Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-01-04 06:39:37 በእውነት በቅድስና በምሳሌነት በመሰጠት በትጋት ደቀመዝሙር በማፍራት እናገልግል ።

በዚህ ዘመን ያለው ግርግር በእጅጉ አስፈሪ ነው። አማኙ ማህበረሰብ አብሮ ያለው ትውልድ መልክ መለየት የቻለ አይመስልም ። ትውልዱ የበረከት ፣ የተዓምራት ፣ የኮንፍራንስና የሜጋ ቸርቾች አሳደጅ ሆኖአል። አማኙ የተያዘበት የሚማርበት አባል የሆነበት ቤ/ክ የለውም ። ዘመኑ ሁሉም አባል የሁሉም ቤተ ክርስቲያን ሁሉም ቤተ ክርስቲያን የሁሉም አባል ነው የተባለ የሚመስልበት ነው።
ጋጋታው የተአምራት እና በረከት ተኮር እንጂ ህይወት ተኮር አይደለም።

ብዙዎች ወደ ጌታ ከመጡ በኃላ በቤ/ክርስቲያን ተገኝት በየሳምንቱ ማምለክ እንጂ ጥሪው ደቀ መዝሙር የመሆን ጥሪ እንደሆነ የገባቸው ጥቂቶች ናቸው፡፡ በመሆኑም አንድ አማኝ ጌታን የግል አዳኙ አድርጎ በሚቀበልበት ጊዜ የጌታ ደቀ መዝሙር ሊሆን ጭምር መጠራቱን ማወቅ ይኖርበታል፡፡

ደቀ መዝሙር ማለት ምን ማለት ነው ?
ደቀ መዝሙር ማለት የጌታ ተከታይ መሆን ማለት ሲሆን ደቀ መዝሙርነት የርሱ ተማሪ ሆኖ ጌታን ለመምሰል በጌታ ህይወት የመቅረፅ ሂደት እንጂ በቤተክርስቲያን በአምልኮ፣ በዝማሬ በአገልግሎት ሥም ግርግር ማብዛት አይደለም።፡፡ (ማቴ 28፡-18-21 ማቴ 4፡-19 ማቴ 11፡-28)
ዓላማውም:-
1ኛ,ጌታን ማወቅ ! በጌታ ህይወት መቅረፅ !
2ኛ, ጌታን መስሎ በእርሱ ህይወት መገኘት !
3ኛ, ያወቁት ጌታ መግለጥ /የጌታ ህያው ምስክር መሆን/ነው !
ይህ እውን ሲሆን የክርስቶስን ህይወት ለሌሎች የማካፈል አገልግሎት ይበዛልናል ።ጌታ እርሱን የሚከተሉትን ደቀ መዛሙርት 24 ሰዓት በህይወታቸው፤ በኑሮአቸው በአገልግሎታቸው የሚከተላቸው በእርሱ ህይወት ሊቀርፃቸው ነው፡፡ እርሱን እንዲመስሉ እርሱ ተልዕኮውን ፈጽሞ ሲሄድ በርሱ ሕይወት እንዲገኙ ነው ።

ጌታ ደቀመዛሙርትን የሚከታተልበት ዓላማ በሕይወታቸው የለውጥ ሂደትን ማካሄድ ነው። ስለዚህም ክርስቶስን እከታተላለሁ የሚል ሰው በእውቀቱ፤በሕይወቱ፤ በኑሮው የለውጥ ሂደት መካሄዱን ማረጋገጥ አለበት፡፡
አለበለዚያ የቤተክርስቲያን ተሳታፊ አባል እንጂ ደቀመዝሙር ሊሆን አይችልም። የደቀ መዝሙር ሕይወት እውቀቱ ከተግባራዊ ሕይወቱ ጋር የተጣጣመለትና ያወቀውን የሚኖር የኖረውንም የሚገልጥ ነው ። ዛሬ ላይ የክርስቶስ የሕይወት መዓዛ ሽታው ከቤ/ክ ለምን ጠፋ ብለው ጠይቀው ያውቃሉ ? እውነታው ደቀ መዝሙር ያልሆኑ አገልጋዮች ፣ ደቀ መዝሙር ያልሆኑ መሪዎች፣ደቀ መዝሙር ያልሆኑ ዘማሪዎች መድረኩን ሞሉት ። ደቀመዝሙር በፊቱ ጌታን ሞዴል አድርጎ :-
1.ደቀ መዝሙር ከጌታው የሚማርና በመንፈሳዊ እውቀት የሚያድግ ነው ! ማደጉ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ
2. ደቀ መዝሙር ወደ ትክክለኛ የመንፈሳዊ ሕይወት የእድገት አቅጣጫ የገባ ነው ! በቃሉ ሥር ሰዶ ለማደግ
3. ደቀ መዝሙር ለዕድገት የሚያስፈልጉ ነገሮችን እንደሚሟሉለት ከጌታ ጋር የጠበቀ ሕብረት ያደረጋል ! የወይኑ ግንድና ቅርንጫፉ ያላቸውን አንድነት ያህል !
4. በዘመኑ ሁሉ የጌታ ተማሪ ሆኖ በእርሱ ሕይወት በመቅረፅ ወደ ሙላቱ ልክ ለመድረስ ዘመኑን ሁሉ የሚገሰግስ ነው
5. ግቡም የጌታ ሕይወት በሙላት መጎናፀፍ ነው !ዘወትር ቃሉ ከሕይወቱ ጋር እንዲዋሃድ ይተጋል !
6. ደቀ መዝሙር እንደጌታው የሚሆን የሚኖረውን የሚናገር የሚናገረውን የሚናገር ነው !

ስለዚህም ደቀ መዝሙር
1. ዘወትር የቃሉን ወተት የሚመኝ ነው !
2. የፅድቅና የእውነት ርሀብ ያለበት ነው !
3. በመንፈስ ቅዱሰ የሚመራ ለቃሉም እውነት የተገዛ ነው !
4. ከምንም በፊት ለእግዚአብሔር ቅድሚያ የሚሰጥና ከእርሱ ጋር የጠበቀ የፀሎት ህብረት ያለው ነው !
5. በተሰጠ አዲስ ሕይወት በብስለት ለማደግ ዕለት ዕለት የሚተጋ ነው !

6.የጌታ ደቀ መዝሙር መታወቂያው ፍቅር ነው ዮሐ 13፡-35 ዮሐ 15፡-10 የጌታ *የጌታን አላማ አላማው ያደረገ ነው !
7.ደቀ መዝሙር መስዋዕትነት ለመክፈል የቆረጠ የተዘጋጀ ሕይወት ያለው ነው !
8.ደቀ መዝሙር መስቀሉን ዕለት ዕለት ተሸክሞ ጌታን ለመከተል የቆረጠ ነው! (ሉቃ 9፡23)
9.ደቀ መዝሙር ለጌታው እስከ ሞት ድረስ የታመነ ነው !

እስቲ እንጠያየቅ !

1ኛ, ዛሬ ቤተክርስቲያን የራሷ አባላት እንጂ እውነተኛ የጌታ ደቀመዛሙርት መፍለቂያ ናትን ?
2ኛ, ቤተ ክርስቲያን ቆም ብላ እራሷን ማየት አለባት ጌታ የሚደስትባት የአባላቶቿን ብዛት ስታሳየው ወይስ እውነተኛ ደቀመዝሙር በማፍራቷ ?
3. የጌታን ሞዴልነት የተከተለ እወውነተኛ አገልግሎት ለመፈፀም በእያንዳንዱ አማኝ
ሕይወት የለውጥ ሂደት የማካሄድ ከገልግሎት ሊኖረን አይገባምን ?

የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን ችግር ምንጩ
እውነትኛ ደቀመዝሙር ያልሆኑ አባላት በቤተክርስቲያን መከማቸታቸውና መሪ አገልጋይ ዲያቆን ዘማሪ አብዛኛው ማለት
በሚቻልበት ሁኔታ ከአባላቶቿ የተመለመሉ እንጂ ከእውነተኛ ደቀመዝሙርነት የወጡ አለመሆናቸው ነው ።

ምን እናድርግ ?
በቅድሚያ እኛ እውነተኛ የጌታ ደቀ መዝሙር መሆናችንን እናረጋግጥ ።
ከዚያም የቤ/ክ አባላትን እውነተኛ
ደቀመዝሙር እናድርግ ።

በሕዝቡ ሕይወት ጌታ እንዲነግስ እንዲገለጥ እንዲከብር እናገልግል
እንጂ እኛ አንንገስ ፣ ጌታን እናክብር እንጂ እኛ አንክበር ፣ ሕዝቡን የከበረውን መንፈሳዊ ሕይወት እንዲጎናጸፍ እንጂ ለጥቅም አናገልግል ። በእውነት በቅድስና በምሳሌነት በመሰጠት በትጋት ብዙ ፍሬ በማፍራት ጌታን የሚያስደስት አገልግሎት እናገልግል ። ተባረኩልኝ !
2 views03:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 06:17:31 ራስን ማጥፋት

ባለንበት ወቅት ከዛም ከዚም ሰዎች ራሳቸውን አጠፉ ሞተ(ች) ይሰማል ። እስኪ በጥቂቱ ለግንዛቤ ቢጠቅም ከመጽሐፍ ቅዱስም ከጥናቶችም በሚዛናዊነት በጥቂቱ እንድንመለከት አሰብኩ።

መጽሐፍ ቅዱስ ራሳቸውን ያጠፉ ስድስት ሰዎችን ይጠቅሳል፤አቤሜሌክ ( መሳፍንት 9፤54)፤ ሳዖል (1ኛ ሳሙኤል 31፤4)፤ የሳዖል ጋሻ ጃግሬ (1ኛ ሳሙኤል 31፤4-6)፤ አኪጦፌል (2ኛ ሳሙኤል 17፤23)፤ ዘምሪ (1ኛ ነገሥት 16፤18) እና ይሁዳ (ማቴዎስ 27፤5)፡፡ አምስቱ ሰዎች ክፉዎች፤ በኃጥአት የተሞሉ ነበሩ፤ (የሳዖልን ጋሻ ጃግሬ ግን ስለ ባህርይው በቂ ነገር አልተገለጸም)፡፡ አንዳንድ ሰዎች የሳምሶንን ድርጊት ራስን የማጥፋት ምሳሌ ያደርጉታል (መሳፍንት 16፤26-31) ነገር ግን የሳምሶን ግቡ የነበረው ራሱን ሳይሆን ፍልስጥኤማውያንን መግደል ነበር፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ ራስን ማጥፋት (መግደልን) ነፍስ ከመግደል ጋር እኩል ያደርገዋል።አንድ ሰው መቼ እና እንዴት መሞት እንዳለበት(ነፍሱ ከስጋው መለየት እንዳለባት) የሚወስነው ሰውን በራሱ መልክ እና አምሳል የፈጠረው እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ መሠረት እንድ ሰው ራሱን በማጥፋት ወደ መንግሥተ-ሰማይ የመግባት ጊዜውን ማፋጠን ወይም ለመግባት እድል ማግኘት አይችልም። ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ ሰው ወደ መንግስተ ሰማይ የሚገባበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ ያስቀምጣል፡፡ አምኛለሁ ባይ ስመ አማኝም ሆነ ያላመነ ሰው ራሱን ቢያጠፋ ወደ ገሃነም የሚገባበትን ጉዞ አፈጠነ እንጂ ምንም የሚጠቀመው ነገር የለም።

እግዚአብሔር የማንንም ሰው ጥፋት አይወድም ክርስቲያን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ይከተላል በመሆኑም ራስን የእርሱ ባለመሆኑ ሊያደርገው አይገባም ። ራስን ማጥፋት በእግዚአብሔር ላይ የሚደረግ ትልቅ ኃጥአት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ራስን ማጥፋ ነፍስን መግደል ነው፤ ማንም ክርስቲያን ነኝ የሚል ሰው በእግዚአብሔር መንፈስ እና ቃል ስለሚመራ ራሱን ለማጥፋት አይደፋፈርም ። ክርስቲያኖች ህይወታቸውን ለእግዚአብሔር ለመኖር ተጠርተዋል፤እናም የሚሞትበት ጊዜ ውሳኔም የእግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡

ባለንበት ዘመን የአዕምሮ ጤናን የተመለከተው ጥናት እንደሚያመለክተው በዓመት እስከ 800,000 ሰዎችራሳቸውን
እንደሚያጠፉ የWHO ሪፖርት ያመለክታል ። ከዚህ ከፍ ያለ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ደግሞ ራሳቸውን የማጥፋት ሙከራ ያደርጋሉ።በተለይም
እድሜያቸው ከ15 እስከ 29 ዓመት በሆኑ ወጣቶች ሁለተኛው ከፍተኛ ሞት የሚመዘገብበት ችግር ነው ።
እንዲሁም 79% ያህሉ በዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሃገራት ላይ የሚስተዋል ነው ።

ሰዎች ራሳቸውን ለማጥፋት የተለያዩ አማራጮችን ሊጠቀሙ ይችላሉ: መርዝ መጠጣት፣ መታነቅ ፣የጦር መሳሪያ መጠቀም፣ ራስን ከፎቆች ላይ መወርወር እና የመሳሰሉትን በዋናነት ይጠቀማሉ ።

አጋላጭ ሁኔታዎች የተለያዩ የአዕምሮ ህመሞች በተለይም (ድባቴ (depression )ከፍተኛ የአልኮል መጠጥ ተጠቃሚነት )፣ከባድ አካላዊ ህመም ፣ የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ጭንቀት፣ ጾታዊ ጥቃት፣ካሰቡት ግብ መድረስ አለመቻል ፣ጦርነት የበዛ ብቸኝነት ዋና ዋና አጋላጭ ችግሮች ናቸው።እንዲሁም ቀደም ባለ ጊዜ ያልተሳካ ራስን የማጥፋት ሙከራ ከነበረ ዋነኛ አጋላጭ ችግር ሊሆን ይችላል ።

ጉዳቱን ለመቀነስ ምን ማድረግ ይቻላል?

በዋናነት ለሰው ልጅ ምድራዊ ሕይወት እውነተኛ ደስታን፣እውነተኛ እርካታን፣እውነተኛ ሰላምን የሚጎናጸፈው በመንፈሳዊ ሕይወቱ ሲያርፍ ነው ። የዚህ ምንጭ እና መሰረቱ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶሰን አዳኙ አድርጎ ማመኑ ወይም መቀበሉ ነው። ዋናው የሰው ልጆች ሁሉ ሰለም ምንጩ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ጌታ የአእምሮ ሕመምን ሊፈውስ ቢችልም እንደ ሰው ራስን የማጥፋትን ችግር መከላከል የሚቻልባቸው መንገዶች መጠቆም አስፈላጊ ነው።
1ኛ, በተለይም ራስን ለማጥፋት የሚረዱ ምቹ ሁኔታዎችን መቀነስ!
2ኛ, ተደጋጋሚ የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመገናኛ ብዙሃን በመስጠት!
3ኛ,ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረገ ማዕከል በማደራጀት ለመምህራን ለወላጆች እንዲሁም ለትምህርት ቤት ማህበረሰብ በቂ የቅድመ ጥንቃቄ መረጃና ትምህርት መስጠት ! 4ኛ,ለተማሪዎች በስነ ልቦና ባለሙያዎች የማማከር አገልግሎት እንዲያገኙ ማመቻቸት፣
5ኛ,የአልኮል መጠጥ አጠቃቀም ላይ ጥንቃቄ ማድረግ !
6ኛ, የትኛውንም ዓይነት የአእምሮ ህመሞችን ቶሎ መለየትና በቂ ህክምና ማድረግ ( በተለይ ድባቴ) እንዲሁም ተገቢውን ክትትል ማድረግ፣በቂ የሱስ ማገገሚያ ማዕከላትን ማቋቋም በእጅጉ አስፈላጊዎች ናቸው ።

7ኛ, ዋነኛው እና መብትሔ ቤተ ክርስቲያን ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ መስበኳ ሲሆን ወንጌል ዓለም ላለችበት ቀውስ ሁሉ ፣የሰው ልጅ ለሚገኝበት እንቆቅልሽ ሁሉ መፍትሔ ነው ።

ቤተ ክርስቲያን በመንፈሳዊ ሕመም ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች ፈውስን፣ ድካም ውስጥ ለሚገኙ ብርታትን፣ በስጋ ሕመም ውስጥ ላሉ የሥጋ ፈውስን፣ ያለ ክርስቶስ ላሉት ደግሞ የዳግም ልደት መታደስን ሊያስገኙ የሚያስችሉ አገልግሎት መስጠት ይጠበቅባታል።

ብዙዎች ራሳቸውን የሚያታልሉ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው ከዓለም ጋር ተወዳጅተው ተቀላቅለው ተመሳስለው መኖር የሚያስከትለውን ጉዳትም የዘነጉ አሉ። ወንጌልን ስበኩ “እንዲህም አላቸው፦ ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ።”
(ማርቆስ 16፥15 ) “ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።”(ማቴዎስ 10፥8)

ስለዚህ :-
1ኛ, ራስን ማጥፋት በእግዚአብሔር ፊት የግድያን ያህል ትልቅ ኃጢያት መሆኑን መገንዘብ ይገባል !
2ኛ,በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መኖር ምድራዊ ለሆነው ኑኖ የደስታ፣ የእርካታ፣ የሰላም ሁሉ ምንጭ እና መሠረት መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል !
3ኛ, በምድ ባለንበት ዘመን ጌታ በሕይወታችን ዓላማ እንዳለው አውቆ መኖር ይገባል !
4ኛ, ላመኑቱ የዘላለም ሕይወት የክብር ተስፋ አለ !
5ኛ, እኛ የራሳችን አይደለንም እና በራሳችንም ላይ አንዳች የማድረግ ሥልጣን የለንም 1ቆሮ 6:-19 !
17 viewsedited  03:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-01 20:29:52 እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ !

ጌታ የተወለደበትን ዓላማ በመረዳት በዓሉን ማክበር ይሁንላችሁ ! (ሉቃስ 2:-8-14)

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ሲታሰብ ከመብልና በመጠጥ፣ የመልካም ምኞት መግለጫ ካርድ ከመለዋወጥ፣ በዘፈን እና በስካር የመታሰቢያ በዓሉን ከማሳለፍ ይልቅ የበዓሉን መልዕክት የእግዚአብሔርን አላማ እና እቅድ መረዳት ሰው በምድር እንዲኖር በተሰጠው ዘመን አገኘሁት ከሚላቸው ውድ ነገሮች ይልቅ መለኮት በሕይወቱ ያለውን የከበረ የደህንነት ዓላማ እንዲረዳ ያስችለዋል።

ዓላማውን የሳተ ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአል መታሰቢያ አከባበር እግዚአብሔርን ደስ አያሰኘውም! በአሉ ትርጉም የሚኖረው ጌታ የተወለደበትን የማዳኑ ዓላማ በመረዳት ታላቁን የወንጌል ተልዕኮ በማወጅ ጌታ ወደምር የመጣበትን የማዳን ዓላማ በማከናወን ነው። እግዚእብሔር ሰውን ከዘላለም ጥፋት ለማዳን ያለው እቅድ እና ዓላማው የወንጌሉ የምስራች ሚስጥር ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስን ለመዳናችን አሳልፎ መስጠቱ ነው ::ስለዚህ እባካችሁን የተወለደበትን ዓላማ ለሰዎች በማወጅ ልደቱን እናክብር።

ስለዚህ ይህ የልደት በዓል በማክበር ብቻ የሚታለፍ አንድ ተራ ታሪካዊ ድርጊት አይደለም :: ይህ ወቅት በሰው ልጆች ታሪክ ውስጥ ከመሆኑም በፊት ያልነበረ ከሆነም በኃላ ያልተደገመ የአስደናቂ መለኮታዊ እቅድ ክንዋኔ ነው:: የሰው ልጅ በኃጢያቱ ምክንያት የሞቱን መርዶ በሕግ ተረድቶ ፣ በሐይማኖት ስርአት ተተብትቦ ፣ በሕግ በአድርግ አታድርግ ተወጥሮ ፣ፍርዱን ሲጠባበቅ፣ የእግዚአብሔር ድምፅ ለራቀው፣ በዲያቢሎስ እስራት ሲሰቃይ ለኖረው ፣ሰው ሁሉ ያለበትን ሁኔታ ጠልቶ ሰላም በጥማት በተፈለገበትና አዳኝ በታላቅ ጉጉት በተጠበቀበት አዳኙ ጌታ ተወለደ !(ሉቃ 2:10) የጌታ መልአክ በታላቅ ብረሀን ታጅቦ ተገለጠ ለህዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ የምስራች አወጀ የምስራቹም " ዛሬ ... መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" የሚል ነው(ሉቃ 2:11)

" አማኑኤል " እግዚአብሔር ከሰው ጋር ሰውም ከእግዚአብሔር ጋር ሆነ ! (የዮሐንስ 1:1)
እግዚአብሔር የሆነው ቃል ሥጋ ሆነ ጸጋንና እውነትንም ተመልቶ በእኛ አደረ (ዮሐንስ 1:14) ስለዚህ ታላቅ ደስታ የተባለው የምሥራቹ ነው ! በስጋ የተገለጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑ ነው (ማቴ 1:21) ይህ እግዚአብሔር በልጁ የገለጠው በፀጋ የሆነ ፅድቅ የሰው ልጅ ኃጢያት የሚያስተሰርይ ነፃ የሚወጣበት ከዘላለም ፍርድ የሚያመልጥበት ከሰይጣን እስራት የሚፈታበት ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብረሀን የሚሻገርበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግስት የሚፈልስበት አስደናቂ የእግዚአብሔር የማዳኑ ጸጋ ነው ። (2ኛ ቆሮ 5:21)

ጌታ በተወለደበት ወቅት ልዪነት ነበር ! በአይሁድና በአህዛብ መካከል በእግዚአብሔርና በሰው ልጆች መካከል በባርያና በጌታ መካከል ልዪነት ጥል ነበረ :: (ኤፌሶን 2:-14 -16) ነገር ግን የሰላሙ አለቃ ኢየሱስ ተወለደ በመካከል ያለውን የጥል ግርግዳ በስጋው አፈረሰ ። ልዩነትንና ጥልን በመስቀል ገደለና አንድ አዲስ ሰውን ፈጠረ ::“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።”
(2ኛ ቆሮ 5፥17)

ስለዚህ አሮጌው ነገር አለፈ ፣ ሁሉም አዲስ ሆነ ፣ ልዩነት ተወግዷል፣ ዛሬ ሰዎች በብሔር፣ በቋንቋ ፣ በዘር ልዩነቶችን እየገነቡ ያሉት ልዩነትና ጥል ጌታ በመስቀሉ የገደለውን ነው:: ጌታ ገድሎ የቀበረውን ልዩነት እና ጥል ከመቃብር ቀስቅሰው ሕይወት ሊዘሩበት ይታገላሉ። ይህ ልዩነት እርስ በርስ የሚያጠፋፋ መርዝ ነው ! ጥላቻን መናናቅን ክፋትና አመፃን የሚዘራ ነው ::

ኢየሱስ የሰላም ዓለቃ ነው !(ት. ኢሳ 9:-6) ስለዚህም ነው ይህንን ያየው ስመዖን የእስራኤልን መፅናናት የንጉስንም መወለድ ሳያይ እንማይሞት በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ ነበር :: ከዚያ ከማርያም ተቀብሎ አቅፎ አቤቱ አይኔ ይህንን ማዳንህን የአዳኙን መወለድ ካየች እኔን ባርያህን በሰላም አሰናብተኝ አለ :: ፈቃዴ መሻቴ ናፍቆቴ ፍላጎቴ ተፈፅሞአል አለ::የሩቅ ምስራቀቅ ጠቢባንም እንዲሁ ብዙ ማይልስ አቋርጠው " የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት ነው ?" እያሉ ወርቃቸውን ከርቤያቸውን እጣኖቻቸውን በግመሎቻቸው ጭነው ሲፈልጉት የምናየው ለዚሁ ነው ::

ለምን ፈለጉት ? የርሱ ንጉሳዊ አስተዳደር ዓለም ላለችበት ችግርና እንቆቅልሽ ሁሉ መፍትሔ ነው :: ምክንያቱም እርሱ የሠላም ንጉስ ነው ! የፍቅር ንጉስ ነው ! ለመንግስቱ ሕግ ሳይሆን የሰው ልጅ እንዳይሞት የራሱን ሕይወትስ እንኳ በወንጀለኛው ፋንታ የሚያኖር ንጉስና አዳኝ ነው :: እርሱ የማይፈታው ቋጠሮ የማይመልሰው ጥያቄ የማይፈውሰው ቁስል የለም ::

የጠቢባኑ ጥያቄ ግራ የሚያጋባ ነው ! ሕዝቡ ከሚያውቁት ንጉስ ሌላ ከየት መጣ ? ኧረ መጥቷል ሰው የተወለደበትን ቦታ አቅጣጫ ባይረዳ ኮከቡ በመለኮት ትዕዛዝ ሊመራ ወጥቷል::እነርሱም በኮከቡ ተመርተው ባገኙት ጊዜ
ተንበርክከው ሰገዱለት :: የያዙትን እጅ መንሻ ሰጡት ይህ ደግሞ ተቀናቃኙ ለግድያ እየፈለገው ስለሆነ ለማርያምና ለዮሴፍ የግብፅ ስደት በቂ የመለኮት አቅርቦት ነው :: የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት ነው ? ዛሬም እርሱ ለሰው ልጆች ሁሉ ያስፈልጋል :: በኃጢያትና በአጋንንት እስራት ፍርዱን ለሚጠባበቅው በሞት ፍረሀት ለሚኖረው የሰው ልጅ ሁሉ ኢየሱስ የመዳኛ መንገድ ነው ! የሽግግር ጌታ ከሞት ወደ ህይወት ያሻግራል ! ታዲያ ይህ ንጉስ አያስፈልግምን ? አፍ ባይናገርም የሰው ልጅ የውስጥ ማንነት የዘወትር ጩኸት ነው ! (መዝ 42:2) የውስጥ ጩኸት ናፍቆትና የዘወትር ጥማት ከተናፋቂው ሌላ ነገር ቢቀርብ እርካታ አይሆንም ሰላም አይሰጥም አያሳርፍም ::

ብዙዎች ለዚህ የውጥ ጩኸት ሌላ ብዙ ምላሽ ቢሰጡም ጩኸቱ ዛሬም አላቆመም ንጉሱ ካልተገኘ ሕይወት ኑሮ ትርጉም አልባ ነው :: ሰላም እና እረፍት አይታሰብም። ዛሬ እንደ ጠቢባኑ ብዙ ማይልስ ማቋረጥ አይጠበቅብንም :: ንጉሱ በስፍራ አይወሰንም ዛሬ እንደ ገሊላ ሴቶች እርሱን ፍለጋ ወደ ሙታን መንደር መሮጥ አያስፈልገንም ::(ሉቃስ 45:-5) ኑ ወደ ንጉሱ ! ሠላማችሁ እንደ ወንዝ ይሆናል :: እረፍታችሁ ይበዛል :: የተጫናችሁ የኃጢያት ሸክም ይራገፋል ::በዚህም በምድር ከሞት በኃላ ሊመጣ ባለው ዓለም ድናችሁ ትቀራላችሁ !“ፊልጶስ ናትናኤልን አግኝቶ፦ ሙሴ በሕግ ነቢያትም ስለ እርሱ የጻፉትን የዮሴፍን ልጅ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል አለው።”(ዮሐንስ 1፥46) ጌታን ማግኘት እና ድኖ መቅረት ይሁንላችሁ ! ተባርካችኃል!
24 viewsedited  17:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-18 20:25:23 ከሰማይ የተገለጠው የወንጌል እውነት ለሚበርዝ ወዮለት !

“ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።”
— ሮሜ 1፥3-4
በዘመናት መካከል ይህንን የወንጌል እውነት ለመሸቃቀጥ የተነሱ ጥቂቶች አይደሉም ። ወንጌል ምንድነው ? በወንጌልስ የሚሰበከው ማነው ? ወንጌል በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የሚለው እውነት ለዘላለም የታመነ ነው ።

ሐዋርያው የያዘውን የወንጌል እውነት እንዲሸቃቅጥ የሚስሩ እጅግ ብዙ ነበሩ እርሱ ግን እንዲህ አለ :-“የወንጌልም እውነት በእናንተ ዘንድ ጸንቶ እንዲኖር ለአንድ ሰዓት እንኳ ለቅቀን አልተገዛንላቸውም።”
— ገላትያ 2፥5
እውነተኛ አገልጋይ የወንጌል እውነት ጸንቶ እና ተጠብቆ እንዲኖርም ጭምር ይተጋል።

ሐዋርያው የወንጌልን እውነት ሲበርዙ የሌለውን ያልተላኩትን ወንጌል የሚሰብኩትን ጨምሮ በእርግማን አውግዞአል። በቤተክርስቲያን አዕማድ የተባለውን ፣ የበጎች እረኛ እና ጠባቂነት የመጋቢነት ኃላፊነት እና ሹመት የተሰጠውን ኬፋን /ጴጥሮስን/ ከወንጌል እውነት ተጣሞ ሲያገኘው ፊት ለፊት ተቃወምኩት አለ ።“ነገር ግን ኬፋ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ ፊት ለፊት ተቃወምሁት፥ ይፈረድበት ዘንድ ይገባ ነበርና።”አለ
— ገላትያ 2፥11

የወንጌል እውነት ተጠብቆ እንዲኖር ዋነኞች መስለው ሊታዩ የሚወዱትን መገሰጽ ይገባል ። ስህተታቸውንም አጋልጦ በማረም ሕዝብን ከጥፋት መታደግ ይገባል።የወንጌል እውነት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። ይህንን አውነት ጥለው በርሱ ቦታ ሌላ ተተክቶ የማያድን የሐሰተ ወንጌል ያቆሙ በእግዚአብሔር ፊት ስላደረጉት ሁሉ ከፍርድ አያመልጡም ። የወንጌል እውነት ያጣመሙ ተጣሞ እንዲጻፍ ያደረጉ የሰበኩትም ጭምር የተረገሙ ናቸው።

"ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።"(ገላትያ 1:-8-9)

ሐዋርያው ጳውሎስ የወንጌል እውነት ተጠብቆ እንዲኖር ሊያጣምሙ የሚሯሯጡትን ከመገሰጽም አልፎ ከተሰበከው ከኢየሱስ ክርስቶስ ውጪ ሌላ ወንጌል እንደሌለ አስረግጦ እየተናገረ ከተሰበከው ውጪ የሚሰብክ የተረገመ ይሁን አለ። ዛሬም ወንጌል ተጣሞ እያዩ ዝም ያሉ ፣ሐሰተኛ ወንጌል የሰበኩ ፣የወንጌልን እውነት አጣመው በመሸቃቀጥ ትውለድን ያሳቱ ፣ሐሰት ተተክቶ እንዲሰበክ ያደረጉ ከተጠያቂነት አያመልጡም። እግዚአብሔር የሰው ልጅ እንዲድንበት የገለጠውን ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን በመስበክ ፋንታ ትውልደ ትውልድ እንዲጠፋ የተሸቃቀጠ የተበረዘ ወንጌል አስቀምጠዋልና።

እውነተኛውን ወንጌል ኢየሱስን በመስበክ እግዚአብሔርን ከመስደሰት ይልቅ ጣዖት ተክለው ለሰው ደስታ ኖረዋልና ታላቅ ፍርድ ይጠብቃቸዋል ።
“ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።”
— ገላትያ 1፥10

የወንጌል እውነት በብሉይ የተተነበየለት ፣ በወንጌል የተገለጠ ፣ በሐዋርያት የተሰበከለት ፣ በመልዕክቶች የተብራራ ፣ በራዕይ በክብር የተገለጠ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። ከርሱ ውጪ የሚሰብክ የሚጽፍ እግዚአብሔር የገለጠውን የመዳን እውነት የሚያዳፍን የተረገመ ነው።
9 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-15 04:24:02 የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል?

መጽሐፍ ቅዱሳች ከእኛ በፊት ከነበሩ ታላላቅ ሰዎች እንድንማር በምሳሌነታቸው ያቀርባቸዋል። ምክንያቱም መጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው ለትምህርታችን ስለሆነ ነው።

“በመጽናትና መጻሕፍት በሚሰጡት መጽናናት ተስፋ ይሆንልን ዘንድ አስቀድሞ የተጻፈው ሁሉ ለትምህርታችን ተጽፎአልና።”
— ሮሜ 15፥4

ለመማር የፈቀደ መጽሐፍ ቅዱሱን ያነባል ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ማንበብ ይወዳል ነገር ግን መሪ ያስፈልገው ነበር ። ኢትዩጵያዊ ከንባብ ባህል ይልቅ የማውራት ባህል አለው። በእርግጥ ያለ አውቀት ወሬስ ከየት ይመጣል የተጻፈን እውነት መሠረት ያላደረገ ወሬ ደግሞ አፈ ታሪክ እና ተረታተረት ከመሆን አይዘልም። ይህ ደግሞ ከእውነታው ይልቅ ውሸት ያመዝንበታል።

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ሲመለስም በሰረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር።(የሐዋ ሥራ 8 :-28)ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ለመማር፣ ለመጠየቅ እና ለመመራት የተዘጋጀ ልብ ነበረው።የኛ የብዙ ኢትዮጵያዊያውያን ችግር አያውቁም እንዳንባል የማናውቀውን "አውቃለው" ያልገባንን "ገብቶናል" የማለት የትዕቢት ችግር እንዳለብን ይወራል።እውነት ነው ያልገባንን እንዲገባን ለመማር ከመትጋት ይልቅ እውነትን አሳዶ ተረቴን አጽድቁልኝ ባይ ሆነናል ግን ለምን ? ወደ መረዳት ባለጠግነት ፣ወደ እድገት፣ ወደ ተሻለ ደረጃ ከፍ የሚለው አለማወቁን አውቆ ለተሻለ እውቀት የሚመራውን የሚፈልግ ነው ።ምክንያቱም ዕውቀት ሁል ጊዜ ተማሪ ልብ ላለው ሰው ነው።

"እርሱም፦ የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል? አለው። ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው። ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ፦ እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል? ስለ ራሱ ነውን ወይስ ስለ ሌላ? አለው።" (ሐዋርያት 8:-33-34)

የመጽሐፍ ቅዱስ ዕውቀት እና እውነት የእምነት መሠረት ነው። ያወቀ የተረዳ የገባው ላመነበት ነገር ወዲያው ትክክለኛ ውሳኔ ይወስናል።ብዙ ጊዜ አባቶች በታላቅነታቸው፣ በትውልድ የቀደሙ በመሆናቸው ብቻ ያዳበሩት የሐይማኖት ባህል ስላላቸው ብቻ ያሉትን ሁሉ በቃሉ እውነት ሳንመዝን ሳንፈተን ለነርሱ ክብር ሲባል ሁሉን አግበስብሰን እንድንሸከም ይፈልጋሉ። ያ ግን እውነትን ሊተካ አይችልም ። ብዙዎችም አለመቀበላችንን እንደ ንቀት ይቆጥሩታል ይህም እውነት አይደለም።

በህይወታችን ያሉ ያልተመለሱ ጥያቄዎች እንቆቅልሾች መልሳቸው ያለው በእግዚአብሔር ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ነው ።ላነበብነው ለሰማነው እና ላመንበት ለእግዚአብሔር ቃል ቶሎ መወሰን እና አለመወሰን ብዙ ርቀት እና ልዩነት አለው።ኢትዮጵያዊው ቃሉ በጁ እያለ ማንበብም እየቻለ የተሻለ እውቀት ያለው መሪ አስፈልጎታል ። መሪውም ወደሚፈለገው የመዳን እምነት ግብ አድርሶታል።

"ፊልጶስም፦ በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ።ሰረገላውም ይቆም ዘንድ አዘዘ፥ ፊልጶስና ጃንደረባው ሁለቱም ወደ ውኃ ወረዱ፥ አጠመቀውም።"(ሐዋርያት 8 :37-38)

አየህ በዕውቀት ሁሉ የደረሰበት ነው ያለው። እስከተረዳው እስካወቀው ድረስ ነው ። ኢትዮጵያዊው ጀንደረባ የወንጌልን እውነት ወደተረዳው ወደ ፊሊጶስ መጠጋቱ ከእውነት ጋር አገናኘው እውነቱም የማይለወጠው ክርስቶስ ነው ።

ክርስቲያናዊ ሕይወት ከእውቀት ጋር የተሳሰረ ነው ። በእውቀት አይዳንም ፣ ያለ እውቀትም አይዳንም ። እውነተኛውን የሚታመን እውቀት ማግኘት ከደህንነት ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ። ክርስትና እውነትን በማወቅ እና በማመን የሚጀመር ጉዞ ሲሆን ታውቆ የማይፈጸመውን ለታማኝነቱም ወደር የሌለውን እግዚአብሔርን ለማወቅ ወደ መለኮት የዕቀት ውቂያኖስ መግባትም ነው ።

የክርስቲያናዊ እውቀት መሠረቱ መለኮታዊ መገለጥ ነው ። እግዚአብሔር በፍጥረቱ ራሱን ቢገልጥም በልጁ ደግሞ ራሱን የገለጠበት የሰውን ልጅ ከጥፋት የመታደግ የወንጌል የምስራች እውነት ከሁሉ የላቀ ነው ። እግዚአብሔር በልጁ መታወቅ እና መታመን የሚፈልግ አምላክ ነው ።
እውቀት ብቻውን ወደ ክርስቶስ ባያቀርብም ያለ እውቀት ወደ እምነት መምጣት አይቻልም ። ጻፎችን ፈሪሳውያም ክርስቶስ የት እንደሚወለድ በቂ እውቀት ነበራቸው። አለማመናቸው ከእወነት ጋር አላገናኛቸውም። ያለ እምነት እውቀት ብቻ መያዝም ሆነ ያለ እውቀት እምነትን ብቻም መያዝ ሁለቱም አደጋ አላቸው ። ከሁሉ የከፋው አደጋ ግን ሳያውቁ የሚያውቁ የሚመስላቸው ፣ ለመማር የተዘጋጀ ልብ እና የዳነ አዕምሮ በማጣት የሰው ብለሃት በፈጠረው ተረት መነዳት ነው ።

በዳነ አእምሮ ያለ ተማሪ ሁለት አስተማሪ አለው። አንደኛ መንፈስ ቅዱስ ሁለተኛ የተሻለ እውቀት ያለው አስተማሪ ። ለመማር የማይሻ ሰው ለራሱም ሆነ ለሌላው ደግሞም ለቤተ ክርስቲያን አደጋ ነው ። ያለ እውቀት ወደ እምነት አይደርስም። እንደ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ፡- “የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል?”( የሐዋ. 8፡31) በእውነት እግዚአብሔር ለመማር የተዘጋጀ ልብ ይስጠን ።ይህን ጥያቄ የተቀበለው ወንጌላዊው ፊልጶስ ተርጓሚ አያሻም እንዳሻህ ተርጉመው አላለውም፣ ተረጎመለት እንጂ። ደግሞም የተሻለ እውቀት በመያዙ አለተመጻደቀም ቀርቦ በትህትና አስተማረው እንጂ ። ኢትዮጵያዊው ጃንደረባም አምናለሁ ብሎ ለመጠመቅ አስቀድሞ አሳብ አቀረበ ። እስከ ጥምቀት ድረስ ባይማር ኖሮ ለመጠመቅ አይጠይቅም ነበር ። በመማር ወደ ዕቀት ባለጠግነት መግባት ለዳኑቱ የተሰጠ ትልቅ በረከት ነው ። እንጸልይ ?

1ኛ, በአውነት እግዚአብሔር እንደ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ አውነትን ለመረዳት የተዘጋጀ ልብ እና የዳነ አዕምሮ ይስጠን !

2ኛ, እግዚአብሔር በተጠየቅንበት ጊዜ ሁሉ በትህትና
በፍቅር እና በቅንነት መልስ ለመስጠት በመሰጠት በተሻለ ዕውቀት የተዘጋጀ ማንነትን ይስጠን !

3ኛ, እግዚአብሔር የተባለውን ሁሉ የተወራውን አፈታሪክ ከማግበስበስ ሕይወት አውጥቶ አንባቢ ትውልድ ያድርገን !
9 views01:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-11 07:51:34 ለምን አንበል !

የሚሆነው ባይገባንም እግዚአብሔር አዋቂ አለው ። የኛ ሲያልቅ የእግዚአብሔር ይጀምራል ! ሞተ ብለው ለቀበሩ በአስክሬን ላይ ሕይወት ዘርቶ ከመቃብር አውጥቶ የሰጣቸው ! ዛሬም ኤልሻዳይ ነው ።ጉልበቱ አይደክምም ።
“አብራምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለአብራም ተገለጠለትና፦ እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤”
— ዘፍጥረት 17፥1

እርሱ አበቃ ብለህ በዘጋኸው ! ፈረሰ ብለህ በጣልከው ! ደረቀ ብለህ የተውከውን.ደርሶ ያለመልማል !

ብዙዎች እግዚአብሔርን ታዘብኩህ ይሉታል ምነው ? ታምኜብህ ጉድ ሰራኸኝ፣ተውከኝ ! ረሳኸኝ ! ጣልከኝ! ምን አደረኩ ? ይላሉ እርሱ በሰዓቱ ሲመጣ እጅ በአፍ ላይ ያስጭናል !
አላያችሁም የሕዝቡን መንገድ የዘጋውን ባህር ሲከፍል ፣ ለ90 አመት አሮጊት ልጅ ሲሰጥ ፣ ከአለት ውሃ ሲያፈልቅ ፣ ከሰማይ መና ሲያዘንብ ኧረ ስንቱ ???

በራሴ ሰዓት ካልሆነ አይባልም ! እኔ ካልመራሁህ የሚሉ ብዙ ናቸው ግን ግን መሪው ሁሌም እርሱ እግዚአብሔር ብቻና ብቻ ነው ! እግዚአብሔር የሚሰራውን ያውቃል !

እርሱ ሲመጣ ፡- የዘጋነውን ይከፍታል ፣ለቀበርነው ጉዳይ ህይወት ይሰጣል ፣ እርሱ በራሱ ሰዓት አይታማም !
ለምን ዝም ይላል ? ለምን ይዘገያል ? ለምን አይፈርድም ? አይባልም ። ለኛ የሚሆነው ባይገባንም እግዚአብሔር አዋቂ አለው ። እርሱ በዚህ ሁሉ ውስጥ ሥራ አለው።የርሱ አሰራር የሚገባን ሥራው ሲያልቅ ነው ። ተውቦ ሲመጣ ነው !ምክንያት ያጣንለት ምክንያት የሚያገኘው ያኔ ነው ! ያኔ ዝም ያለበት፣ የዘገየበት ዓላማ ግልጽ ይሆንልናል !

እስከዚያው እኛ እንደ እንባቆም እርሱ በተቀደሰ መቅደሱ አለና ዝም እንበል ! “እግዚአብሔር ግን በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤ ምድርም ሁሉ በፊቱ ዝም ትበል።”
— ዕንባቆም 2፥20

እየሆኑ ያሉት ነገሮች ባይገቡንም ለጌታ ያለንን ልብ እንጠብቅ ! መዘግየቱ ለምን ሊያስብለን ይችላል ነገር ግን ጌታ ቢዘገይም አይቀደምም ! ጌታን ለትናንትናው ብቻ ሳይሆን ለዛሬም እንመነው !
የእግዚብሔርን ጊዜ እንመን! ኢየሱስ በአባቱ ሰዓት እንጂ በኛ ሰዓት አይሰራምና ! እርሱ ያላየን፣ ያልሰማን፣ የማይደርስልን ቢመስለን አርሱ አይቶናል፣ ሰምቶናል ይደርስልናል ! ጩኸታችንን ሰምቷል ይመልሳል !
የተናገረውንም ይፈፅማል ! ለኛ ያለው ፍቅሩ አይለወጥም !

ጌታ ለልጆቹ የቅርብ አምላክ ነው! ለልጆቹ ይራራል እውነተኛ ወዳጅ ነው !ጌታ በዘጋነው፣ አበቃ ባልነው ፣ ተበላሸ ባልነው ፣ ታሪክ ላይ ተገልጦ ነገርን ይለወጣል ! ሞትን በሕይወት ይተካል ! ለጌታ የሚሳነው ምን አለ ?
እርሱ ኤልሻዳይ አምላክ ነውና !
ብቻ እኛ :-
1, ተስፋ ባለመቁረጥ እንጸልይ !
2, ትንሳኤውን እናለን !
3,በምስጋና እንቆማለን !
4, በአደራረጉ ያስደንቀናል ! አሜን ! አሜን ! አሜን !
14 views04:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 04:55:10 የራሱን ትውልድ መልካምና በጎ የተድላ ዘመን የማይናፍቅ ማነው ?

"... ሰው የሚዘራውን ሁሉ ያንኑ ደግሞ ያጭዳልና፤ … ባንዝልም በጊዜው እናጭዳለንና መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት።"(ገላትያ 6 :-7, 9)

ለነገው ትውልዱ መልካምና በጎ የተድላ ዘመንን የማይናፍቅ ማነው ? እንግዲያውስ መጪው ትውልድ ዛሬ የምንዘራው ዘር ውጤት ነውና ዛሬ ለምንዘራውን ዘር እንጠንቀቅ ።

የቤታችን መልክ በሰፈራችን፣ የሠፈራችን መልክ በወረዳችን፣ የወረዳችን መልክ በከተማችን፣ የከተማችን መልክ በሐገራችን ይገለጣል ። ለአንድ ትውልድ እድገት ላይ በአወንታዊም ሆነ በአሉታዊ መልኩ ከቤተሰብ ጓዳ እስካደገበት ማህበረሰብ ድረስ የየራሳቸው አስተዋጽኦ መኖሩ እሙን ነው ። ስለዚህ ብንቀበልም ባንቀበልም የሀገራችን መልክ የቤታችን መልክ ነው። የቤታችንም መልክ የሀገራችን መልክ ነው።

ዛሬ ላይ በልጆቻችን ላይ የምንሰራው ትውልዱ ከኛ ላይ በተግባርም ሆነ በቲዎሪ የሚቀርጸው ዕውቀት የነገ ኑሮውን ይወስናል ። ዛሬ በቤታችን ውስጥ በልጆቻችን ላይ የሰራነው መልክ ነው ነገ በውጭ በአደባባይ ተገልጦ የሚታየው።

በትውልዱ ላይ የምንዘራው ዘር ነገ የሚታጨድ ነው። ዘረኝነትን የሚዘራ ነገ የዘረኝነትን ውጤት ያጭዳል። ቂም፣ ጥላቻና አመጻን የሚዘራም ያንኑ ያጭዳል ። የዘራችሁትን ዘር ውጤት መቀየር አይቻልም ። የምንወልዷቸው ልጆች የነገ ሠላም የነገ ፍቅር የነገ አንድነት መተማመን በፍቅር አብሮ መኖር የምንፈልግ ከሆነ ነገ የሚገለጠው የምርት ውጤት ዛሬ የሚዘራው በመሆኑ ቆም ብለን እየሰራን ያለነውን ሥራ ልንፈትሽ ይገባል ።

ዛሬ በልጆቻችን ላይ በተግባራዊ ምሳሌነትም ሆነ በንግግር ለምንዘራው ዘር እንጠንቀቅ። ያ የመጪውን ትውልድ አኗኗር ይወስናልና ። አመጽ ዘርቶ ሠላምን የሚያጭድ የለም ። ክፋትን ዘርቶ በጎነትን የሚያጭድ የለም። ጥላቻን ዘርቶ ፍቅርን የሚያጭድ የለም። ስለዚህ በትውልድ ላይ መልካም ዘርን መዝራት ለነገው የትውልዳችን የልጆቻችን ሰላም፣ ፍቅር እና አንድነት እጅግ በጣም ወሳኝ ነው። ይህንን እውነት ቆም ብለን በእውነት ትኩረት ሰጥተን ካላሰብንበት ለነገው የልጆቻችን የተመሠቃቀለ፣ የተበላሸ ኑሮ ፣ለሰላሙ መደፍረስ ፣ ለፍቅር ለእርቅ መጥፋት ምክንያቶቹ እኛው እንሆናለን። ይህ ማለት የራስህ ትውልድ ጠላት አንተው እራስህ ትሆናለህ ማለት ነው።

ስለዚህ የዛሬው አኗኗራችን የትውልድ ቀረጻ ስራችን የነገው እውነተኛ ወላጅ ወይም የተውልዳችን ጠላት ሊያደርገን ይችላል ማለት ነው ። ለትውልድህ ጥላቻን ቂምን አመጽ እና ጦርነትን አታውርስ። ከወዲሁ በትኩረት አስብበት ይገባልና ሀገርንም ቤተክርስቲያንንም የሚረከቡት እነርሱ ናቸውና።
እንደ ቤተሰብ፣ እንደ ቤተክርስታያን፣ እንደ አብያተ ክርስቲያናት፣ እንደ ሐይማኖት ተቋማት፣ አብሮ በጉርብትና እንደሚኖር ማህበረሰብ፣ እንደ ወረዳ ፣እንደ ከተማ፣ እንደ ሐገር ይህንን በትኩረት ካላሰብንበት የነገዋ የበለጸገች ሐገር ለትውልድ እናስረክባለን ማለት ዘበት ነው ። ዛሬ ያልዘራነውን ነገ ከየት እናጭዳለን ?

ይህ የሁሉም ኃላፊነት ነው ። በአብያተ ክርስቲያናት ፣በሐይማኖት ተቋማት፣በፖለቲካ መሪዎች ፣ በሐገር መሪዎች ፣በእያንዳንዱ ቤተሰብ የነገውን የልጆቻችንን ሠላም ፍቅር አንድነት በማሰብ በጥብቅ ሊንሰራበት ልናተኩርበት ልንጸለይበት ይገባል። አልፎም ትውልዱን በመልካም ሥነምግባር የሚቀርጹ አስተማሪዎች ወደየትምህርት ቤቱ ገብተው በመልካም የጋራ እሴቶች ላይ በማተኮር ሊያስተምሩ ይገባል። የነገውን የትውልዱን ሞት ጥፋት ቁስቁልና የማይሻ ለዚህ እውነት ትኩረት ሰጥቶ በትጋት ይሰራል።

ለነገው የትውልዳችን ሠላም ፍቅር አንድነት ዛሬ በነርሱ ላይ የምንዘራውን ዘር እንምረጥ እንጠንቀቅ ። ተባረኩልኝ !
2 views01:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-01 07:29:21
21 views04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-27 19:50:26 2ኛ, ምስጋናዋ (ሉቃ1:- 47- 55)
"ማርያምም እንዲህ አለች። ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤ የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ሥራ አድርጎአልና፤ ስሙም ቅዱስ ነው። ምሕረቱም ለሚፈሩት እስከ ትውልድና ትውልድ ይኖራል።"

3ኛ, ዕውቀቷ (ሉቃ1:-47-55)
ታዲያ ማነው ብፅዕናዋን ከሚያውጅ ትውልድ እድል ፈንታ እነዲሆንለት የማይሻ ?ታዲያ ዘመኗን ህይወቷን ትዳሯን ክብሯን ለእግዚአብሔር ክብር የተወች ። ያን ያህል የሐዘን ሰይፍ በሕይወቷ ያሳለፈችውን ። ህጻኑ በሄሮድስ እንዳይገደል ይዛ አገሯን ምድሯን ቤቷንና ኑሮዋን ጥላ ስለጌታ የተሰደደችውን ።

ሌት ተቀን ከጌታና ከአገልግሎቱ ሳትለይ ለአገልግሎቱ መፈፀም እስከቀራኒዮ የተከተለችውን በእውነት ሰይጣን ካልሆነ ማን ጠላቷ ሊሆን ይችላል? እኛስ በእውነት እንወዳታለን ። ይልቁንም የማይወዷት ጌታ ያዘዘውን የማያደርጉ ! ( ዮሐንስ 2:-5) በስሟ ያልተባለውን ያልተደረገውን የሚጽፉ አመጸኞች ናቸው ።
እርሱ እንዲሰበክ ያዘዘውን ወንጌል የማይሰብኩ ! (ማቴ 28:-18-20)
13 views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-27 19:50:26 እኛስ የጌታችን እናት የንጽህት ድንግል ማርያም ወዳጆች እንጂ ጠላቶች አይደለንም !

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እናት የንፅህት ድንግል ማርያም ወዳጃች እንጂ ጠላቶች አይደለንም ።ብዙ ጊዜ በሃይማኖት በዓላት ጊዜ በአደባባይ ሲዘፈን ፣ በመጽሔት ሲጻፍ ፣በፌስቡክ ሲፓሰት የምናየው የተለመደ ነገር ጴንጤ መናፍቅ የማርያም ጠላት ……ወዘተ መስማት ማየትና ማንበብ የተለመደ ነገር ነው ።በውኑ አማኝነት የማርያም ጠላት ያስብላልን ? ማርያም እራሷ በርሱ እንድናምን አልሰበከችምን ? ይህ ተቃዋሚዎች አማኞችን ለማጥላላት በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዳይኖረን የተጠቀሙበት አማኙን የማጥላላት ዘመቻ እንደነበረ ነው ።

ስለዚህ አማኝ ሁሉ ቅድስት ፣ብጽዕት፣ ንጽህት የጌታችንን የመድኃኒታችንን እናት ይቅርና እውነተኛ አማኝ ጠላቱን እንኳን እንዲጠላ አልተፈቀደለትም። ስለዚህ አማኙ እንድናመልካት፣ እንድሰግድላት ፣ታቦት በስሟ ተቀርጾ ከወራት አንድ ቀን ተቆርጦ በስሟ ተሰይሞ ለማርያም እንዲሆን የታዘዘ የአክብሮት ስግደት በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የለም ። ትክክልም አይደለም ማርያምም እራሷ አትቀበለውም።

ለሁሉም በማናውቀው ጉዳይ የማርያም ጠላት ተብለን የማርያም ወዳጅ ነኝ ያለ ሁሉ ለፍቅሩ ያለውን ዱላ በጠላቷ ላይ ያሳርፍ እየተባለ ቤተሰብ ልጁን፣ልጅም ወላጁን እንዲጠላ ሲዘራ የኖረ አመጽ ተነቅቶበታል። ይህ አማኙ በሕዝብ ፣በቤተሰብ፣ በዘመድ አዝማድ ፣ በወገኑ እንዲጠላ የተደረገበት ይፈዊ ዘመቻ ነበረ ። ሥም የማጠፋት ዘመቻ ዛሬ ላይ ተነቅቶበታል። ጴንጤ/አማኝ / ማርያምን እንደማይጠላ በሁሉ ዘንድ የታወቀ ሆኖአል። ስለዚህ ማርያም ከተጻፈላት ውጪ አይደለችም እርሷም ምንም መሆን ማድረግም አትፈልግም።ንጽህት፣ብጽዕት ፣ቅድስት ናት። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን እናት እጅግ በጣም እንወዳታለን ።

እኛ የማርያም ወዳጅ እንጂ ጠላት አይደለንም። ቅድስት ማርያም እራሷ “የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና። እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤” ብላለችና።( ሉቃስ 1፥48) እኛ የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን እናት ንፅህት ድንግል ማርያምን የምንወዳት ማንም ስላዘዘን አይደለም ቅዱስ ቃሉ ስፍቅር ስለሚነግረን ነው አበቃ። የኛን መወደድ አለመውደድ ፣ማክበር አለማክበር ማንም እንዲነግረን አያስፈልገንም። በመሆኑም እኛ የማርያም ወዳጆች እንጂ ጠላቶች አይደለንም ::

ተቃዋሚዎች የሌለውን እንዳለ ያለውንም እነደሌለ በማወጅና በማሳወጅ ፣ በማውራትና በማስወራት የአማኞችን ስም ለማጠልሸት ለራሳቸው በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት አና በአንፃሩ ደግሞ አማኞችን በሕዝቡ ዘንድ እንዲጠሉ ፣በሕዝቡ እንዲገለሉ ፣ እንዲሰደዱ ለማድረግ ሲሮጡ ሲሰሩ ኖረዋል። ከዚህ ይልቅ እንዲሰብኩት የታዘዙትን ወንጌል ቢሰብኩ ምንኛ ውጤታማ በሆኑ። ራሳቸው ለቤ/ክ የሚቀኑ ማስመሰል ምናልባት ያልነቃው ሕዝብ ሆዳቸውን በእንጀራ ይሞላላቸው ይሆናል እንጂ በውሸት ማንም የትም መድረስ አይችልምና ዛሬም ምክራችን መሳሳት ይብቃችሁ ነው:: እኛ የማርያም ጠላቶች እንዳልሆንን ከናንተ መካከል ተመልሰው በወንጌል ያመኑ ወገኖች አረጋግጠዋል:: ለቀራችሁትም እግዚአብሔር አምላክ በተናገራችሁት ሁሉ ምህረት ያድርግላችሁ።
የሚቃወሙን ይህን በማለታቸው የመጣው መገፋት እና ስደት ለጊዜው ብዙ መከራና ስቃይ ቢያደርስም አሁን ግን አለፈ። ሁሉ ውሸት እንደሆነ ተረጋገጠ ። እኛ ከጌታ የተማርነው ይቅርታን ነው ።እኛም በርሱ የመስቀል ላይ ሞት ምህረት የተደረገልን ኃጢያተኞች ነን። ያኔ እንዲህ ቢጻፍ ከመከራው ለማምለጥ ብለው ነው ይባል ነበር እንግዲያውስ አሁን እውነቱን ይህ ነው ።

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ንፅህት ድንግል ማርያም አግዚአብሔር የሰው ልጆችን ከኃጢያታቸው ለማዳን ፈቃዱን የፈፀመባት ለፈቃዱም መፈፀም ራሷን ቀድሳ የተገኘች ልቧንም ለፈቃዱ የከፈተች በድንግልና ፀንሳ ብትገኝ የሚደርስባትን መከራ ስቃይ መገለል ቢያስፈልግ እንደ ህጉ መወገርም ቢሆን ለመቀበል ራሷን ያዘጋጀች ለእግዚአብሔር ፈቃድና እውነት መገለጥ እጮኛዬ ይተወኛል ሰው ምን ይለኛል ሳትል ለእየሱስ ክርስቶስ በስጋ መገለጥ እግዚአብሔር የተጠቀባት የፍጥረት ሁሉ ባለውለታ ነች ። ታዲያ ሰይጣን ራሱ ካለሆነ ማን የማርያም ጠላት ሊሆን ይችላል ? እግዚአብሔር ያከበረውንስ ማን ያዋርዳል? ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ነበር (ማቴ 1:- 1 - 18) በዚህ ሁኔታውስጥ በናዝሬት እያለች መለዓኩ ገብርኤል ወደ እርሷ ተላከ ወንድ ሳታውቅም በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ቅዱሱን የእግዚአብሔር ልጅ በድንግልና እንደምትወልድ አበሰራት ቃሉን አምና ወደ ዘመዷ ወደ ኤልሳቤጥ ሄደች (ሉቃ:-26-40) ማርያም ወደ ዘካርያስ ቤት በገባች ጊዜ ኤልሳቤጥ ማርያም ጌታን እንደምትወልድ በመንፈስ ቅዱስ ተረድታ "ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ " አለቻት ደግሞም ማርያም የጌታን ቃል በማመኗ ብፅዕት ነሽ አለቻት ( ሉቃ 1:- 40-45 ) ለሶስት ወር ያህል በኤልሳቤጥ ዘንድ ተቀመጠች ምናልባት ዮሐንስ እስኪወለድ ድረስ ይሆናል ከዚያም ወደ ቤቷ ተመለሰች (ሉቃ 1:-56 )

ዮሴፍ ግን እንደፀነሰች አይቶ ሊተዋት አሰበ :: ነገር ግን የጌታ መልዓክ እርሷን ለመውሰድ እንዳይፈራ በሕልም ነገረው :: ዮሴፍም ታዘዘ ዕጮኛውን ማርያምን ወሰደ:: በኩር ልጇንም እስከምትወልድ ድረስ አላወቃትም (ማቴ 1:-18-25) በመንግስት ትዕዛዝ ምክንያት ዮሴፍና ማርያም ወደ ቤቴልሄም ሄዱ በዚያም ኢየሱስን ወለደች (ሉቃ 2:- 1- 20) በሙሴ ሕግ መሰረት ወደ ቤተመቅደስ በሄዱ ጊዜ ስመዖን አገኛቸው" …በአንቺ ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል ብሎ የሚደርስባትን ሐዘን ተነበየ ( ሉቃ 2:- 22-35)

ሰበዓ ሰገል(ጠቢባን) በኮከብ ተመርተው የተወለደውን ህጻን አግኝተው ከሰገዱለትና ስጦታንም ከሰጡት በኃላ ማርያም ከዮሴፍና ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ ተሰደደች:: ከዚያም አሳዳጁ ንጉስ ሄሮድስ ከሞተ በኃላ ወደ ናዝሬት ተመለሰች (ማቴ 2:-1-33) መርያምም ኢየሱስን አሳደገችው:: የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ ሲሆንም ለፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች:: ማርያምም ስለ ህጻኑ የተባለውን በልቧ ትጠብቀው ነበር :: ማርያም ከቤተሰቧ ጋር በናዝሬት የታወቀች ሴት ነበረች (ማቴ13:-55, ማር6:-3, ሉቃ 2:-19) በቃና ሰርግ የወይን ጠጅ አልቆባቸው ሲቸገሩ ማርያም ለኢየሱስ ነግራ የመጀመርያ ተዓምራቱን በዚያ አደረገ:: ከዚህ በኃላ ከኢየሱስ ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወረደች (ዮሐ 2:-1-12) ኢየሱስ ሲያስተምር ትጎበኘው ነበር ::(ማቴ12:-46,ማር 3:-31-35, ሉቃ8:-19-21) እስከ ቀራኒዮ ተከተለችው ኢየሱስ በመስቀል ላይ ሳለ ወደ ቤቱ አንዲወስዳት " እነኃት እናትህ " ብሎ ለዮሐንስ ነገረው :: ዮሐንስም ወደ ቤቱ ወሰዳት (ዮሐ 19:-25-27) ከትንሳኤ በኃላ ከሐዋርያቱ ጋር ነበረች (ሐዋ 1:-12-14)

1ኛ, ብፅዕናዋ (ሉቃ 1:-28,42-48)
" መልአኩም ወደ እርስዋ ገብቶ። ደስ ይበልሽ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።"(ሉቃ 1:28)
እምነቷ (ሉቃ1:-34-38,45 ዮሐ 2:-5)
" ማርያምም። እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች"(ሉቃ 1:38)
12 views16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ