2022-05-22 10:21:19
May 22
የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 4 መጻህፍ ላይ "የአንዳምንን ስልጣኔ ማውደም!" የሚል ተልዕኮ ተሰጥቶዋቸው እሱኑ ሊያስፈጽሙ የመጡ 180 ዜጎች (ማለትም 90 ሴቶችና 90 ወንዶች) ምልምል ኢትዮጵያውያን ባለስልጣናት እንዳሉ ተገልጾዋል::
እነዚህ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ መንግስታዊ ሴክተሮች በስልጣን ላይ እና በስራ ላይ የነበሩ ሲሆኑ (ወደፊት ከሚደረገው) ከመንግስት ለውጥ በሁዋላ (ኦልሬዲ ለውጡ ተደርጎዋል) ዋና ዋናውን የመንግስትነት ስልጣን ይዘው እንዲቀጥሉ የታጩ ናቸው::
እነዚህም ቀደም ብለው ተመልምለው ለትምህርት ለስልጠና ለወዘተ... በሚል ወደ ውጭ አገር የሄዱና በሲ.አይ.ኤ.እና በመሰል ዓለም አቀፍ ተቁዋማት አማካኝነት በልዩ ሁኔታ የሰለጠኑና በ2014 እ.ኤ.አ ልዩ እና ረቂቅ የተባለውን ስልጠናቸውን አጠናቀው ተመርቀው የተላኩ ናቸው::
እነርሱም ከለውጡ በሁዋላ በየዘርፉ ተሰማርተው ዓላማቸውን የሚከውኑ; የማይተዋወቁ መስለው ነገር ግን ተናብበው የሚሰሩና የተሰጣቸውን ተልዕኮ በየዘርፉ ተሰማርተው ሊፈጽሙ በእንግሊዙዋ ንግስትና በG20 አገራት መሪዎች ፊት የደም ቃል ኪዳን የፈጸሙ እንደሆኑ በመጽሃፉ ተገልጾዋል::
ከተልዕኮዋቸው ውስጥም አንዱና ዋናው "የአንዳምንን ስልጣኔ ማውደም!" የሚል ነው::
"የአንዳምንን ስልጣኔና አራማጆቹን ማፍረክረክ! ማሽመድመድና ማውደም! የሚለው......... ከተልዕኮዋቸው ውስጥ አንዱና ዋናው ነው::
ይህም በዋናነት ሐይማኖተኛውንና ሴሜቲኩን ህዝብ የሚመለከት ሲሆን; በዋናነት "ነጻ ህዝብ" ብለው የሚጠሩትን የአምሐራ እና ትግራይን ብሄር መንግስታዊ በሆኑና ባልሆኑ ልዩ ልዩና ሁሉን አቀፍ በሆኑ ዘርፈ ብዙ ዘመቻዎች ማፍረክረክ, ማሽመድመድና ከጥቅም ውጭ ማድረግ...!" የሚለው ይገኝበታል::
ይህ ከመሆኑ በፊት ግን በፖለቲካ ሰበብ የትግራዩን ሴሜቲክ ህዝብ ቀድሞ ማፍረክረክ እንደሚያስፈልግ, ሁለቱን ህዝብም እስከመጨረሻው ማቆራረጥ ግዴታ እንደሆነና ይህም በቅርቡ እንደሚደረግ, በስልጣን ያለውን መንግስትም (ህወሃትን) ማፍረስ ግድ እንደሆነና ያንንም እንደሚያደርጉ; ከዚሁ ጋርም አገሪቱን የኢኮኖሚ ቅኝ ተገዥ ያደረጋትን የገዥውን ፓርቲ ኤፈርት የተባለ ድርጅት ማፍረስ እንደሚያስፈልግ ከ ቁጥር 4 ቱ መጻህፍ በፊት በተጻፈው በቁጥር 3 ቱ መጻህፍ ተገልጾ ነበር::
ኢትዮጵያን በሚመለከት ጉባዔተኞቹ እ.ኤ.አ በ2014 ዓ.ም በአሜሪካ ኒዮርክ, በአውስትራሊያ ሜልቦርን እና በቤልጀም ብራሰልስ አዳራሾች በዝግ ጉባዔያቸው በዶለቱት መሰረትም ብዙዎቹን እቅዶቻቸውን ወደ ተግባር መለወጥ ጀምረዋል::
ኢትዮጵያን በሚመለከት አጠቃላይ እቅዳቸውን በኛ አቆጣጠር በ2007 ዓ.ም ለህትመት ከበቃው "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ" ከሚለው ከመጀመሪያው መጻህፍ እና የዚያ መጻህፍ ተከታይ ክፍሎች ሆነው ተከታትለው ከወጡት "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 1, "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 2," "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 3" እና "የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ ቁጥር 4" በተሰኙት መጻህፍት አጠቃላይ እቅዳቸው በሙሉ በሰፊውና በዝርዝር እንዲሁም ቃል በቃል ተገልጾዋል::
በበኩሌ እነዚህን አራት መጻህፍት ገዝታችሁ እንድታነቡዋቸው ብቻ ሳይሆን በየሸልፋችሁ እንዲገኙ ከመምከር አልፌ ማሳሰብ እፈልጋለሁ!
ይህን የምለውም በምክንያት ነው እውነታው ያለው በእነዚህ መጻህፍት ውስጥ ስለሆነ ነው!በዚህም እርግጠኛ ስለሆንኩ ነው!
ኢትዮጵያን በሚመለከት በኅያላን አገራት መንግስታት በኩል ወደፊት የታቀደው ወይም የተደገሰው ምን እንደሆነ ለመረዳት ብቸኛ ምርጫችሁ እነዚህ መጻህፍት እንደሆኑ እርግጠኛ ሆኘ እነግራችሁዋለሁ!
"ለምን ኢትዮጵያን? እንዴት ኢትዮጵያን? ይቺን ተራ እና ምስኪን አገር በዚህ ደረጃ ማጥመድ ለምን አስፈለገ? ከኢትዮጵያ ምን ፈልገው?" ወዘተ... የሚሉ ጥያቄዎችን መረዳትም ሆነ ትክክለኛ ምላሻቸውን ማግኘት የሚቻለው በርግጥ በእነዚህ መጻህፍት ነው!
ማመን ያለማመን የእናንተ መብት ነው! ነገር ግን መጻህፍቱን እዩዋቸው አንብቡዋቸው!
የተጻፉትን አንዳንድ ነገሮች ዛሬ ላይ ላታምኑ ትችላላችሁ:: ነገር ግን የተጻፉት ነገሮች ወደ ተግባር ሲለወጡ ስታዩ ማመናችሁ ስለማይቀር ማንበብ ባትፈልጉ እንኩዋን መጻህፍቱን ይዛችሁዋቸው ቆዩ ብዬ በልበ ሙሉነት እመክራለሁ!
ሁሉም መጻህፍት ደግሞ እጅግ ቅናሽ በሆነ ዋጋ ገበያ ላይ የሚገኙ ናቸውና ፈጥናችሁ እዩዋቸው እላለሁ::
በቅርቡ ቁጥር 1, ቁጥር 2, ቁጥር 3, በተራኪ አፕ ተዘጋጅተው ሊቀርቡ እንደሆነ መረጃው አለኝ::
እስከዚያው ግን ቁጥር 4 ላይ አንዳንድ መረጃዎችን እየያዛችሁ ትቆዩ ዘንድ ያለ በቂ ዝግጅትም ቢሆን ወቅታዊ ክንውኖች ላይ በማተኮር አንዳንድ ሃሳቦች በወፍ በረር የሚተረኩበትን ይህን ቻናል ጆይን አድርጋችሁ እንዳንድ አሳቦችን እንድታደምጡ ተጋብዛችሁዋል::
ለምሳሌ "የአንዳምንን ስልጣኔ ማውደም!" ሲሉ ምን ማለታቸው ነው? "አንዳምን" የሚሉት ምኑን ነው? የሚለውን ነገር የቫቲካኑ ጳጳስ እንዲህ ሲሉ ገልጸውታል::
በመጽሃፉ ውስጥ ያለው "የአንዳምንን ስልጣኔ ማውደም" የሚል ገለጻቸው ያለ በቂ ዝግጅት በአጭሩ እንዲህ ተተርኮዋልና አድምጡት::
Stay_safe_and_Keep_your_distance_from_Vaccination
Stay connected and keep sharing.
https://t.me/joexo00
1.1K viewsTheotokos, 07:21