Get Mystery Box with random crypto!

Assosa online

የቴሌግራም ቻናል አርማ asosaonline — Assosa online A
የቴሌግራም ቻናል አርማ asosaonline — Assosa online
የሰርጥ አድራሻ: @asosaonline
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 802
የሰርጥ መግለጫ

እውነተኛ ታማኝ እና ወቅታዊ መረጃዎችን እናደርሳለን፡፡
ቻናሉን ሼር ኢንቫይት እና ጆይን በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ::

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-26 17:07:02
ቀን 18/08/2014 ዓ.ም
ወደ ሁለቱ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች የ2014 ዓ.ም አዲስ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጥሪ ማስታወቂያ
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በቅድመ-ምረቃ መርሃ ግብር በ2014 ዓ.ም የተመደባችሁ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያው ቀን በሚከተለው መልኩ የተዘጋጀ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡
 ምዝገባው የሚከናወንበት ቀን ሚያዚያ 28 ና 29/2014 ዓ.ም ሲሆን
 ገለፃ የሚሰጥበት ቀን ሚያዚያ 30/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ
 እንዲሁም ትምህርት የሚጀመርበት ቀን እና በቅጣት የመመዝገቢያ ቀን ግንቦት 01/2014 ዓ.ም መሆኑን እየገለፅን
አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲዎቹ ለምዝገባ በምትመጡበት ወቅት መርሳት የሌለባችሁ፡
1) የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን
• የ 10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሰርተፍኬት
• ከ 9ኛ-12ኛ ክፍል የተማራችሁበት ትራንስክሪፕት
2) 4 ፓስፖርት ሳይዝ ፎቶ ግራፍ
3) አንሶላ፣የትራስ ጨርቅ እና ብርድ ልብስ
4) የስፖርት ልብስና ጫማ
ይዛችሁ እንድትመጡ እያሳወቅን ከላይ ከተጠቀሱት የመመዝገቢያ ቀናት ውጪ ቀድሞም ይሁን ዘግይቶ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲዎቹ የማያስተናግዱ መሆኑን አበክረው ይገልፃሉ፡፡
ማሳሰቢያ፡ የዩኒቨርሲቲ ምደባችሁን ለማወቅ የሁለቱን ዩኒቨርሲቲዎች ድህረ ገፅ (www.aastu.edu.et or www.astu.edu.et) መመልከት ትችላላችሁ፡፡
በዩኒቨርሲቲው በኩል የሚተላለፉ ሌሎች መረጃዎችን በዩኒቨርሰቲው መገናኛ ዘዴዎች የምንገልፅ በመሆኑ አባል በመሆን ትክክለኛ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

t.me/asosaonline/666

አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት
832 viewsedited  14:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 16:53:55
Job vacancy announcement
Teachers are required

Millineum College of Medicine will like to hire part time teachers on the following fields

Communicative English
General psychology
Critical thinking and related fields
Geography
Maths
Physics
Physical fitness

For more information join our telegram channel
t.me/asosaonline
576 views13:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 12:49:40 የዩኒቨርሲቲዎችን ትክክለኛ ገፅ ብቻ በመከተል ከሀሰተኛ የዩኒቨርሲቲ ጥሪዎች እራሳችሁን ጠብቁ ፦

ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/DDUniv/

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Hawassa.University/

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Addis-Ababa-University-496255483792611/

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/TheUniversityofGondar/

ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/bduethiopia/?ref=page_internal&mt_nav=0

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/ArbaMinchUniversityCCD/?_se_imp=0ueaW0ZojpEObV9zR

ሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/HRMUNIV/

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/JimmaUniv/

አርሲ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=357578986410375&id=100064748293256

ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፦https://m.facebook.com/pages/category/Education-website/Wolaita-Sodo-University-246568056057804/

ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WachemoUniversity2008/

ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/265529850297666/posts/1845133279003974/?app=fbl

መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/141864125910414/posts/4794315817331865/?app=fbl

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education-website/Wollega-University-Corporate-Communications-2319182621440303/

አሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/234983083247967/posts/5141798579233035/?app=fbl

ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/2181225212102194/posts/3109977289226977/?app=fbl

ቦረና ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/BoranaUniversityBRU/

ቀብሪድሃር ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education/Kebri-Dehar-University-306587496533329/

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/pages/category/Education/Jinka-University-178538809733160/

ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/547073878695780/posts/5065885566814566/?app=fbl

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/1879460055640998/posts/3057857987801193/?app=fbl

ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WoldiaUniversity/

ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/WolloUniversity111/

ደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/1301588393256101/posts/5145148712233364/?app=fbl

ኦዳቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/OBUEthiopia/

አምቦ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/AmboUniversityofficial/

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://m.facebook.com/Mizan-Tepi-University-MTU-362390684253048/

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/614590095253065/posts/5432186613493365/?app=fbl

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/979926502053136/posts/5129611493751262/?app=fbl

ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/336146983089022/posts/5029908297046177/?app=fbl

ኮተቤ ፦ https://www.facebook.com/792405150779154/posts/5397052686981021/?app=fbl

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/100064618752509/posts/386404006856888/?app=fbl

መቱ ዩኒቨርሲቲ ፦ https://www.facebook.com/330316734055129/posts/1468350973585027/?app=fbl

ተጨማሪ ጥያቄዎች ካላችሁ ከታች በአስተያየት መስጫው አስቀምጡ!

https://t.me/asosaonline
https://t.me/asosaonline
546 views09:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-25 09:04:53
የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ

ሚያዝያ 17/2014 ትምህርት ሚኒስቴር የ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ አደረገ።

የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር ዐቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ ለማየት በድረ ገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣ በSMS፡- 9444 እንዲሁም በቴሌግራም፡- @moestudentbot መጠቀም ይችላሉ ነው የተባለው።

ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድረ ገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።

ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢውን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርኃ ግብር የሚያሳውቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል።

ከዚህ በፊት በተገለጸው የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል።
445 views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 16:29:00
#ትንሳኤ

ውድ የክርስትና እምነት ተከታይ የAssosa Online አባላት በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ፤ አደረሰን።

በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን።

በዓሉን ስናከብር ፤ የተቸገሩ ወገኖቻንን አለንላችሁ በማለት ፣ የወደቁትን በማንሳት ፣ በሀዘን ላይ ያሉ ወገኖችን በማፅናናት፣ ከክፉ ድርጊት እና ሀሳብ ርቀን ሊሆን ይገባል።

በዚህ የትንሳኤ በዓል ፤ በሰላም እጦት ፣ በግጭት ፣ በድርቅ ክፉኛ የተጎዱ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በገዛ ቄያቸው ከሞቀው ቤታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ የወደቁትን፤ በፀሃይና ዝናብ የሚንከራተቱትን ፤ የተቸገሩትን ፣ የሚወዱትን ተነጥቀው በጥልቅ ሀዘን ላይ የሚገኙትን ፣ ታመው በየሆስፒታሉ የተኙትን ፣ በየሰው ሀገር በስደት ስቃያቸውን እያዩ ያሉ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በግልም ፤ በሀገርም ላለብን ችግር ሁሉ አምላክ መፍትሄ እንዲያበጅልን እየተማፀንን እንድናሳልፍ አደራ እንላለን።

የሰላም፣ የመተሳሰብና የበረከት በዓል ያድርግልን !
ፈጣሪ ሀገራችን ሰላም ያድርግልን ፤ በምድር ላይ ያሉ የሰው ልጆችን ሁሉ ይጠብቅልን።

መልካም በዓል !
#asosaonline
452 views13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-20 11:41:09 በዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ላይ እርማት እንዲደረግ በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ጠየቀ።
በአማራ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም ዛሬ ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ የ12ኛ ክፍል መግቢያ ፈተና እና ውጤት ላይ እርማት እንዲደረግ ጠይቋል።
የመግቢያ ፈተናውን ውጤት ተከትሎ የሚወጡት መረጃዎች ያልተለመዱና አስደንጋጭ ናቸው ያለው የአማራ ክልል ዩኒቨርሲቲዎች ፎረም በተወሰኑ ተማሪዎችና ወላጆች ግፊትና ጫና የተስተካከሉ ውጤቶች ለተፈጠረው ስሕተት ኹነኛ ማሳያዎች ናቸው ብሏል።
የአማራ ትምህርት ቢሮ የኹሉንም ትምህርት ቤቶች ውጤት ዝርዝር መረጃ በመሰብሰብ ለትምህርት ሚኒስቴርና ለሕዝብ ይፋ ማድረግ እንደሚገባው የጠቆመው ፎረሙ ትምህርት ሚኒስቴርና የፈተናዎች ድርጅት ለችግሩ ትኩረት ሰጥተው ለማረም እድል ያገኛሉ ብሎ እንደሚያምን በደብዳቤው ገልጿል።
በተማሪዎችና ወላጆች እየቀረበ ያለውን ጥያቄ ሁሉም ወገን በቅንነት ተቀብሎ የድጋሜ እርማትን እንዲሁም ተጨማሪ ማጣራት ማድረግ በዜጎች ዘንድ ፍትሐዊነትና ተዓማኒነት ከማረጋገጡም በላይ ለሀገር ሰላምና መረጋጋት ይጠቅማል ሲልም ፎረሙ አሳስቧል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተናውና ውጤቱ ላይ እየተነሱ ያሉ ጥያቄዎች እንደ ፖለቲካ ጥያቄ አቻችሎና ሰምቶ በመተው የሚፈቱ ሳይኾን የትውልዱን እድል የሚወስኑ በመኾናቸው በፍጹም አካዳሚያዊ ሥነ ምግባርና ከፍተኛ መኾን አለበት ብሏል ፎረሙ።
ፎረሙ በጻፈው ደብዳቤም ኹሉም አካላት ችግሩ መፍትሔ እንዲያገኝ ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ጠይቋል።
ፈተና በደቦ እየተሠራ መልካም ትውልዶችን መፍጠር አይቻልም ያለው ተቋሙ ጉዳዩ ከብሔር አውድ ፍፁም ነጻ እንዲኾን ኹሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት እንዲሠሩ ጠይቋል።
ተማሪዎችና ወላጆች ጥያቄው መልስ እስኪያገኝ ተረጋግተው እንዲጠብቁም ጥሪ አቅርቧል።
(አሚኮ)
t.me/asosaonline
766 views08:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-13 15:44:07
ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ጋዜጣዊ መግለጫ!

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎችና በርካታ ተመልካቾች በተሰበሰቡበት አስክሬኖች እና አንድ በሕይወት የነበረ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ እሳት ውስጥ ሲጨመር የሚያሳይና በማኅበራዊ ሚድያ በተሰራጨ የቪድዮ ምስል በደረሱት ጥቆማዎች መሰረት ስለሁኔታው አፋጣኝ ማጣራት አድርጓል።

ኢሰመኮ ምስክሮችን በማነጋገር እንዳጣራው ክስተቱ የተፈጸመው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በጉባ ወረዳ አይሲድ ቀበሌ ውስጥ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. መሆኑን፣ ከዳኝነት ውጪ የተፈጸመ ግድያ (extra-judicial killing) እና አስከሬኖችን አንድ በሕይወት ከነበረ ሰው ጭምር የማቃጠል ድርጊቱ የተፈጸመው በመንግሥት የፀጥታ አባላትና ሌሎችም ሰዎች ተሳትፎ ጭምር የነበረ መሆኑን አረጋግጧል። እንዲሁም ለዚህ ክስተት መነሻ ስለሆነው ድርጊቱ ከተፈጸመበት አንድ ቀን በፊት ቢያንስ በ 20 የመንግሥት ፀጥታ አባላት እና በሲቪል ሰዎች ላይ በታጣቂዎች ስለተፈጸመው ግድያ ሁኔታም አረጋግጧል፡፡

የካቲት 23 ቀን 2014 ዓ.ም. በመተከል ዞን፣ በጉባ ወረዳ፣ አይሲድ ቀበሌ፣ አፍሪካ እርሻ ልማት ማኅበር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ገደማ፣ ከግልገል በለስ ከተማ በመኪና ተሳፍረው፣ በአካባቢው ካለው የደኅንነት ስጋት አንጻር በተለመደው አሰራር መሰረት በመከላከያ ሠራዊት ታጅበው ወደ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ፤ ወደ ማንኩሽና ወደ አሶሳ ከተማ ሲጓዙ የነበሩ ሰዎች ላይ ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ፈጸሙ። በጥቃቱም 1 መኪና አሽከርካሪ፣ 1 በንግድ ሥራ የሚተዳደሩ ሰው እና 1 መምህር በአጠቃላይ 3 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል፤ መንገደኞቹን አጅቦ በመጓዝ ላይ የነበሩት የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኪና በከባድ መሳሪያ ተመትቶ ሻለቃ አመራሩን ጨምሮ ቢያንስ 20 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ሞተዋል፣ እንዲሁም 14 የመከላከያ ሠራዊት አባላት ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡

በዕለቱ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችና እና ጥቃቱን በፈጸሙ የታጠቁ ኃይሎች መካከል የተደረገው ውጊያ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 12፡00 ሰዓት የቆየ ሲሆን፣ በማግስቱ የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ተጨማሪ የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በቦታው ደርሰው ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ በቆየ የተኩስ ልውውጥ ከታጣቂዎቹ መካከል ወደ 30 የሚሆኑ መገደላቸውንና ቀሪዎቹ ታጣቂዎች መሸሻቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡

ይህንን ተከትሎ የመከላከያ ሠራዊት የመንግሥት ፀጥታ አባላቱና የሲቪል ሰዎች መንገደኞች መኪኖች የካቲት 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ አይሲድ ከተማ ደረሱ። በተከሰተው አደጋም የከተማው ፀጥታ ሁኔታ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደነበር የአካባቢው ነዋሪዎች ያስረዳሉ።

የመንግሥት የፀጥታ አባላቱ አግኝተናል ባሉት ጥቆማዎች መሰረት በአካባቢው በነበሩ ተሽከርካሪዎችና በመኖሪያ ቤቶች ላይ እንዲሁም ከግልገል በለስ ከተማ ወደ ማንኩሽና ባምዛ የሚጓዙ የነበሩ ሲቪል ሰዎች ላይ ፍተሻ ማካሄድ ጀመሩ።

በፍተሻው ሂደት ውስጥ በቅርቡ ከእስር ተፈትተው ከመተከል ዞን ማረሚያ ቤት የይለፍ ወረቀት በመያዝ ወደ መኖሪያቸው የተመለሱና የአካባቢው ነዋሪዎች የነበሩ 8 የትግራይ ተወላጆችን “እናንተ ናችሁ መረጃ ሰጥታችሁ ጥቃቱን ያስፈጸማችሁት” በማለት ከተሳፈሩበት መኪና እንዳስወረዱና በፍተሻውም አንድ የወታደራዊ መገናኛ ሬዲዮ፣ የተለያዩ ፎቶግራፎች እና ከ40,000 ብር በላይ ገንዘብ እንደተገኘ ተገልጿል። የመንግሥት ፀጥታ አባላቱም ተጠርጣሪዎቹን እየደበደቡ ተጨማሪ መረጃ መጠየቅ ጀመሩ።

ከዚህ ተከትሎም ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ “በአካባቢው በተፈጸመው ጥቃት ላይ እጃችን አለበት፤ ባምዛ በሚባለውና በግልገል በለስ ቦታዎች ሰዎች አሉን” ማለቱን ተከትሎ፣ የመንግሥት የፀጥታ ኃይል አባላቱ ሁኔታውን የተቃወሙ ሁለት የጉሙዝ ተወላጆችን ጨምሮ 10 ሰዎችን ተኩሰው ገድለዋል።

ከዚህ በመቀጠልም የፀጥታ ኃይል አባላቱ የተገደሉትን ሰዎች አስከሬኖች ከከተማዋ ወጣ ብሎ ወደሚገኝ ጫካ ስፍራ በመውሰድ አስክሬናቸውን ማቃጠል መጀመራቸውን የዓይን ምስክሮች አስረድተዋል። በዚህ መካከልም ከተጠርጣሪዎቹ ተገዳዮች ጋር ግንኙነት አለው የተባለን አንድ ሌላ የትግራይ ተወላጅ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሳፈረበት መኪና ውስጥ ተደብቆ በጥቆማ ካገኙት በኋላ በገመድ አስረው በመውሰድ ቀድሞ በመቃጠል ላይ ከነበሩት አስክሬኖች ላይ እንደጨመሩት እና በእሳት ተቃጥሎ እንደሞተ ምስክሮች ለኮሚሽኑ አስረድተዋል፡፡

በአካባቢው የነበሩት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች የመከላከያ ሠራዊት አባላት፣ የአማራ ክልል ልዩ ፖሊስ አባላትና የደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ልዩ ፖሊስ አባላት ሲሆኑ፤ በአጠቃላይ ሁኔታው በቀጥታ ድርጊት በመፈጸም ወይም አስገዳጅ ተግባሮችን ባለመፈጸም (by commission or omission) የነበራቸው የተለያየ የተሳትፎ መጠን በተጨማሪ የወንጀል ምርመራ ሊጣራ የሚገባው ነው፡፡

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ እንደገለጹት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እጅግ ፈታኝ በሆኑ አካባቢዎች በከፍተኛ መስዋዕትነት የሕዝብ ደኅንነት የሚጠብቁ መሆኑ የማይዘነጋ ሕዝባዊ አገልግሎት መሆኑ እንደሚታወቅ ገልጸው፤ ሆኖም ግን በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ከዳኝነት ሂደት ውጭ መግደል እና በተለይም በእሳት አቃጥሎ መግደል ፈጽሞ ከሕግ አስከባሪ አባሎች የማይጠበቅ ግፍና ጭካኔ የተሞላበት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በመሆኑ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በተጠርጣሪዎች ላይ ተገቢውን የወንጀል ምርመራ በአፋጣኝ
እንዲደረግ አሳስበዋል።

ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አክለውም “የመንግሥት ሕግ አስከባሪ አባሎች እራሳቸው በግልጽ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ፈጻሚዎች ሆነው መታየታቸው፤ ሰዎች በሕጋዊ ሥርዓት ላይ የሚኖራቸውን እምነት የሚሸረሽርና ለተጨማሪ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የሚያጋልጥ በመሆኑ፤ መንግሥት የምርመራውን ሂደትና ውጤት በተመለከተ የተሟላ መረጃ
ለሕዝብ ይፋ ሊያደርግና ፍትሕን ለማረጋገጥም የሟች ቤተሰቦችን ሊክስ ይገባል” ብለዋል።

@asosaonline
@asosaonline
702 views12:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-07 14:03:00
#Dessie

ደሴ ከተማን ሙሉ በሙሉ ማዳረስ የሚያስችል ከ605 ሺህ ሊትር በላይ ዘይት ከፌቤላ የዘይት ማምረቻ ኢንዱስትሪ ጋር በመተባበር በተያዘው ሳምንት ለነዋሪዎች እንደሚከፋፍል የከተማዋ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

የዘይት አቅርቦቱ በ 'ሸማች ማህበር' በኩል ይቀርባል የተባለ ሲሆን በገበያው ላይ የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለመከላከል የቁጥጥር ስራም እየተሰራ ነው ተብሏል።

በከተማዋ በሸማች ማህበራት በኩል የሚቀርበው የዘይት ዋጋ ፡-

1. ባለ 3 ሊትር 290 ብር ከ06 ሳንቲም

2. ባለ 5 ሊትር 474 ብር ከ40 ሳንቲም

3. ባለ10 ሊትር 936 ብር ከ69 ሳንቲም

4. ባለ 20 ሊትር 1 ሺህ 834 ብር ከ66 ሳንቲም

5. ባለ 25 ሊትር 2 ሺህ 277 ብር ከ90 ሳንቲም መሆኑ ተገልጿል፡፡

t.me/asosaonline
611 views11:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-07 13:20:49 ማስታወቂያ
ለትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ:-
የአሶሳዩ ኒቨርሲቲ በማታና ቅዳሜና እሁድ ትምህርት መርሃ ግብር በመጀመሪያ ድግሪ ፕሮግራም በአሶሳ፣ በ2014 ዓ.ም መማር ለምትፈልጉ አዲስ አመልካች የመጀመሪያ ድግሪ ከየካቲት 24/2014 ዓ.ም እስከ መጋቢት 15/2014 ዓ.ም በተከታታይ የስራ ቀናት ምዝገባ ይካሄዳል፡፡
በመሆኑም ለመጀመሪያ ዲግሪ አመልካቾች አድሱ ሥርዓተ ትምህርት ፕሮግራሙ በተፈጥሮ ሳይንስ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስክ መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ከላይ በተጠቀሱት ቀናት በአካል ወይም በተወካይ በኩል በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ሪጅስትራል ኦርጅናል ዶክመንትና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በማቅረብ ለመጀመሪያ ዲግሪ ለአሶሳ አመልካቾች 100 ብር በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዩኒቨርሲቲው የውስጥ ገቢ አካውንት 1000021168355 በመክፈል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ዩኒቨርሲቲው የሚሠጣቸው የትምህርት መስኮች
በመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራም
1. በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ (College of Business and Economics)
ማናጅመንት (management)
አካውንቲግ (Accounting)
ኢኮኖሚክስ (Economics)
ህዝብ አስተዳደር ልማት ስራ አመራር (Public Administration Development Management)
ቱሪዝም ማናጅመንት (Tourism Management)
2. በማህበራዊሳይንስናስነ-ሰብኮሌጅ (College of social science and humanities)
ጅኦግራፊ (Geography)
ሥነ-ዜጋ (Civic)
እንግሊዝኛ (English)
ሳይኮሎጂ (Psychology)
ሶሾሎጂ(Sociology)
ጋዜጠኝነት እና ስነ -ተግባቦት (Journalism and Communication)
3. በተፈጥሮ ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ /College of Natural and computational science /
ባዮሎጂ (Biology)
ኬሚስትሪ (Chemistry)
ፊዚክስ (Physics)
ስፖርትሳይንስ (sport science)
ሒሳብ (Mathematics)
እስታትስቲክስ (Statistics)
ጅኦሎጂ (Geology)
4. በምህንዲስና ኮሌጅ (College of engineering)
ሲቪልመህንዲስና (Civil engineering)
ኤሌክትሪክና ኮምፒውተር ምህንዲስና (Electrical and computer engineering)
ግንባታና ቴክኖሎጂ አመራር (Construction Technology Management )
ቅየሳ ምህንዲስና (Survey engineering)
ውሃ ሀብት ምህንዲስና (water resource and irrigation engineering)
-መካኒካል እንጂነርግ (Mechanical Engineering)
5. በኮምፒውቲግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ (College of computing and informatics)
ኮምፒውተር ሳይንስ (Computer science)
ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ (Information Technology)
ኢንፎርሜሽን ሳይንስ (Information Science)
6. በግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ኮሌጅ (College of agriculture and natural resources)
እፅዋት ሳይንስ (Plant science)
እንስሳት ጤና (Animal health)
ተፈጥሮ ሀብት አያያዝ (Natural resource and management )
እንስሳት ሳይንስ (Animal science)
ግብርና ምጣኔ ሀብት (Agricultural economics)
አፈር ሀብት እና ተፋሰስ አያያዝ (soil Resource and watershed management)
7. በህግ ትምህርት ቤት /school of law /
 በህግ /LLB in Law /
የመመዝገቢያ መስፈርት
ለመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ሚኒስቴር የመግቢያመስፈርት
በሌቨል ለተመረቁደረጃ 3 እና 4 ሲኦሲ ውጤት ከለላቸው እስከ አንድ አመት ድረስ ለማቅረብ ውል በመግባት ማመልከት የሚችሉ ሲሆን የመምህራን ሰልጣኞችን አይመለከትም
 የቀድሞ 12ኛክፍልከሆኑለወንዶች 3.2 ለሴቶች3.0
 2013/14 ዓ/ም ያጠናቀቃችሁ ከ700 የተፈተናችሁ 350 እና ከዚያ በላይ ከ600 የተፈተናችሁ 300 እና ከዚያ በላይ ውጤት ማስመዝገብ ይኖርባችኋል፡፡
 2012/13 ዓ/ምለወንዶች 330 እናለሴቶች 320 እናለታዳጊክልሎችበሁለቱምጾታ 310፤ለአካልጉዳተኛ 300
 2011 ዓ/ም 140 እና ከዚያበላይ
 2008-2010ዓ/ም 295 እና ከዚያበላይ
 2007 ዓ/ም 295 እና ከዚያበላይ
 2006ዓ/ምተፈታኞች 250 እና ከዚያበላይ
 2003-2005 ዓ/ምተፈታኝ 265 እና ከዚያበላይ
 2002 ዓ/ም 280 እና ከዚያበላይ
 2001-200 እና ከዚያበላይ ሊኖራቸው ይገባል
ለመጀመሪያ ዲግሪ አመልካቾች መማር የምትፈልጉትን ድፓርትመንት በመምረጥ ማመልከት ይኖርባችኋል
ምልመላውን ላለፉ ሰልጣኞች በውስጥ ማስታወቂያ የመመዝገቢያ ቀን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ 0578875023 በመደወል መረጃ ማገኘት ይቻላል::
የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የተከታታይና ርቀት ትምህርት ፕሮግራም ዳይሬክቶሬት
@asosaonline
504 viewsedited  10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-06 13:45:12
#BahirDar

በባህር ዳር የምግብ ዘይት መሸጫ ዋጋ ይፋ ሆነ።

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ንግድ መምሪያ የምግብ ዘይት መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

ከነገ ከ28/06/2014 ዓ.ም ጀምሮ መሰራጨት የሚጀምረው ፓልም ዘይት መግዣና መሸጫ ዋጋ መረጃ ይህንን ይመስላል ፦

ቸርቻሪዎች / ሸማቾች ህ/ስ/ማ ከአለ በጅምላ የሚገዙበት የጅምላ ዋጋ ፦

1. ባለ 20 ሊትር 1575.6 ብር ፣
2. ባለ 5 ሊትር 408.6 ብር፣
3. ባለ 3 ሊትር 251.10 ብር ሲሆን፣

ቸርቻሪዎች / ሸማቾች ህ/ስ/ማ #ለተጠቃሚው_ማህበረሰብ የሚያሰራጩበት ዋጋ ደግሞ ፦

1. ባለ 20 ሊትር 1641.80 ብር ፣
2. ባለ 5 ሊትር 425.80 ብር፣
3. ባለ 3 ሊትር 261.70 ብር መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር

@asosaonline
450 views10:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ