቅ ተወዳዳሪ የሌላት ኦርቶ | ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

ወገኖች! Apostolic Succession (ሐዋርያዊ ሰንሰለትን) በመጠበቅ ተወዳዳሪ የሌላት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 2000 ዓመታት በተቀደሰው ትውፊት (Holy Tradition) አማካኝነት ቅዱሳት መጻሕፍትንና ከእነርሱ የሚመነጨውን ርቱዕ (የቀና) አስተምህሮ ያስረከበችን፣ ማንም የመሰለውን መላምት እያመጣ ከቀጥተኛው (ኦርቶዶክሳዊ) መንገድ እንዳይወጣ አጥር ሆነው የሚጠብቁ Holy Canons (ቅዱሳት ቀኖናት) ስላሏት ነው፡፡ ይህን ለመረዳት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለውን የአምልኮ ውበት እና ሥርዓት፣ Protestantism ውስጥ ካለው ቀውስ (chaos/anarchy) ጋር በማነጻጸር መረዳት ይቻላል፡፡ ኢየሱስ ስላልን ተወገዝን ተባረርን የሚሉ አካላት ይህንን በመናድ ቤተክርስቲያኒቱን ማተረማመስ የሚሹ አካላት ናቸው።

በጥራዝ ነጠቅ አካሔድና አነጋገር፣ በዘመናት ተፈትኖ ያለፈውንና በምድር ላይ ሆነን ሰማያዊ ሐሴትን እንድንለማመድ የሚያደርገንን ኦርቶዶክሳዊ ሥርዓተ አምልኮ ሸርሽረን እንደ አንዳንድ ሥርዓት እንደሌላቸው ቤተእምነቶች ወደ ሥርዓት አልበኝነት እንዳንገባ የሚያደርጉ ስሑት አስተምህሮዎችንና አካሔዶችን ታርማለች ትመክራለች ትገስጻለች አልሰማም ካለ ሌላውን እንዳይበክልና መለያየት እንዳይፈጠር አውግዛ ትለያለች። በዚህ ስህተታቸው ሲወገዙ ኢየሱስ ስላልን ተወገዝን ብለው መሸሸጊያ ፍለጋ ሊያሳብቡ ይችላሉ። ኢየሱስ ስላለ የሚባረርና የሚወገዝ ቢኖር ኖሮ አንድም ቀዳሽም ሆነ ኪዳን አድራሽ ካህን ባልተገኘ ነበር። ውሸት ነውና ዝም ብለው ለሚዋሹ ዋሾዎች ስንሰማ ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡

ከአባ ጌዴዎን ዘደብረሊባኖስ ለሶፍያ ሽባባውና መሰል ምልከታ ላላቸው ሁሉ ተጻፈ 29/07/2015 ዓም