Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-11-27 19:48:19 እውነተኛው የአዲስ ኪዳን ታቦት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው የምንለው ይህንን መሠረታዊ የሆነ የቃሉን እውነት ይዘን ነው ! እርሱንም በሕያው መቅደሱ በልባችን ጽላት ላይ አንግሰነዋል ኢየሱስ ክርስቶስን በብሉይ ኪዳን የተተነበየለት÷ በወንጌላት የተገለጠ÷ በሐዋርያት የተሰበከ÷ በራዕይ በክብር የተገለጠ ! ጌታችን መድኃኔታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው ። ኢየሱስ ክርስቶስ ብቸኛው አዳኝ እውነት መንገድና ሕይወትም !( ዮሐ 14:-6)
10 views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-27 19:48:19 ፈጥናችሁ ወደ ሚሻለው ኪዳን ተሻገሩ !

ክፍል ስድስት

1ኛ ,መቅደሱ ተቀይሮአል !

" የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንደ ሆናችሁ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንዲኖርባችሁ አታውቁምን?
ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።"
(1ኛቆሮ 3:-16-17 )

2ኛ, ታቦቱ ተቀይሮአል !

" እናንተም በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ እንጂ በቀለም አይደለም፥ ሥጋ በሆነ በልብ ጽላት እንጂ በድንጋይ ጽላት ያልተጻፈ፥ በእኛም የተገለገለ የክርስቶስ መልእክት እንደ ሆናችሁ የተገለጠ ነው።በክርስቶስም በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ያለ እምነት አለን።"(2ኛቆሮንቶስ 3:-3-4)
" ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።"
(ወደ ዕብራውያን 8:7)
" አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል።"(ወደ ዕብራውያን 8:13)

3ኛ, ደሙ ተቀይሮአል !

" የዘላለምን ቤዛነት አግኝቶ አንድ ጊዜ ፈጽሞ ወደ ቅድስት በገዛ ደሙ ገባ እንጂ በፍየሎችና በጥጆች ደም አይደለም።"(ዕብራውያን 9:12)
" ነገር ግን እርሱ በብርሃን እንዳለ በብርሃን ብንመላለስ ለእያንዳንዳችን ኅብረት አለን፥ የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።"(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:7)

4ኛ , ካህናቱ ተቀይረዋል !

አሁን በክህነት የሚያገለግለው የሌዊ ነገድ ሳይሆኑ በክርስቶስ አምነው የዳኑ ሁሉ ናቸው :: ሊቀ ካህኑም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ::
" እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤"(1ኛ የጴጥሮስ 2:9)
" ሕጉ ድካም ያላቸውን ሰዎች ሊቀ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣ የመሐላው ቃል ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ይሾማል።
"(ወደ ዕብራውያን 7:28)

5ኛ, ሕግ በጸጋ ተተክቶአል !

" አሁን ግን በሕግና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤"(ሮሜ 3:-21-22)

6ኛ, ፊተኛው ኪዳን የተባለው:-

በብሉይ ኪዳን የተገለጸው በሲና ተራራ ለሙሴ የተሰጠው የመጽሐፍ ቅዱሱ ታቦት ነው። በውስጡ ሦስት ነገሮች አሉበት፡፡ በ(ዕብ.9:-1-10) አንብቡ፡፡
1ኛ- ሕጉ የተፃፈበት ጽላት
2ኛ- የለመለመችው የአሮን በትር
3ኛ- እስራኤላውያን በምድረ-በዳ የበሉት መና ያለባት መሶበ-ወርቅ ናቸው፡፡ ፊተኛው ኪዳን የአዲሱ ኪዳን ጥላ ነው።
" ሕጉ ምንም ፍጹም አላደረገምና፥ ስለዚህም የምትደክም የማትጠቅምም ስለሆነች የቀደመች ትእዛዝ ተሽራለች፥ ወደ እግዚአብሔርም የምንቀርብበት የሚሻል ተስፋ ገብቶአል።"
(ወደ ዕብራውያን 7:18-19)

7ኛ,የአዲሱ ኪዳን ደግሞ :-

1ኛ, ቤተ መቅደሱ አማኙ እራሱ ነው (1ኛቆሮ 3:-16)
2ኛ, የመንፈስ ቅዱስ ማደርያ አካላችን ነው (1ኛቆሮ 6:-19)
3ኛ, ሕጉ የተጻፈበት ጽላት ልባችን(2ኛቆሮ3:-3,ዕብ 8:-10)
4ኛ, የጸጋው የመለኮት ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው(ዮሐ1
:-1 , 14 )

8ኛ, አስተማማኝ መለኮታዊ ዋስትና የተሰጠውን አዲስ ኪዳን ተቀበሉ :-

" እንዲሁ ኢየሱስ ለሚሻል ኪዳን ዋስ ሆኖአል።"
(ወደ ዕብራውያን 7:22)

9ኛ, ኢየሱስ በሞት ሊሻር የማይችል ክህነት አለው :-

ሞት ሊሽረው የሚችልው የሰው ልጆች ክህነት ኪዳናዊ ዋስትና የለውም ። "እነርሱም እንዳይኖሩ ሞት ስለ ከለከላቸው ካህናት የሆኑት ብዙ ናቸው፤
እርሱ ግን ለዘላለም የሚኖር ስለሆነ የማይለወጥ ክህነት አለው፤"(ዕብራውያን 7:-23-24)

10ኛ, ፍጹም የሆነው ዘላለማዊ ካህን የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ተሾሞአል :-

" ሕጉ ድካም ያላቸውን ሰዎች ሊቀ ካህናት አድርጎ ይሾማልና፤ ከሕግ በኋላ የመጣ የመሐላው ቃል ግን ለዘላለም ፍጹም የሆነውን ልጅ ይሾማል።"(ወደ ዕብራውያን 7:28)

11ኛ, ፊተኛው ኪዳን ለሁለተኛው አዲስ ኪዳን ስፍራውን ለቆዋል ! አርጅቶአልና ። የብሉይ የጥላ ኪዳን የአዲሱ የአካሉ ምስክር ብቻ ነው :-

" ፊተኛው ኪዳን ነቀፋ ባይኖረው፥ ለሁለተኛው ስፍራ ባልተፈለገም ነበር።"(ወደ ዕብራውያን 8:7)
" አዲስ በማለቱ ፊተኛውን አስረጅቶአል፤ አሮጌና ውራጅ የሆነውስ ሊጠፋ ቀርቦአል።"(ወደ ዕብራውያን 8:13)

12ኛ, ከአብ ጋር መታረቂያው መንገድ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው:-

" ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤"
(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:18) " አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤"
(1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:5)

13ኛ, ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢያታችንን ወስዶ የርሱን ጽድቅ ሰጥቶ አድኖናልና :-

" እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
"(2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 5:21)

14ኛ, የብሉይ ኪዳን የሲናው ታቦት ለአዲስ ኪዳን ሕያው ታቦት ምሳሌ ብቻ ነው ። በ( ዕብራውያን 9:1 - 10)
ሐዋርያ ጳውሎስ ስለ ታቦቱ ሰፊ ትንታኔ ከሰጠ በኃላ :- በ(ዕብራውያን 9:9-10)" ይህም ለአሁኑ ጊዜ ምሳሌ ነው፥"ይላል።

15ኛ,የብሉይ ኪዳን የሲናው ታቦት እና ስርዓቶቹ ስለ ምግብና ስለ መጠጥም ስለ ልዩ ልዩ መታጠብም የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና :-

" ....እንደዚህም መባና መስዋዕት ይቀርባሉ፤ እነዚህም እስከ መታደስ ዘመን ድረስ የተደረጉ፥ ስለ ምግብና ስለ መጠጥም ስለ ልዩ ልዩ መታጠብም የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና "(ዕብራውያን 9:9 )

16ኛ, እነዚህ ስርዓቶች የሚያመልከውን በህሊና ፍጹም ሊያደርጉት አይችሉም።"(ዕብራውያን 9:10 )

17, ሕሊናችንን ፈጽሞ ከሞተ ሥራ ሊያነጻ የሚችል የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ብቻ ነው :-

" የኮርማዎችና የፍየሎች ደም በረከሱትም ላይ የተረጨ የጊደር አመድ ሥጋን ለማንጻት የሚቀድሱ ከሆኑ፥ ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?" (ዕብራውያን 9:-13-14)
" ..... የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።"(1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1:7)

18ኛ,ኃጢያታችንን ወስዶ በመስቀል ላይ ጠርቆ ዳግም ላያስበው ከመንገድ አስወግዶታል :-

" በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል።"
(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 2:14)
16 views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-23 04:04:23 Channel photo updated
01:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-29 21:09:41 Channel photo updated
18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-18 19:47:11 Trust in God and God alone!

People who believe in our Lord Jesus Christ, I pray, I pray for all of you.
Don't worry about what happened in Ethiopia.

Do you know why?

We have a great father.
His name is Jesus Christ.
He knows all. "Even if the Lord gives you the bread of trouble and the water of trouble, your teacher will not hide from you, but your eyes will see your teacher, and if you turn to the right or the left, your ears will hear the words behind you: This is the way, walk in it." Isaiah 30:-20-21

He is a father who comforts us in all our sufferings and guides us.
He is great, Healer, He will free you from all your problems according to His will.
He has a great plan for your life. He stands today and sees your end. Your problems, sufferings and pains do not scare God.
He has a purpose for your life.
"Until the word came to him, the word of God tested him."
— Psalm 105:19

Everything is for good, as Paul reminded the children of God, "We know that all things work together for good to those who love God and to those who are called according to his purpose."

- Romans 8:28

God is almighty.
He changes crying with laughter, sadness with joy, emptiness with fullness...etc.
But God is faithful, who does not allow you to be tested beyond what you are capable of, and He will also make a way out for you with the test so that you can be patient."

— 1 Corinthians 10:13

Brokenness leads to blessing, death to life, suffering to glory, but thinking about our problems prepares our minds.Full of questions.
Why is God silent most of the time? Why did God do this?
We say.

Why doesn't God protect those he loves?
Why didn't God intervene?
But do you know what the word of God says?
"Trust in God with all your heart, and lean not on your own understanding."
— Proverbs 3:5

It is the Lord who has taken your guarantee.
He knows the way to guide and bless.
A second is enough to heal us.

And if we trust in Him, He...gives meaning to our meaningless selves, gives hope and hope to our hopelessness, gives strength to our weakness, and guides our aimless running.

"Your child, the Holy One of Israel, thus says the Lord: I am the Lord your God who will teach you what you need and guide you in the way you should go." - Isaiah 48:17

He will fulfill what he said to you. For Joseph, the way of slavery may not seem like the way of kingship!
Trust Him to learn more about what He has in mind!
Believe it beyond the grave!
Lazarus being buried dead and counting the days, the hope is over, the memory seems to be removed from the earth, but when Jesus comes, life will be sown, there will be a resurrection, and the veil of death will be removed.
His plan is far beyond your perspective.
Trust him to keep his word!
Trust him to be on time!
Trust Him to be enough!
Trust Him to set you free!
Trust him...........and only him!
Our God is great!
41 viewsedited  16:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-17 04:48:55 አማላጅ !

“... ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።” — ሮሜ 8፥34
“... መንፈስ ራሱ በማይነገር መቃተት ይማልድልናል፤” — ሮሜ 8፥26
“...በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን... ከእግዚአብሔር ነው፤” — 2ኛ ቆሮ 5፥18
“አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤ — 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5
“...ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።”—1ኛ ዮሐንስ 2፥1
“የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ...”— ዕብራውያን 12፥24

ይህንን የቃሉን እውነት በሚገባ ለመረዳት አማላጅ የሚለውን ቃል ትርጉም በሚገባ መረዳት ያስፈልጋል።

አማላጅ ማለት ምን ማለት ነው?
"አማላጅ"የሚለው ቃል የተገኘው "ማለደ" ከሚለው ግስ ሲሆን "ማለደ" ማለት ደግሞ ለመነ፣ወይም ፣ጸለየ ፣ ለማስታረቅ ኃላፊነቱን ወሰደ ማለት ነው። ማማለድ…ማለት መለመን ፣ ማስታረቅ ማለት ነው ።
አማላጅ ደግሞ ይህን ተግባር የሚያከናውን አካል ነው፡፡ ተግባሩ ደግሞ
ምልጃውን ፣እርቁን ማከናወን ነው፡፡

ይሁን እንጂ አማላጅ ማለት ምልጃን የሚያቀርብ ቢሆንም ምልጃ ሁሉ ግን
አንድ ዓይነት አይደለም፡፡

የክርስቶስ ምልጃ አለ /ት.ኢሳ 53፥1-12/ደግሞም የሰዎች የጸሎት ምልጃ አለ /2ቆሮ 9፥14/
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ጌታችንና መድኃኒታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሲናገር "ማለደ… ያማልዳል… ይማልዳል…" ብሎ በግልጽና በተደጋጋሚ
ይናገራል። ነገር ግን ብዙ ጊዜ ክርስቶስ "አምላክ ነውና ወደ ማን ይማልዳል?" የሚል ጥያቄ ሲነሳ ይታያል። ይህ ባጭሩ የስላሴን የእግዚአብሔር አንድነት አና ሦስትነት የአብን የወልድን የመንፈስ ቅዱስን የሥራ ድርሻ እንደሚገባ ካለመረዳት የሚነሳ ጥያቄ ነው።

በክርስቶስ የተከናወኑ ሁለት ዓይነት ምልጃዎች አሉ። እነርሱም
የክርስቶስ የጸሎት ምልጃ እና በክርስቶስ የመስቀሉ ሥራ (መስዋዕትነት)
የተፈፀመ የኃጢአት ሥርየት ምልጃ ናቸው።ኢየሱስ ክርስቶስ የጸሎት ምልጃ
ኢየሱስ ክርስቶስ ጌታ ሆኖ ሳለ፣ በሥጋ ተገልጦ የሰውን ልጅ የኃጢያት ፍርድ በመስቀል ላይ ተቀብሎ ከማዳኑም በላይ ምሳሌ እና ሞዴል ሆኖ ጻድቅ ሰው ለጌታው እንዴት መገዛት እንዳለበት በተግባር ያሳየ "የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና "ተብሎ ተጻፈ. - 1ጴጥሮስ 2፥21

አማላጅነት ማስታረቅ ነው። ለማስታረቅ የሚላክ መካከለኛ ነው። ሰው በኃጢያቱ ምክንያት ከእግዚአብሔር በመለየቱ ከሰው ወደ እግዚአብሔር ሊላክ የሚችል ጻድቅ አስታራቂ አልተገኘም ። ስለዚህ እግዚአብሔር የሰውን ልጅ በልጁ ከራሱ ጋር እንዳስታረቀ ቃሉ ይናገራል ።“ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤”
— 2ኛ ቆሮ 5፥18

ስለዚህ አብ በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ከራሱ ጋር እንዳስታረቀን የእግዚአብር ቃል ይናገራል።ኢየሱስ ክርስቶስ በሰው ልጅ እና በእግዚአብር መካከል መካከለኛ አስታራቂ ሆነ ። “አንድ እግዚአብሔር አለና፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥5

ሌላው የምልጃ ትርጉም አንድ ሰው ሌላውን ወክሎ ስለመሪዎች ፣ ስለቤተክርስቲያን፣ስለ ሰዎች ችግር መለኮታዊ ጣልቃ ገብነትን እንዲኖር በትጋት፣ በእምነት ፣ በጽናት እና በሸክም፣ ተግቶ የሚጸልይ እግዚአብሔርን የሚለመንበት ጸሎት የምልጃ በጸሎት ይባላል። የሚጸልየው ደግሞ ማላጅ ይባላል።

ብዙ ጊዜ አማላጅ ሲባል ከማን ጋር የሚል ጥያቄ ይነሳል ?
ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህን ፣ ነብይ ፣ ንጉስ ፣ መልዕክተኛ፣ አዳኝ ...ወዘተርፈ መባሉ አምላክ መሆኑኑን ሊያስቀረው አይችልም ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ሆኖ መካከለኛ ሆኖ ከአብ ጋር አስታርቆናል ። ስለዚህ “የሞተው፥ ይልቁንም ከሙታን የተነሣው፥ በእግዚአብሔር ቀኝ ያለው፥ ደግሞ ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።”
— ሮሜ 8፥34
ተባርካችኃል !
151 views01:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 05:01:23
36 views02:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-15 05:01:17 መንፈሳዊ ውጊያ !

ክፍል አንድ

ቤ/ክ ወደ ታቀደላት በእግዚአብሔር ወደታየላት በረከት እንዳትገባ የሚቃወሙ ኃይሎች አሉባት ።
ማሰናከል ማደነቃቀፍ ከእግዚአብሔር ጋር የለንን ሕብረት ፣ ግኑኝነት ማበላሸት የጠላት የሰይጣን ሥራ ነው ። ለዚህ ነው ቤተክርስቲያን ወታደራዊ አቋም እንዲኖት የተፈለገው ። ቤ/ክ ስለታየላት ብቻ የታየላትን መውረስ አትትችልም ነገር ግን ነቅታ ዲያቢሎስን በተሰጣት ስልጣን መቃወም ፣ስራውን ማፍረስ፣ በጽናት መቆም ፣ የጠላትን እቅድ ሴራ ተንኮል የሐሰት አዋጅ ማፍረስ ይኖርባታል ።

ይህም የሚከናወነው ፦
1,እውነትን በመታጠቅ !
2,ጽድቅን በመልበስ !
3,የሰላምን በመጫማት !
4,እምነትን አንግባ !
5,ደህንነትን አጥልቃ !
6,የቃሉን ሰይፍ ጨብጣ !
7, በብርቱ ጸሎት ጸንታ ስትቆም ነው ።
ይህ ደግሞ ከጩኸት ከዝላይ ከጭብጨባ ያለፈ በዕለት ተዕለት ኑሮ ውስጥ የሚገለጥ ሰብዕና መያዝ ነው።
34 views02:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 06:37:18
35 views03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 06:35:16 የመንፈሳዊ ጦር ዕቃችንን እናንሳ እንልበስ !

( ኤፌ 6፡ 10 - 18 )

"በቀረውስ በጌታና በኃይሉ ችሎት የበረታችሁ ሁኑ።የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ጦር ዕቃ ሁሉ ልበሱ።" (ኤፌሶን 6:-10-11)
የሚያበረታን የኃይሉ ችሎት እና የሰይጣንን ሽንገላ በመቃወም ጸንቶ ለመቆም የሚያስችለን ድንቅ ብቃት የሚያስታጥቀን ክብር የኃይሉ ችሎት ነው።

1ኛ, የእዉነት ቀበቶ ፦ የእዉነት ቀበቶ ጠላት ትጥቅ የሚያስፈታበትን የሐሰት ፕሮፓጋንዳውን የምንቃወምበት ጦር ዕቃ ነው ።

2ኛ, የጽድቅ ጥሩር ፦ በኢየሱስ ያገኘነው ጽድቅ እርግጠኝነት ሲሆን ይህ መንፈሳዊ ሁለንተናችንን የምናስጠብቅበት መንፈሳዊ ጦር ዕቃ ነው።

3ኛ, የመዳን ራስ ቁር ፦ የዳንበት እዉነት የምናስጠብቅበት መንፈሳዊ ጦር ዕቃ ነው ።

4ኛ, የወንጌል ጫማ ተጫምተን ፦ በወንጌል እዉነት ተሞልተን የፍቅሩን የማዳን ስራ ለሁሉ በምንደርስበት ስፍራ ሁሉ እንድናውጅ ተልከናል ።

5ኛ, የመንፈስ ሰይፉ ፦ የእግዚአብሔር ቃል ነው ። የምንኖርበት ፣የምንዋጋበት ፣ የጠላትን ክህደትና ሐሰት የምናፈርስበት ፣ የወንጌሉን እውነት የምናስጠብቅበት ሕያው የመለኮት ሰይፍ የሆነ ጦር ዕቃ ነው ።

6ኛ, የእምነት ጋሻ ፦ መሰረቱ መጽሐፍ ቅዱስ የሆነ እውነት (ክርስቶስ)፣ የምንደገፍበት ፣ የተቀበልነው የወንጌል እውነት በኛ የሚገለጥበት ፣ የክርስቶስ የመስቀል ላይ ሥራ ለኛ መሆኑን የተቀበልንበት ፣በመንፈሳዊ አለም የማይታየውን ፣ የማይዳሰሰውን ፣ በክርስቶስ የሆነልንን በረከት ሁሉ የምናይበት መንፈሳዊ ዓይን እና የምቀበልበት መንፈሳዊ እጅ ነው

7ኛ, በመንፈስ መፀለይ፦ከመለኮቱ ኃይል ከምንጩ ጋር የምንናኝበት መንገድ መንፈሳዊ ጦር ዕቃ ነው።

ይህንን መንፈሳዊ ጦር ዕቃ በመልበስ በዕናት በመቆም የክርስቶስ አምባሳደር ሆነን ብዙዎችን ከሞት ወደ ሕይወት ፣ ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብረሃን እንድናፈልስ ተጠርተናል።ይህ በክርስቶስ ድል መንሳት ተገልጦ ምርኮን መበዝበዝ ነው ። ተባርካችኃል !
35 views03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ