2022-02-24 21:34:06
አጫጭር መረጃዎች የዩክሬን-ራሺያን ቀዉስ በተመለከተ
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ዜጎች እንዲዋጉ ጥሪ በማቅረብ መሳሪያ ለሚፈልጉት ሁሉ እንደሚሰጥ እና ዩክሬን ታሸንፋለች በማለት ተናግረዋል፡፡በተጨማሪም ጊዜያዊ የጦር አስተዳደር አውጀዋል።
እንግሊዝ ዋና ዋና የሩሲያ ባንኮች ንብረታቸው እንዲታገድ እና ከዩናይትድ ኪንግደም የፋይናንስ ስርዓት እንዲገለሉ የሚያስቻ ውሳኔ አሳልፋለች።በሌላ በኩል የእንግሊዝ የተቃዋሚው ሌበር ፓርቲ መሪ ሰር ኪር ስታርመር ዩክሬን የጦር መሳሪያ ያስፈልጋታል ሲሉ ተናግረዋል።
የሩስያ ፖሊስ ጦርነቱን ተቃውመው ሰልፍ የወጡ ከ650 በላይ ሰዎችን ማሰሩን የተቃውሞ ተቆጣጣሪ ቡድን ኦቪዲ-ኢንፎ አስታውቋል። ቡድኑ ሞስኮን ጨምሮ በ40 የተለያዩ ቦታዎች ሰልፎች መካሄዳቸውን ይፋ አድርጓል።
ሩሲያ 74 የዩክሬን ወታደራዊ ተቋማትን ማውደሟን አስታዉቃለች።የሩስያ የመከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው በዛሬዉ እለት በዩክሬን የሚገኙ 74 ወታደራዊ መሠረተ ልማት አውታሮችን ያወደሙ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 11 የበረራ ማኮብኮቢያና ማረፊያ መውደማቸውን ኖቮስቲ የዜና ወኪል ዘግቧል።
የዩክሬን ዋና ከተማ ኪየቭ ከንቲባ በከተማው የሰዓት እላፊ ጥለዋል፡፡የኪየቭ ከንቲባ የቪታሊ ክሊችኮ ለሩሲያ ጥቃት ምላሽ ለመስጠት በዩክሬን ዋና ከተማ የሰዓት እላፊ መታዘዙን የተናገሩ ሲሆን የከተማዋ ነዋሪዎች በመኪና ለመሸሽ ሲሞክሩ የሚያሳዩ ምስሎችን መሰራጨቱን ተከትሎ ነዉ፡፡
የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃልኪዳን ኔቶ ዋና ጸሀፊ ስቶልተንበርግ ኔቶ ወታደሮቹን ወደ ዩክሬን የመላክ እቅድ የለውም ሲሉ ተናግረዋል፡፡ኔቶ በዩክሬን ውስጥ ምንም ወታደር እንደሌለው በመግለጽ በሞስኮ ወረራ ምክንያት አዲስ ማዕቀብ የሚጣልበት የአውሮጳ ህብረት አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚኖር ተናግረዋል፡፡
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት ስብሰባ ጠርተዋል፡፡ብሄራዊ የጸጥታ ምክር ቤቱ እንዲሰበሰብ የተፈለገዉ በዩክሬን ጉዳይ ለመወያየት መሆኑን የዋይት ሀውስ ባለስልጣናት አስታዉቀዋል፡፡
የሩሲያ የማዘጋጃ ቤት ተወካዮች፣ ጋዜጠኞች እና ሳይንቲስቶች ወረራውን የሚቃወሙ ግልፅ ደብዳቤን ፅፈዋል። የሞስኮ፣ ሴንት ፒተርስበርግ፣ ሳማራ እና ቮልጎግራድ ከተሞችን ጨምሮ ከ180 በላይ የማዘጋጃ ቤት ተወካዮች የፑቲንን ዩክሬን የመውረር ውሳኔ አጥብቀው አውግዘዋል።
የዩክሬን ጦር ወደ 50 የሚጠጉ የሩስያ ወታደሮችን ገድያለሁ እና ቢያንስ 6 የሩሲያ አውሮፕላኖችን መመታቱን ቢያሳዉቅም በገለልተኛነት አካል ግን አልተረጋገጠም፡፡
የዩናይትድ ኪንግደም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከሩሲያ አምባሳደር ጋር 'አስጨናቂ' ውይይት ማድረጋቸዉን ተናግረዋል፡፡
የዩክሬንን ሰማያዊ እና ቢጫ ባንዲራ የያዙ ሰልፈኞች ጸረ-ሩሲያ መፈክሮችን በማሰማት በለንደን ኋይትሆል ከዳውኒንግ ስትሪት ፊት ለፊት ተሰብስበዋል።"አሸባሪ" እና "ነፍሰ ገዳይ" ከሚሉት ቃላት ጎን ለጎን የቭላድሚር ፑቲን ምስል የያዙ ሰልፈኞች በስፍራዉ ድምጻቸዉን አሰምተዋል፡፡
የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሩሲያ ለውይይት ዝግጁ ትሆናለች ሲሉ ተናግረዋል፡፡እንደ አለመታደል ሆኖ ምዕራባውያን ጓደኞቻችን ዓለም አቀፍ ህግን አያከብሩም፣ ለማጥፋት እና ደንቦችን መሰረት ያደረገ ስርዓት የሚሉትን ለማስተዋወቅ አይሞክሩም ሲሉ ላቭሮቭ ተናግረዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ፈረንሳይ ከዩክሬን ጎን እንደምትቆም እና ሩሲያ በጎረቤቷ ላይ የምታደርሰው ወረራ ለአውሮጳ አህጉር ዘላቂ እና ጥልቅ መዘዝ እንደሚያስከትል አስጠንቅቀዋል፡፡
የዩክሬን ዲፕሎማት ከጎናችን ቆመሻል በማለት ኬንያን አመሰግናለሁ ሲሉ ተናግረዋል፡፡በናይሮቢ የዩክሬን አምባሳደር አንድሪ ፕራቬድኒክ በእነዚህ አስቸጋሪ ጊዜያት የምታደርጉትን ድጋፍ በጣም እናደንቃለን ብለዋል።
የዩክሬን የድንበር ባለስልጣናት እንደተናገሩት የሩሲያ ሃይሎች ወደ ዩክሬን ኪየቭ ክልል እና ዚዮቶሚር ወደ ሚባለዉ ክልል ለመግባት እየሞከሩ ነው ሲሉ አስታዉቀዋል።
ከ4,000 የሚበልጡ ሰዎች በተለይም ሴቶች እና ህጻናት እስካሁን ዩክሬን ለቀው ወደ ሞልዶቫ የተሰደዱ ሲሆን እዚያው ሞልዶቫ ለመቆየት ወይም ወደ ሮማኒያ ሊሻገሩ እንደሚችሉ ተናግረዋል።
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ዜለንስኪ አማካሪ ኦሌክሲይ አሬስቶቪች ሞስኮ ጥቃት በከፈተች በሰአታት ውስጥ ከ40 በላይ የዩክሬን ወታደሮች ሲገደሉ፣ በርካቶች መቁሰላቸው እስከ 10 የሚደርሱ ንፁሀን መገደላቸውን ተናግረዋል።
@bbc_amharic1
53 views18:34