Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-21 11:37:55 Channel photo updated
08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 23:17:24 https://www.tiktok.com/@sanamesi1/video/7245957327923219714?_op=1&_r=1&_t=8dHHKe16hOg&social_sharing=v4
51 views20:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 23:14:43 Channel photo updated
20:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-18 23:10:11
43 views20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-31 19:44:57 አሁንስ ናፈቀኝ !

ያኔ ገና ያኔ ድሮ
ሁሉ ሲኖር ተንቀባሮ
ኢትዮጵያ ሐገሬ እማማ
ነበር ሲሰማብሽ የፍቅር ዜማ
የእድገት መሠረት የሥልጣኔ ማማ

ያገር ባህል ድምቀቱ
የሰው ለሰው ሕብረቱ
የአንድነት ውበቱ
መተጋገዝ መረዳዳቱ
እርስ በርስ መጽናናቱ
መከባበር ቤተሰባዊነቱ
የአንዱ ጥቃት የሁሉ ጉዳት
የአንዱ ውበት የሁሉ ድምቀት
በሌላው ደስታ ተደስተን
በሐዘኑ አዝነን
የወደቀውን እያነሳን
በአብሮነት ሕይወት ተጋምደን
በዜግነት ክብር ኮርተን
የአንድ አብራክ ክፋዮች
የአንድ ሐገር ሕዝቦች
የእናት ኢትዮጵያ ልጆች
ታላቅ ሐገር ይዘን
ምነው መንደር ናፈቀን ?

ዛሬ ዛሬማ ነገር ተገላብጦ
በተቃራኒው ተለውጦ
ወንድም የወንድሙን ሕይወት ሊቀማ
ለመጠፋፋት ሲጠማ
ባገር ሆነን ሐገር ሲናፈቀን
የሚሰማው ሁሉ ሲያሰቅቀን
እነሆ አመታትን ቆጠርን

ለናት ሐገር የሚያስብ ጠፍቶ
ሁሉ አበደ የዘር መርዝ ተግቶ
መካሪ እና ሐይ ባይ የጠፋባት
ሕዝብ በዘረኛነት ተመርዞ
አገር ጥሎ ወደ መንደር ጉዞ
እኔ የኔ እያለ ለሞት ተጠርዞ
ታላቅ የተባለው ሕጻን ልጅ ሆነብን
አንቀልባ እየገዛን ስንቱን ሰው አዘልን
ያስተምራል ብለን አክቲቪስት ያረግነው
ወደ እናቱ ሸክም ተመልሶ አየነው !

ነገር ሁሉ የመልካሙ ተገላቢጦሽ
ወየው ሐገሬ ምን ላድርግሽ
አስለቀሰኝ የዛሬ ላይ ምጥሽ
የትውልዱ ሩጫ ፍለጋ ሲፈተን
እውቀት ጥሎ ዘሩን ሲተነትን
ፍቅር ጥሎ ጥላቻን
ክብር ጥሎ ውርደትን
አገር ጥሎ መንደሩን
ያባት ጉምጉምታ የእናት ሐዘን
እባክህ ፈጣሪ በቃ በለን !

ያን ሁሉ መተሳሰብ ፍቅር ጥለን
ዛሬ ዛሬ ላይ ይኸው ወድቀን
መሥራት ቀርቶ ለአመጹ እጅ ሰጠን
የሟቹን ሞት አልወድም ያለ ፈጣሪ
የእውነት የጽድቅና የፍትህ መሪ
ወየው ለኛ የሚበጀንን ላላወቅን
ቅኑን መንገድ ጥለን አመጻን ለመረጥን
በለው በለው ባዩ አስተኳሹ በዝቶ
ሐገር ሰላም አጥታ ጭንቀተ ተንሰራፍቶ
አልሚ ሳይሆን አፍራሽ ባገር የናኘበት
ወይ አገሬ ጫካው ከየት ላምጣሽ
ብፈልግሽ ብናፍቅሽ ከየት ላግኝሽ
ዲያስፖራው ከምቾት ማማ ላይ
በለው በለው እንጂ ስቃይሽን ላያይ
ወንድማማቾች ጦር ሲማዘዙ
ጠላቶችሽ በደስታ ስካር ሲፈነጥዙ
አመጻ ጦርነት ሲስፋፋ
ምነው አስተዋይ ጠፋ ?

አስታራቂ ለሰላም የሚጮህ
ሁሉ አገርህ ሁሉ ወገንህ
የሚል ሁሉን በእኩል የሚያይ
ሰላምን አስፍኖ የሚያሳይ
ላገር ለወገኑ የሚያስብ
ሁሉን በአንድ እቅፍ የሚሰበስብ
አስፍቶ የሚያይ አርቆ አሳቢ
ወላጅ ያጡትን አሳዳጊ ቀላቢ
የአባቶቹን ኪዳን ጠባቂ
እውነትና ጽድቅን አርቃቂ
የተናገረውን የሚኖር መራቂ
አሁንስ ናፈቀኝ የአንድነት ድምቀቱ
የመከባበር ክብረቱ የፍቅር ውበቱ !
71 views16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-26 21:30:15 የጎዱህን የምትላቸውን ለመባረክ የምስጋና ቀን አዘጋጅ !

" ጌታም የጭንቀትን እንጀራና የመከራን ውኃ ቢሰጥህም አስተማሪህ እንግዲህ ከአንተ አይሰወርም፤ ዓይኖችህ ግን አስተማሪህን ያያሉ፥ወደ ቀኝም ወደ ግራም ፈቀቅ ብትል ጆሮችህ በኋላህ፦ መንገዱ ይህች ናት በእርስዋም ሂድ የሚለውን ቃል ይሰማሉ። (ት.ኢሳ 30 :-20-21) ጭንቀት እና መከራውን የሰጠህ ጌታ ሆኖ ሳለ ስለምን በአስጨናቂዎችህ እና መከራን ባሳዩህ ሰዎች አስፈጻሚው ታዝናለህ ታቄማለህ ? አየህ እነርሱ ጉዳይ አስፈጻሚ ብቻ ናቸው ።

የጭንቀት እንጀራ እና የመከራ ውሃ አያስደስትም አንዳንዴ እንጀራውም ውሃውም ከእንባህ ጋር ወደ አፍህ የሚገባ ይሆናል። ታለቅሳለህ ታነባለህ በምሬት ትንገበገባለህ ይሁን እንጂ ለገር ለሁ ለበጎ መቀየሩ አይቀሬ ነው ።

በቆይታ መከራው የመጣው ጭንቀቱ የመጣው ለጥቅምህ ለጥቅምህ እንደሆነ ይገባሃል ። አየህ መራራውን ያላየ የጣፋጩን ጣዕም አያደንቅም ። ሐዘንን ያላየ የሐሴት እና የደስታ ልኬት የለውም።ስለዚህ ነገር ቢመርህም ቢጨንቅህም አስተማሪህ ካንተ ጋር ነውና አታስብ በጉዞህም አቅጣጫ ጠቋሚ መሪ አስተማሪ አለ እርሱም ጌታ ነው።

እግዚአብሔር መልካም አስተማሪ ነው። አሳደዱኝ ገፉኝ አሰቃዩኝ አንላቱኝ አንቋሸሹኝ ተፉብኝ ጎዱኝ... ወዘተርፈ
ያልካቸው ሁሉ ባለውለታዎችህ ናቸው ። ዛሬ ይህ እውነት ገብቶህ ለማመስገን እግር ለማጠብ ለመሸለም ተነሳ ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን ይመስገን!

እስቲ አስቡ ምንም ብትገፉ አልወደቃችሁም ፣ ቢያሳድዷችሁ ሳያውቁት አሳደው አሳደው የጌታ እጅ ላይ ጣሏችሁ ፣ ቁልቁል ቢወረውሯችሁም ራሳችሁን ያገኛችሁት በተራሮች አናት ላይ ነው ። የተባለባችሁ አልሆነባችሁም አሳደው አሳደው በዘመናችሁ ወደማትችሉበት ክብር አደረሷችሁ ።

እየሆነ ያለው ነገር ቶሎ ባይገባንም ዘመን ይመጣል የሆነው ሁሉ እንኳን ሆነ የቀረው ሁሉ እንኳን ቀረ የምንልበት ። ያኔ ለምን ቀረ ብለን ያነባንበት ለምን ሆነ ብለን ምርር ብለን ያለቀስንበት ጊዜው ሲደር እንዳዲህ ይዘመርበታል ። ከጉዳታችን ትርፉ ይበልጥና ፣ ከሐዘኑ በላይ ደስታው ይልቅና እግዚአብሔር አዋቂ ነው ብለን ለምስጋና እንቆማለን።

ወርቅ በእሳት ነጥሮ ለጌጥ እስኪሆን ጌጥ አይደለም ፣ እንጨት በመጋዝ በመቁረጫ ማሽን በመላጊያ በመሳሰሉት ነገሮች ተሰርቶ ተቆራርጦ ለከበረ ዕቃነት እስከሚበቃ እንጨት እንጂ ዕቃ አይባልም ጌታም እኛን ለመስራት አንዳንድ ሰዎችን እንደ መጋዝ ፣ አንዳንድ ሰዎችን እንደ ማንጠርያ የእቶን እሳት ፣አንዳንድ ሰዎችን እንደ መግረፊያ አለንጋ (ጅራፍ) እና እንደ መቅጫ ዱላ የሚጠቀማቸው ሰዎች አሉ። እግዚአብሔር ልትቀረጹ ልትመከሩ ልትማሩ የምትችሉባቸውን መንገዶች ያዘጋጃል።እርሱስ ቢሆን “ምንም ልጅ ቢሆን፥ ከተቀበለው መከራ መታዘዝን ተማረ፤” አይደለምን ? (ዕብራውያን 5፥8)

ታዲያ መንገዱ በመከራም ቢሆን ዛሬ ላለህበት ያበቁህ ባለውለታዎችህ አይደሉም¡ እንዴ ? ናቸው እንጂ ።

በፍጻሜ ግብህ
በጸጋው የምትጎናጸፈው ድል ነው
በክብር የምትጎናጸፈው ጽናት ነው
የምትጎናጸፈው መንፈሳዊ ብቃት ነው
በምስጋና በተራሮች አናት ላይ ትሆናለህ
97 views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 10:22:22 Channel name was changed to «የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )»
07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 10:17:09
15 views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 10:16:23 እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና !

በመላው ዓለም ለምትገኙ ክርስቲያኖች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታች ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ !

" ... እናንተስ አትፍሩ የተሰቀለውን ኢየሱስን እንድትሹ አውቃለሁና፤ እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ።"( ማቴዎስ 28:-6)

ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት አስቀድሞ እንደሚነሳ ተናግሮ ነበር ። ደቀ መዛሙርቱ ግን ይህንን እውነት አላስተዋሉትም ። ስለዚህ ተስፋ በመቁረጥ ሲያዝኑ ሲተክዙ አንዳንዶችም ገና ሲጠሩ ወደነበሩበት የኃልዮሽ ሲገሰግሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተናገረው በሦስተኛ ቀን ተነሳ ።

የኢየሱስ ትንሳኤ ለሁሉ የተገለጠ ነበር ። እንደ ተናገረው የሞትን ጣር አጥፊቶ ተነስቷል። መቃብሩ ባዶ ነው። ስለዚህ ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም ኑና አረጋግጡ እዩም ተባሉ። በአንጻሩም ፈሪሳውያን ሱዱቃውያን ተቃዋሚዎች ሁሉ ጠባቂዎችን በማኖር ትንሳኤውን ሊሸፋፍኑ ጥረት ቢያደርጉም ኢየሱስ በብዙ ማስረጃ ለአርባ ቀን ሕያው ሆኖ ታያቸው ።(የሐዋርያት ሥራ 1:2)

እኛ ልንረዳው የሚገባውንን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የሞት እና የትንሳኤ ሚስጥር ምንድነው ?

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ የኢየሱስ ክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ብቻ አይደለም። በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ ውስጥ አንተም አንቺም ሁላችን አለን ። ምክንያቱም እርሱ የተቀበለው ሞት የሞተው የተነሳውንም ትንሳኤ የተነሳው ለእኔና ለእናንተ ነው ።

ስለዚህ የድነታችን ሚስጥር የተሰወረበት እውነት ነው ። የተከናወነው ልውውጥ ነው ። እርሱ ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ቁስላችንን ወስዶ ፈወሰን ፣ እስራታችንን ወስዶ ፈታን ፣ ስቃያችንን ወስዶ ያሳረፈን፣ ሞታችንንም ወስዶ ህይወት ሰጠን ፣ መቃብራችንን ወስዶ ትንሳኤን ሰጠን በፍጻሜውም የሞትን ጣር አጥፍቶ ተነስቶ አርጎ በአብ ቀኝ ተቀምጦ በአብ ቀኝ ከርሱ ጋር ያስቀመጠን የጌቶች ጌታ የነገስት ንጉስ እርሱ ጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

ስለዚህ ትንሳኤውም የእኔና የናንተ ነው ። ለዚህ ነው በሞቱና እና በትንሳኤው ከርሱ ጋር ለመተባበር የምንጠመቀው ። ይህ የተከናወነው እውነት ምሳሌያዊ መግለጫ አና ከእርሱ ጋር በመተባበራችን በሁሉ ፊት የምንገልጥበት ምስክርነታችን ነው። በመሆኑም ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኔና ስለናንተ በመስቀል ላይ ያከናወነውን ሁሉ ስለ እኛ መሆኑን በማመን የእዳ ጽህፈታችን በርሱ እንደ ተደመሰሰልን አምነን ስንቀበል በርሱ በሆነልን ሥራ ድነታችን ይፈጸማል ። በጥምቀትም ሞቱ ሞታችን ፣ ቀብሩም ቀብራችን፣ ትንሳኤውም ትንሳኤአችን እንደሆነ በመቀበል ከዓለም ተሰናብተን ለአዲስ ሕይወት መለየታችንን እናውጃለን።

ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሆኖ “ተፈጸመ” አለ (ዮሐ 19፡30) “ተፈጸመ” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል “tetelestai" ቴቴሌስታይ ሲሆን ይህ ቃል “ሙሉ በሙሉ ተከፈለ” ማለት ነው ።

1ኛ, የሰው ልጅ የኃጢአት ዕዳው ሙሉ በሙሉ መከፈሉን ነው ያወጀው ። ስለዚህ በርሱ የሚያምኑ ሁሉ ከኃጢያት ዕዳ ነጻ ናቸው።ስለዚህ ይህን እውነት ያላመናችሁ ( 2ኛ ቆሮ 6፥2)

2ኛ,የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ በእውነት ያመኑበት ሁሉ ሞት ትንሳኤ ነው። የሞት መውጊያ ተሰብሯል የሞት መውጊያ ኃጢያት ነው። ( 1ኛ ቆሮ15፥55 )

3ኛ,በአስደናቂ የትንሳኤ እውነት የተረጋገጠ ሞትን የሚሻገር የከበረ ተስፋን የጨበጠ እምነት የክርስትና እምነት እና ሕይወት ብቻ ነው ። እንኳን ክርስቲያን ሆንኩኝ ።

4ኛ,ዛሬም ውድቀታችሁን ለሚጠብቁ መነሳት ይሆናል፣ሞታችሁ ለሚጠብቁ ትንሳኤ ይሆናል ፣ውርደታችሁን ለሚጠብቁ ክብር ይሆናል በሏቸው አውጁ ጠላም ሰዎችም ፍጥረትም ሁሉ ይስማ ።

እግዚአብሔር ትንሳኤያችሁን በግልጽ ያሳያችኃል ! የተመከረባችሁ ምክር አይጸናም ! እንደተደረገባችሁ ክፋት አይከናወንም ! እንደተወራባችሁ ሟርት አይሆንም ! ሰይጣን ያለው ሳይሆን እግዚአብሔር የተናገራችሁ ይፈጸማል። መጪው የአሸናፊነት የድል ጊዜ ፣ የሥኬት እና የመከናወን ጊዜ ይሆናል ።

ፓስተር አለማየሁ አበበ እና ቤተሰቡ
ከረጲ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን
15 views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 23:51:32 https://vm.tiktok.com/ZMYpfNVkt/
19 views20:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ