Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-09-07 05:39:51 #በክርስቶስ_ኢየሱስ_በማመናችሁ_ብቻ_እንኳን_ደስ_አላችሁ_!!

“ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”
— ሮሜ 11፥36

በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ያመናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ! እንኳንም የጌታ ሆናችሁ ! ይህ ሁሉ ሆኖላችኃልና !

1.በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ የእግዚአብሄር ልጆች ናችሁ ።
“ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤”
— ዮሐንስ 1፥12

2. በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ የእግዚአብሄር ፅድቅ ናችሁ።
“እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥21

3. እናንተ የክርስቶስ ኢየሱስ ምስክር ናችሁ ።
“ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወረደ ጊዜ ኃይልን ትቀበላላችሁ፥ በኢየሩሳሌምም በይሁዳም ሁሉ በሰማርያም እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ አለ።”
— ሐዋርያት 1፥8

4. እናንተ የኢየሱስ የክርስቶስ ልብ አላችሁ።
“እንዲያስተምረው የጌታን ልብ ማን አውቆት ነው? እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 2፥16

5. እናንተ የምድርን ጣዕም የምትቀይሩ ጨው ናችሁ።
“እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፤ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል? ወደ ውጭ ተጥሎ በሰው ከመረገጥ በቀር ወደ ፊት ለምንም አይጠቅምም።”
— ማቴዎስ 5፥13

6. እናንተ በክርስቶስ አዲስ ፍጥረት ናችሁ።
“ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥17

7.ከድቅድቅ ጭለማ ወደ ሚደነቅ ብረሃን ተጠርታችኃል ።
“እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥9

8.የንጉሱ ካህናት ሆናችኃል ።
"የተመረጣችሁ ትውልድ የንጉስ ካህን ቅዱስ ህዝብ ለርስቱ የተለያችሁ ወገን ምህረትን ያገኛችሁ ናችሁ።"
- 1ጴጥ 2፡9

9. እናንተ የእግዚአብሄር መንፈስ ማደሪያ ቤተ መቅደሱ ናችሁ።
“ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ።”
— 1ኛቆሮ3፡16-17

10. የእናንተ ሀገር በሰማይ ነው።
“እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤”
— ፊልጵስዩስ 3፥20

11. በአለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ይበልጣል።
“ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።”— 1ኛ ዮሐንስ 4፥4

12. እናንተ የክርስቶስ አካል ናችሁ።
“እናንተም የክርስቶስ አካል ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 12፥27

13. ወደ አብ መግባትን አግኝችላችኃል።
“በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና።”
— ኤፌሶን 2፥18

14. በሰማያዊ ስፍራ ተቀምጣችኃል።
“... በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።”
— ኤፌሶን 2፥6-7

15.ለፅድቅ ከክርስቶስ ጋር በህይወት ተነስታችኃል።
"ለኃጢያት ሞታችሁ ለፅድቅ ከክርስቶስ ጋር በህይወት ተነስታችኃል።"
-ሮሜ6፡8 -ቄላ3፡3

16. እናንተ የእግዚአብሄር ምርጥ ናችሁ።
“ዓለም ሳይፈጠር፥ በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን።”
— ኤፌሶን 1፥4

17.ብፁዓን ናችሁ።
“ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ።”
— ማቴዎስ 5፥11

18.የዓለም ብርሃን ናችሁ።
“እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም።”
— ማቴዎስ 5፥14

19.የኢየሱስ ክርስቶስ የማዳኑ ምስክሮች ናችሁ።
“እናንተም ለዚህ ምስክሮች ናችሁ።”
— ሉቃስ 24፥48 -ማቴ 28:-18-20

20. የጌታ ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ ።
“ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤”
— ዮሐንስ 8፥31

21.በክርስቶስ ንጹሐን ናችሁ።
“እናንተ ስለ ነገርኋችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ፤”
— ዮሐንስ 15፥3 — ዮሐንስ 13፥10

22.የኪዳን ልጆች ናችሁ።
“እናንተ የነቢያት ልጆችና እግዚአብሔር ለአብርሃም፦ በዘርህ የምድር ወገኖች ሁሉ ይባረካሉ ብሎ፥ ከአባቶቻችን ጋር ያደረገው የኪዳን ልጆች ናችሁ።”
— ሐዋርያት 3፥25

23.የኢየሱስ ክርስቶስ ልትሆኑ የተጠራችሁ እናንተ ደግሞ ናችሁ።
“በእነርሱም መካከል የኢየሱስ ክርስቶስ ልትሆኑ የተጠራችሁ እናንተ ደግሞ ናችሁ።”
— ሮሜ 1፥6

24.ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ።
“... ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ።”
— ሮሜ 6፥16

25.የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ።
“የእግዚአብሔር እርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንፃ ናችሁ፤ ከእርሱ ጋር አብረን የምንሠራ ነንና።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥9

26.በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና።
“በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤”
— ገላትያ 3፥26

27.በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።
“አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።”
— ገላትያ 3፥28

28.የተስፋውም ቃል ወራሾች ሆናችኃል።
“እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።”
— ገላትያ 3፥29

29.የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ።
“እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም።”
— ኤፌሶን 2፥19

30.ከጭለማው አገዛዝ አምልጣችኃል ።
“ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ አሁን ግን በጌታ ብርሃን ናችሁ፤”
— ኤፌሶን 5፥8

31.እግዚአብሔር ምስክሮች ሆናችኃል።
“.....እናንተና እግዚአብሔር ምስክሮች ናችሁ፤”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 2፥10

32. የብርሃን ልጆች ሆናችኃል።
“ሁላችሁ የብርሃን ልጆች የቀንም ልጆች ናችሁና። እኛ ከሌሊት ወይም ከጨለማ አይደለንም፤”
— 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥5

33.አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ሆናችኃል።
“እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥10

34. አሸናፊዎች ተደርጋችኃል።
“ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥4

35. በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።
“... ነገር ግን በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥11
1 viewedited  02:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 20:01:32 የወጣቶች አያያዝ እና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን

ክፍል ሦስት

መጽሐፍ ቅዱስ ወጣቶችን ጠቦቶች ጎበዛዝዝት ብሎ ይጠራቸዋል ቅዱሳት መጻሕፍት ወጣትነት ልዩ ጥበቃ እና እንክብካቤ እንደሚያስፈልገው በስፋት ያስተምራሉ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን የሰጠው ትልቅ አደራ ወጣቶችን እንድትጠብቅ ነው (ዮሐ .21፥152-18)።

ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የወጣትነት ጊዜውን በጥበብ እና በማስተዋል በእግዚአብሔር እና በሰው ፊት እንዳደገ ጽፎልናል።(ሉቃ.2፥52)። የወጣቶች መገኛ ቤተሰብ እና ቤተክርስቲያን መሆኑን ከጌታችን የምንማረው ትልቅ ትምህርት ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን ወጣትነት የበለጠ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት የምናጠብቅበት ዘመን መሆኑን በግልጽ ይናገራል። “ የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስበ”። (መክ. 12፥1-3)

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወጣቶች ክርስቲያኖች በጥበብ እና በማስተዋል እንዲሁም በጥንቃቄ መመላለስ እንዳለባቸው ይመክራል። “እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞቸ አትሁኑ። መንፈስ ይሙላባች እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና።” (ኤፌ.5፥ 15-119)

ቅዱስ ጳውሎስ በተለይ ወጣቶች ጓዶኞቻቸውን መምረጥ እንዳለባቸው እና ከክፉ ባልንጀራ መራቅ እንዳለባቸው ሲመክር እንዲህ ብሏል “አትሳቱ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥራ እግዚአብሔርን የማያወቁ አሉና አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።” (1ኛቆ.15፥33-34)

የመፍትሔ ሀሳቦች

ወላጆች ኃላፊነታችንን እና ግዴታችንን መወጣት ወጣቶች ደካማ ሞራል ካላቸው ጓደኞቻቸው እንዲርቁ፣ መርዳት ሞራል የጎደላቸውን መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ ድህረ ገጾችን እና የቴሌቪዥን ትዕይንቶችን ወጣቶች እንዳይመለከቱ ማገዝ ወጣቶች ሥልጠና እና የምክር አገልግሎት የሚገኙባቸውን ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ወጣቶች በሃይማኖት ተኮትኩተው በመልካም ሥነ ምግባር ታንጸው፣ በማንነታቸው የሚኮሩ ፣ ሀገር ወዳድ ፣ ዜጋ እንዲሆኑ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ይኖርብናል። በተለይ ቤተክርስቲያን ወጣቶች የመጠበቅ አደራዋን መወጣት አለባት።በማኀበራዊ እና ሃይማታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መሥራት(ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ሬድዮ፣ቲቪ)
.........ይቀጥላል !
96 views17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 19:59:09 የወጣቶች አያያዝ እና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን

ክፍል ሦስት

መጽሐፍ ቅዱስ ወጣቶችን ጠቦቶች ጎበዛዝዝት ብሎ ይጠራቸዋል ቅዱሳት መጻሕፍት ወጣትነት ልዩ ጥበቃ እና እንክብካቤ እንደሚያስፈልገው በስፋት ያስተምራሉ። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቤተክርስቲያን የሰጠው ትልቅ አደራ ወጣቶችን እንድትጠብቅ ነው (ዮሐ .21፥152-18)።

ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የወጣትነት ጊዜውን በጥበብ እና በማስተዋል በእግዚአብሔር እና በሰው ፊት እንዳደገ ጽፎልናል።(ሉቃ.2፥52)። የወጣቶች መገኛ ቤተሰብ እና ቤተክርስቲያን መሆኑን ከጌታችን የምንማረው ትልቅ ትምህርት ነው። ጠቢቡ ሰሎሞን ወጣትነት የበለጠ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን ግንኙነት የምናጠብቅበት ዘመን መሆኑን በግልጽ ይናገራል። “ የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስበ”። (መክ. 12፥1-3)

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወጣቶች ክርስቲያኖች በጥበብ እና በማስተዋል እንዲሁም በጥንቃቄ መመላለስ እንዳለባቸው ይመክራል። “እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። ስለዚህ የጌታ ፈቃድ ምን እንደሆነ አስተውሉ እንጂ ሞኞቸ አትሁኑ። መንፈስ ይሙላባች እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና።” (ኤፌ.5፥ 15-119)

ቅዱስ ጳውሎስ በተለይ ወጣቶች ጓዶኞቻቸውን መምረጥ እንዳለባቸው እና ከክፉ ባልንጀራ መራቅ እንዳለባቸው ሲመክር እንዲህ ብሏል “አትሳቱ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። በጽድቅ ንቁ ኃጢአትንም አትሥራ እግዚአብሔርን የማያወቁ አሉና አሳፍራችሁ ዘንድ ይህን እላለሁ።” (1ኛቆ.15፥33-34)

የመፍትሔ ሀሳቦች

ወላጆች ኃላፊነታችንን እና ግዴታችንን መወጣት ወጣቶች ደካማ ሞራል ካላቸው ጓደኞቻቸው እንዲርቁ፣ መርዳት ሞራል የጎደላቸውን መጻሕፍት፣ መጽሔቶች፣ ድህረ ገጾችን እና የቴሌቪዥን ትዕይንቶችን ወጣቶች እንዳይመለከቱ ማገዝ ወጣቶች ሥልጠና እና የምክር አገልግሎት የሚገኙባቸውን ምቹ ሁኔታዎች መፍጠር ወጣቶች በሃይማኖት ተኮትኩተው በመልካም ሥነ ምግባር ታንጸው፣ በማንነታቸው የሚኮሩ ፣ ሀገር ወዳድ ፣ ዜጋ እንዲሆኑ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ይኖርብናል። በተለይ ቤተክርስቲያን ወጣቶች የመጠበቅ አደራዋን መወጣት አለባት።በማኀበራዊ እና ሃይማታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሚዲያዎች ላይ በስፋት መሥራት(ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ሬድዮ፣ቲቪ)
.........ይቀጥላል !
84 views16:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 19:58:55 የወጣቶች አያያዝ እና አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን

ክፍል ሁለት

በሰው ልጆ ታሪክ ውስጥ ዓለማችን የስልጣኔ ጫፍ ላይ የደረሰችበት እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማዕበል የተጥለቀለቀችበት ዘመን ይህ እኛ የምንኖርበት ሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው። ሃያ አንደኛው መቶ ክፍለ ዘመን የመረጃ፣ የቴክኖሎጂ፣ ዓለም አቀፋዊነት /Globalization/ ዘመን እየተባለ ይጠራል። ሥልጣኔው እና ቴክኖሎጂው የሰው ልጆችን አኗኗር ቀላል ከማድረጉ ባሻገር የተለያዩ እድሎች እና አማራጮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አድርጓል። ከዚህ የተነሳ የሰው ልጆች የአኗኗር ዘይቤ እጅግ በፍጥነት እየተለወጠ ሊሔድ ችሏል ።

በዚህ ዘመን የሚኖሩ ወጣቶች የስልጣኔው እና የቴክኖሎጂው ተጠቃሚ መሆናቸው እንደ መልካም እድል ቢቆጠርም ለውጡ ያመጣቸው ችግሮች እና ፈተናዎች ደግሞ የወጣቶችን ሕይወት እጅግ ከባድ አድርጎታል።

ወጣቶች ብዙ ግራ የሚያጋቧቸው፣ የሚያስጨንቋቸው እና ጫና የሚፈጥሩባቸው ከዘመኑ ጋር ተያይዘው የመጡ ችግሮች አሉ። ይህም በትምህርት ቤት፣ በወጣቶች መካከል ያለው ውድድር እና ፉክክር (በውጤት፣ በውበት፣በልብስ፣በሥራ)ወ.ዘ.ተ.ር.ፈ በዚህ ምክንያት አንዳንድ ወጣቶች የወደፊት ሕይወታቸው ጨለማ እና አስቸጋሪ እንደሆነ አስበው ከወዲሁ ተስፋ በመቁረጥ ይጨነቃሉ፣የመኖር ትርጉሙ ጠፍቷቸው በድብርት/ድብት/ ይሰቃያሉ።

በዓለማችን እየታየ ካለው ፈጣን ለውጥ ጋር በተያያዘ አዳዲስ ልማዶች፣ ለሌላ ባዕድ ሃይማኖት እና ባህል ተጋላጭ መሆን፣ የአኗኗር ዘይቤ መቀየረ ወጣቶች ምን እንደሚፈልጉ፣ ምን እንዳሚመርጡ እና ምን እንደሚሆኑ ከባድ አድርጎታል። ይህ ክስተት በብዙ ወጣቶች ዘንድ ግራ መጋባትን፣ በሕይወት መሰላቸትን እና ከፍተኛ ቀውስ አስከትሏል። ስለዚህ ወጣቶች እግዚአብሔርን እንዲያስቀድሙ ቃሉን በመሞላት ወደፊት በኑሮአቸው ስኬታማ፣ ደስተኛ እና ውጤታማ እንዲሆኑ ቤ/ክ የድርሻዋን ልትወጣ ይገባል ፣ ደግሞም ተሰጥዖአቸውን ለይተው እንዲያውቁ ልናግዛቸው፣ ጊዜያዊ ደስታ እና እርካታ ሳያታልላቸው ዘላቂ ዓላማ እና ራእይ ይዘው እንዲጓዙ ከሁሉም የሚጠበቅ ግዴታ ነው። ወጣቶች ትክክለኛ ምርጫ እና ውሳኔ ለመወሰን ራሳቸውን እንዲያዘጋጁ የቤተሰብ እና በወጣቶች ላይ የሚሰሩ የሰንበት ት/ቤት በየ አጥቢያ ቤተክርስቲያን እና ሌሎችም ተቋማት እገዛ ያስፈልጋቸዋል።

ለማንኛውም ትውልዱን ለሚወድ እና ለእነርሱ የሚጨነቅ ሁሉ እንቅልፍ የማያስተኛ በትውልድ ላይ የተጋረጠ ከባድ ተግዳሮት ስለሆነ ቤተሰብ ፣ ቤተ ክርስቲያን ፣ ለአገልጋዮች፣ መሪዎች ለሁላችንም ትልቅ የቤት ሥራ ነው።

ዓላማው:-
1ኛ.በቤተ ክርስቲያን ክፍተት ከሚታይባቸው የመንፈሳዊ ዘርፍ አገልግሎት አንደኛው የወጣቶች አገልግሎት ነው።

2ኛ.ወጣቶች ካለባቸው ተግዳሮቶች አንጻር የቤተክርስቲያን ኃላፊነት ምን መሆን እንዳለበት ለማስረዳት።

3. እያንዳንዱ ወጣት ለወጣቱ ያለው ኃላፊነት እንዲረዳ ።

4. ቤተክርስቲያን እና ቤተሰብ ካለባቸው ኃላፊነት አንጻር ለወጣቱ ጥሪ ያለው ሸክም ያለው ጥሪው ሌት ተቀን የሚያሮጠው ለወጣቶች ወጣት ፓስተር የሚያስፈልግ መሆኑን ለማስረዳት።

......ይቀጥላል !
75 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-04 19:58:10 የወጣቶች አያያዝ እና አገልግሎት በተመለከተ በቤተ ክርስቲያን ኃላፊት ላይ እንወያይ ።

ክፍል አንድ

ወጣቱ ያለበት የእድሜ ክልል በራሱ ተግሮት ነው። በመሆኑም በብዙ መልኩ ለተለያዩ አደጋዎች ያለው ተጋላጭነት የሰፋ ነው ፡፡ በጎና ክፉን ሳይለይ ሁሉንም ነገር ፊት ለፊት የሚጋፈጥ ስለሆነ በብዙ ነገር ተፈላጊ ነው፡፡በዓለም፣ በሰይጣን ፣በፓለቲካ፣በሐሰት አስተማሪዎችና በቴክኖሎጂ ለሚተላለፉ ክፉ አሰራሮች በልዩ ልዩ ዓለማዊ ፍልስፍናዎች ወጥመድ ተዘርግቶበታል ፡፡

በመሆኑም ዘወትር አዳዲስ ነገር ናፋቂው ወጣት በየጊዜው የእውነት መሰረት በሌላቸው አዳዲስ ፍልስፍናዎች የሚጠመድ በመሆኑ ከፍተኛ ክትትል እና እገዛ ያስፈልገዋል፡፡ ስለዚህም ለወጣቱ መያዝ ትልቅ መፍተሔ የሚሆነው እና ስር ነቀል የሆነ መንፈሳዊ ለውጥ የሚመጣው እንደተለመደው ለወጣቱ የተለያዩ የቤ/ክ አገልጋዮች እየለዋወጡ መስጠት ሳይሆን
1ኛ,ወጣቱን እራሱን በማነሳሳት እና ወጣት ለወጣት የወንጌልና የጠፋዉን የመፈለግ አገልግሎት እንዲያከናውን በልዩ ሁኔታ በማደራጀት ወጣቱ ራሱ ለወጣቱ ታላቅ ኃላፊነት እንዳለበት ማስገንዘብ ነው ፡፡

2ኛ,ብዙዎች ሳያውቁ ወደ ጥፋት ሊገቡ በመንደርደር ላይ ስላሉ ይህንን ተተኪ ትውልድ ለማዳን ሁላችን ትኩረት ልናደርግ ይገባል ፡፡ ይህም ትኩረት አስፈላጊ የሚሆነው ከተሰጠን ተልዕኮ አንጻር እና በመጪው ዘመን ቤተ ክርስቲያን ተረካቢ ትውልድ እንዲኖራት እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ በመሆኑ መስራትም ያለበት አሁን በመሆኑ ነው ፡፡

ስለዚህም መፍትሔው ፡-

1ኛ. ጠንካራ ወጣት ለወጣት የወንጌልና የጉብኝት አገልግሎት እንዲኖር ማድረግ !

2ኛ. አገልጋዮች ከወጣት ወላጆች ጋር የጠበቀ ግንኙነት በማረግ ቤተሰብን አጥብቆ ተከታታሎ በመያዝና በመመገብ ልጆቻቸውን መያዝ !

3ኛ. ወጣቱን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊሰቡና ከቤ/ክ ጋር እንደዲቆራኝ የሚያርጉ ትምህርቶችን ፣ስፖርታዊ ጨዋታዎች፣ የካምፋየር ምሽቶችን፣ልዩ ልዩ መንፈሳዊ ጭውውቶችን፣ የዝማሬ ኮንሰርቶችን በማዘጋጀት ፣የጥያቄና መልስ ጊዜ ማዘጋጀት ወዘተ…..

4ኛ. የመኃልየ መኃልይ ጥናትና የቅድስና ሕይወት ት/ት ማዘጋጀት !

5ኛ. የመንፈሳዊ እድገት ትርጉምና ምንነትን ማስተማር !

6ኛ. በተቀደሰ ክርስቲያናዊ ጋብቻ የመጣመር አስፈላጊነትን ማስተማር !

7ኛ. በክርስቲያን ቤተሰቦች ውስጥ ዕድሜያቸው ለደህንነት ትምህርት የደረሱትን በአንድነት ሰብስቦ በማስተማር እና በመከታተል !

.....ይቀጥላል !
144 views16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 08:03:14 ራዕይ

ክፍል ሦስት

“ንጉሥ አግሪጳ ሆይ፥ ስለዚህ ከሰማይ የታየኝን ራእይ እምቢ አላልሁም።”
— ሐዋርያት 26፥19
ራዕይ ምንጩ ሰማይ ነው (የእግዚአብሔር ዙፋን) ራዕይ ሲገለጥ የምታስተውልበት ሰማያዊ ጥበብና ማስተዋል አብሮ ነው የሚሰጥህ ። ለዚህ ነው ዳንኤል “አስተማረኝም፥ ተናገረኝም እንዲህም አለ፦ ዳንኤል ሆይ፥ ጥበብንና ማስተዋልን እሰጥህ ዘንድ አሁን መጥቻለሁ።”
— ዳንኤል 9፥22

ራዕይ ምንጩ ሰማይ ነው ጥበብና ማስተዋልም እንዲሁ ።
ራዕይ እግዚአብሔር የሚያየውን ማየት ነው ። ራዕይ ወይም መገለጥ የተባለው በውጫዊው የስጋ አይን የማይታ ስላልሆነ ነው። ራዕይም ሆነ መገለጥ የሚለሉት ቃላቶች ይህንን ይይገልጣሉ ። ራዕይ ውስጣዊ የልቦና አይኖች ሲከፈቱ ሲበሩ የምታየው ነው ። ይህም ከስብዓዊ እና ከሥጋዊ ልምምድ አልፎ የሚገኝ የእግዚአብሔር ጥልቅ ሚስጥር ነው።

ራዕይ ሁሉ በቃሉ የሚመዘን ተፈትኖም የሚያልፍ ከቃሉ የተሰጠ ተስፋ መፈጸሚያ እንጂ በቅዱስ ቃሉ ያልተካተተ አዲስ ግልጠት አይደለም። ለዚህ ነው ቅዱስ ቃሉ የሁሉም ነገር መሠረት እና መለኪያ ነው የምንለው ። በቃሉ ተፈትኖ የማያልፍ ራዕይ ምንጩ ሥጋ እና ደም እንጂ መንፈስ ቅዱስ አይደለም።

ራዕይ የአንድ ቀን ድራማ እና የአንድ ቀን ጭፈራና ዝላይ ጉዳይ ሳይሆን ሕይወትን፣ አገርን የሚቀይር፣ ዘመን ተሻጋሪ ፣ በመከራ የማይገደብ ፣ በሞት የማይያዝ ከትውልደ ትውልድ የሚሸጋገር በመገፋት የማይከስም የሚፈጸም የእግዚአብሔር የልቡ አጀንዳ ነው።

ራዕይ በአንድ ግለሰብ በኩል ማለፍ ቢችልም የሚሰጠው ለአንድ ግለሰብ ዝና፣ ጥቅም፣ ክብር ወይም ትምክህት አይደለም ። ራዕይ የሚሰጠው ለእግዚአብሔር ክብር ለሰው ልጆች ሁሉ ጥቅም ለውጥ እና እድገት ነው። ዓላማ እና ግቡ በትውልደ ትውልዶች ላይ ያተኩራል። ከእግዚአብሔር የሚሰጥ ራዕይ የእግዚአብሔር የራሱ የብቻው ነው ።

እግዚአብሔር በመረጣቸው በጠራቸው በልጆቹ በኩል ራዩን ያስተላልፋል ። ለራዕይ መገለጥ የተጠራ ሰጪውን ማክበር ማሰተዋልና ጥበብን ለምኖ ራዕዩን በጥልቀት በመረዳት ማደግ ፣ለተገለጠው ራዕይ ታዛዥ መሆን ፣ ለራዕዩ ተግባራዊነት ታማኝ በመሆን መትጋት ፣ ራዕዩን በሥራ ላይ ማዋል ፣ ራዕዩን ለሌሎች በማካፈል ተጨባጭ ማድረግ ይኖርበታል።

ራዕይ ተጨባጭ ሆኖ ይገለጥ ዘንድ የሕይወት ፣ የገንዘብ ፣ የጊዜ የጉልበት ፣ የዕቀት ወዘተርፈ መሰዋዕትነት ይጠይቃል ። ምሁራን የምትሞትበት ራዕይ ከሌለህ የምትኖርበት ዓላማ የለህም ይሉ የለ ። ራዕይ እስከሞት የምትታመንለት እንጂ ሁኔታዎች እስኪስተካከሉ ይዘህ ሲመችህ የምትጥለው አይደለም ። ተባርካችኃል !
.............ይቀጥላል !
94 views05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-01 06:43:35 ራዕይ
ክፍል ሁለት

እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ለከበረ ለዓላማ ነው።
“.....ወንዶች ልጆቼን ከሩቅ ሴቶች ልጆቼንም ከምድር ዳርቻ፥ በስሜ የተጠራውን ለክብሬም የፈጠርሁትን፥ የሠራሁትንና ያደረግሁትን ሁሉ አምጣ እለዋለሁ።”
— ኢሳይያስ 43፥6-7
የተፈጠርነውና የምንኖረው ለክብሩ መሆን ዓለበት ። ሕይወታችን፣መኖራችን ፣ ምልልሳችን ፣ አገልግሎታችን ፣ ሥራችን የእግዚአብሔርን ክብር የማይገልጥ ከሆነ ከተፈጠርበት ዓላማ ውጭ ነን ።

ራዕይ ከሥጋና ከደም ያልሆነ እና የሰማይ አባት የሚገልጠው ከምድር ያለፈ እይታ ነው። አይኖችህ ሲከፈቱ የእግዚአብሔር ቃል ፍቺ ሲያበራልህ ሥድርን ሳይሆን ከምድር ያለፈውን ታያለህ ። “የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።”
— ኤፌሶን 1፥17
ሐዋርያው ጳውሎስ ምጥ ለቅዱሳን የጸሎት ምጥ የቅዱሳን የልቦና አይኖች መከፈት የሆነው ለዚህ ነው ።

መንፈሳዊ ግልጠቶች ምንጫቸው ሰማይ ነው። ብዙ ጊዜ መለኮዊ ግልጠት የሚጨበጥ ተግባራዊ የሚሆን አይመሥልም ። ለባርነት በተሸጠው በዮሴፍ ወሰጥ ንግስናን ማየት ይከብዳል። ከአንድ ደሃ ቤተሰብ በከብቶች በረት በተወለደ ህጻን ዓምን ሁሉ ይዳናል ብሎ የዓለምን ደህንነት በውስጡ ማየት ይከብዳል።የሚደንቀው ግን እግዚአብሔር ክብሩን የሚገልጠው በዚሁ መንገድ ነው ።

መለኮታዊ ራዕይ እግዚአብሔርን እንጂ አንተን ላያስከብር ይችላል ። ብዙ ጊዜ መለኮታዊ ራዕይ በመከራ የታጀበ ነው። የዮሴፍን መከራ ፣የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ የደም ልብ ፣የመሥቀል ላይ ጣር ፣ ውርደት ...ማየት በቂ ነው ። ዮሴፍ ንግስና ተነግሮት ተሸጠ ባርያ ሆነ፣ በወንድሞቹ ላይ እንደሚነግስ ቢነገረውም እነርሱ ለባርነት ሸጡት ፣ ራዕይ ሁል ጊዜ በተቀባይነት የታጀበ ላይሆን ይችላል ። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ገዛ ወገኖቹ መጣ አልተቀበሉትም።

አንተ ያየኸውን ራዕይ ሰው ላያይልህ ይችላል። በራዕይሆ ቅናት ሊነሳብህ ይችላል “ዮሴፍም ሕልምን አለመ፥ ለወንድሞቹም ነገራቸው፤ እነርሱም እንደ ገና በብዙ ጠሉት።.........ለአባቱና ለወንድሞቹም ነገራቸው፤ አባቱም ገሠጸው፥ እንዲህም አለው፦ ይህ ያለምኸው ሕልም ምንድር ነው? በውኑ እኔና እናትህ ወንድሞችህም መጥተን በምድር ላይ እንሰግድልህ ይሆን? ወንድሞቹም ቀኑበት አባቱ ግን ነገሩን ይጠብቀው ነበር።"
— ዘፍጥረት 37፥5,10-11

ራዕይን የሚለውን ቃል ትርጉሙ ለየቅል ቢሆንም መንፈሳዊ የሆኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆኑ መንፈሳዊ ያልሆኑትም ሰዎች ይጠቀሙበታል ። በመሆኑም ራዕይን የምንተረጉምበት ይዘት ወሳኝ ነው። ለራዕይ ያለን ዕይታ የዓለማውያን እይታ ከሆነ የራዕይ ምንነት አልገባንም ማለት ነው። ራዕይ እግዚአብሔር ዓላማውን ፈቃዱን በነርሱ ሊፈጽም በጠራቸው ሰዎች የሚገልጠው መለኮታዊ መርህ ነው። ይህም ለእግዚአብሔር በመኖራችን በእኛ ሊፈጽመው የጀመረው ነገር ራዕይ ይባላል። እይታችንን ከሌሎች ልዩ የሚያደርገው እግዚአብሔርን የሚያስከብር የሰውን ልጅ የአኗኗር ዘይቤ የሚቀይር እና ለሰው ልጆች ሁሉ በረከት እና ጥቅም የሚሆን ለመኖራችን አስደናቂ ትርጉም የሚሰጥ እውነት ነው ።

እንደ እግዚአብሔር ቃል ራዕይ ማለት ምን ማለት ነው ? ራዕይ ማለት እግዚአብሔር የሚያየውን ማየት ማለት ነው፣ ራዕይ ማለት ከእግዚአብሔር የሚሰጥ መገለጥ ነው፣ራዕይ ከዕለት ተዕለት ልምምድ ከተፈጥሮ ሕግና አሰራር ውጭ የሆነ እግዚአብሔር የሚገልጠው አደራረግ ነው ።

እግዚአብሔር ከሰው ከተፈጥሮ ልምምድ ውጭ ራሱንም ሆነ ክብሩን ይገልጣል። ራዕይ እግዚአብሔር የገለጠውን ዓላማ እና እቅድ በተግባር የሚተረጉምበት ስልቱ ነው። ራዕይ እግዚአብሔር ለልጆቹ የሚሰጠው መለኮታዊ ምሪት ነው።ራዕይ እግዚአብሔር ሕዝቡን ስርዓት የሚያስይዝበት ድንጋጌው ነው። ያለ ራዕይ ሕዝብ መረን ይሆናል ማለትም ስድ፣ ልቅ ፣ዓላማ የሌለው፣ ግብ የሌለው፣ መርህ አልባ ፣ ስሜታዊ ግልቢያ ፣ ንፋስን እንደመጎስም ባዶ ሩጫ ይሆንበታል ። ሰው ስሜቱ ፣ ልቅነቱ ፣መርህ ፣ አልባነቱ ወደ ራዕዩ አያደርሰውም ። ተረጋግቶ በማስተዋል በእርጋታ ወደ ራዕዩ የሚደርስበትን መለኮታዊ መርህ ማግኘት አለበት ይህም የተቀደሰው ቃል ዕውቀት በመንፈስ ቅዱስ አብርሆት ሲገለጥ ማለት ነው።

ራዕይ በሰማይ የሚከናወን መለኮታዊ ዕቅድ በምድር ተገልጦ የሚፈጸምበት መንገድ ነው ።ስለዚህ ራዕይ መለኮታዊ መርህ ፣እቅድ ፣ ዓላማ የሚፈጸምበት መርህ ነው።ራዕይ ተጨባጭ ተግባራዊ በመሆኑ የሚፈጸምበትን እውቀትና ጥበብ መያዝ ያስፈልጋል። ተባርካችኃል!

..............ይቀጥላል !
22 views03:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 20:46:27 ራዕይ

“ራእይ ባይኖር ሕዝብ መረን ይሆናል፤ ሕግን የሚጠብቅ ግን የተመሰገነ ነው።”
— ምሳሌ 29፥18
ራዕይ ምንድነው ? የሚለውን ጥያቄ በሚገባ ለመመለስ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ራዕይ የሚናገረውን መሰረታዊ እውነት ማወቅ የተገባ ነው። ራዕይ ለሕዝብ ጥቅም ከእግዚአብሔር የሚሰጥ መለኮታዊ መመሪያ ነው ። እግዚአብሔር ራዕይን የሚሰጠው እርሱ በመረጠው በጠራውና በለየው ሰው በኩል ነው ።

ራዕይ ሕዝብን መረን ከመሆን ይታደጋል ራዕይ ያለው ሕዝብ በግምት የሚሔድበትን የሚደርስበትን ሳያውቅ የገዛ ስሜቱ እና ፈቃዱ ወደ ነዳው የሚነዳ አይደለም። ይልቁንም ራዕይ ያለው ሕዝብ መነሻ እና መድረሻ ዓላማ እና ግብ ያለው ለፍሬያማነት ለስኬት እና ለመከናወን የሚጓዝ የሚተጋ እና ታታሪ የሆነ መርህ ያለው ሕዝብ ነው።

ብዙ ጊዜ ሰዎች ከእግዚአብሔር እውነት የሚጎሉበት ምከንያት ሕዝብ ሲኖር መሪ መኖሩን ፣ መሪ ሲኖር መመሪያ መኖሩን ፣ መመሪያ ካለ ደግሞ ለመመሪያ ተገዢ በመሆን መታዘዝ እንደሚጠበቅባቸው ይዘነጋሉ ። ከዚህ የተነስ በጋራ ሊኖራቸው ወይም ሊደርሱበት ከተሰጣቸው ወጤት ይጎላሉ። ከጋራ ተጠቃሚነት ፣ እድገት ፣ ዓላማ እና ግብ ወደ ኃላ በመቅረት መረንነት ለሚያመጣው ውድቀት መፈራረስ አደጋ ይጋለጣሉ ።

ራዕይ ብዙዎችን ከብዙ አመለካከት ወደ አንድ አመለካከት እና እይታ የሚያመጣ አያያዥ ኃይል ከመሆኑም በላይ በዓላማ ግብና ስኬት ፣ ወደ ውጤት እና ወደ ፍሬያማት በጋራ እንድንተም የሚያደርግ የከበረ እውነት ነው። መለኮታዊ ራዕይ ሲኖር እግዚአብሔር ሕዝብ ፣ መሪ እና ተመሪ ፣ በአንድ አቅጣጫ ፣ በአንድ መንገድ ፣ ልብ ለልብ በመያያዝ ፣ በአንድ መንፈስ ፣ በፍቅር ፣ በመሰጠት ፣ ባለመገፋፋት አብሮ መራመድ በአንድ ዓላማ ለአንድ ግብ መትመምን የሚፈጥር ነው።

ብዙዎች ሰለ ራዕይ ትርጓሜ ያላቸው አመለካከት የተለያየ ቢሆንም ሰው ሁሉ በራዕ መመራት እንዳለበት ግን በሁሉም ዘንድ ይታመናል ። በራዕይ አንጻር ብዙ አመለካከቶች አሉ ከነዚህም ጥቂቶቹ ።ራዕይ አሸናፊ ሐሳብ ነው የሚሉ አሉ ፣ ራዕይ የብዙ ሐሳብ ተዋጾ ነው የሚሉ አሉ፣ ራዕይ እቅድ ነው የሚሉ አሉ ፣ራዕይ የምንመኘው መልካም ሐሳብ ነው የሚሉ አሉ ፣ ካለተጨበጠ ነገር የሚነሳ መልካም አመላካከት አና ዓላማ ነው የሚሉም አሉ ፣ እንዲሁም ራዕይ እግዚአብሔር ለክብሩ በሰዎች ልብ ውስጥ የሚያስቀምጠው መነሻ እና ግብ ያለው መሻት እና ፍላጎት ነው የሚሉም አሉ ። (ፊል 2:-13) ተባርካችኃል !

...........ይቀጥላል !
21 viewsedited  17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 11:59:17 ኑ ወደ ብቸኛው አዳኝ !
የእግዚአብሔር የተዘጋጀው ብቸኛው አዳኝ ማነው ?

“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
— ሐዋርያት 4፥12

የሰው ልጆችን የኀጢአት ውጤት ከሆነው የዘላለም ሞት ሊያድን የሚችለው አንዱ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው።(ዮሐ3:-16) ለመዳን አስፈላጊው ነገር እሱን መቀበል ነው።( ዮሐ1:-12) የሰውን ልጆች ሞት በመስቀል ላይ የሞተ እርሱ ብቻ ነው።እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሱን አስከመስጠት ድረስ የወደደህ ሊወድህም የሚችል የለም (ዮሐ15:-13) በአብ የተሰጠን አዳኝ ፣ እውነት ፣ሕይወት ፣ መንገድ እርሱ ብቻ ነው።(ዮሐ 14:-6) ከርሱ ውጭ ሊያድንህ የሚችል በሰማይም በምድርም የለም ። (ሐዋ 4:-12)
“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤...”
(1ኛ ጢሞ 1፥15)

አዳኝ መሆን የሚችል ፍጹም ንጹ ቅዱስ እንከን የሌለበት ከወዴት አለ ? ከሰማይ ከወረደውና የማዳኑን ሥራ ፈጽሞ ካረገው እና በአብ ቀኝ ከተቀመጠው ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አዳኝ መሆን የሚችል የለም። “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
— ሐዋርያት 4፥12
አስታራቂ ሆኖ በሰው ልጅና በእግዚአብሔር አብ መካከል መካከለኛ የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ ነው ።

" ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ።"(2ኛ ቆሮ 5:-18-19)
እግዚአብሔር አብ መካከለኛ እና አስታራቂ አድርጎ ያቆመው ሌላ አካል የለም ።

ስለዚህ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የግል አዳኝህ አድርገህ ተቀበል “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤”
— ዮሐንስ 1፥12

በእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ውስጥ ለመዳን እርሱን ለመቀበል ቀጠሮ አይሰራም ።“በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2
ስለዚህ ዛሬውኑ አሁኑኑ ወደ ማዳኑ ኑ !
28 views08:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 07:36:20
41 views04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ