Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2022-08-26 07:34:05 በአዲሱ ዓመት ጉዞው በመለኮት ብረሃን ነውና እንኳን ደስ አላችሁ !

ተነሱ እና አብሩ !

ኢየሱስ የዓለም ብርሃን ነው ”ደግሞም ኢየሱስ፦ ” እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ ፤የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም::” ብሎ ተናገራቸው። (ዮሐ 8፥12 )

ምክንያቱም ብርሃን የሆነው ጌታ እኛንም የዓለም ብርሃን አድርጎናልና:: “ እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ። በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሰወር አይቻላትም ”(ማቴዎስ 5፥14)
እኛ እናበራ ዘንድ ጌታ በተራራ ላይ ያቆመን ብርሃኖች ነን ለሁሉ የምናበራ መደበቅ የማይችል ለሁሉ የምንታይ የጌታ ክብር ነጸብራቆች ነን። “እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።” (2ኛ ቆሮ 3፥18)

ነገር ግን ማንም በጨለማ እየተመላለሰ ብርሃን ነኝ ሊል አይችልም። ብረሃኑም ጨለማውም የተገለጠ ነው ማንም ሁለት መልክ ሊኖረው አይችለም “ከእርሱ ጋር ኅብረት አለን ብንል በጨለማም ብንመላለስ እንዋሻለን እውነትንም አናደርግም፤” (1ኛ ዮሐ 1፥6) ጨለማ ከብረሃን ጋር አይስማማም ።ይለቁንም ጨለማ ብረሃን ሲመጣ ይሸሻል። አዎ በእኛ ድንቅ የመለኮት የህይወት ብርሃን ተገለጧል። የብርሃን ጥቅም የሚታወቀዉ ጭለማ በሚከበን ወቅት እንደ ሆነ ሁሉ እግዚአብሔር ደግሞ ለጭለማችን ብርሃን ነው ።

ትናንተ ለጽዮን ዛሬ ለኛ የተባለው "ብርሃንሽ መጥቶአልና፥ የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻልና ተነሺ፥ አብሪ።"(ት. ኢሳ 60:1) ለኛ ታውጇል እግዚአብሔር በነብዩ ኢሳያስ ተገለጠና በጽዮን ፊት ወጥቻለሁ እለ። እግዚአብሔር በጭለማው ላይ ብረሃን ይሁን አለ ። በጨለማ ከምትደነባበርበት፣ እንዳታዩ አይንን ከሚጋርድ ድቅድቅ ጨለማ ሊያወጣን ብረሃን ሆኖ የተገለጠ ጌታ ነው።እግዚአብሔር በመለኮት ብርሃን በስልጣኑ ቃል ሲገለጥ ነገር ይቅየራል !እግዚአብሔር በብረሃን በፊታችን ሲወጣ መጪው ጊዜ ብሩህ ይሆናል። አዲስና አስደናቂ የክብር ምዕራፍ ይከፈታል ፣ የብልጽግና፣የጉብኝት፣ የተሐድሶ ምዕራፍ ይከፈታል። በመለኮቱ ብረሃን ፊት ሊቆም የሚችል ምንም የለም ።

ሰይጣን ሰዎች ወደዚ ድንቅ መለኮታዊ ብረሃን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲመጡ አይፈልግም። እውነት እንዳያዩ ይከድንባቸዋል የልቦናዎቻቸውን አይኖች ያሳውራል ።ለዚህ ነው ቅዱሱ ቃል:- "ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉ ነው።
ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።" (2ኛ ቆሮ 4 :-3 -4 )
የመለኮቱ ብርሃን ሲገለጥ ማዳኑን እንዳታይ ያደረገህን ቅርፊት ከአይንህ ላይ ይጥለዋል ።የመለኮቱ ብርሃን ሁለንተናዊ ክብር፣ ምርኮ ፣አስናቂ ጉብኝት የያዘ የመለኮት ብረሃን ነው።

ነገር ግን ከእንግዲህ ነገር እንዳለ አይቅጥልም ዛሬ የምታየው የጭለማው ብርታት ብርሃንህ ደምቆ እንዲበራ ነው ። ብርሃን ትርጉም የሚኖረው በድቅድቅ ጭለማ ውስጥ ነው ። ብረሃን በፊታችን ስለወጣ የኛ ጨለማ በመለኮቱ ብረሃን ተወግዶአል።ብርሃንህ ወጥቶአል ተብለሃል።ለጽዮን የእግዚአብሔርም ክብር ወጥቶልሻል አላት ።እና ? ተነሽ ፣ አብሪ የመጣው ክብር ብረሃናዊ ክብር ነው። ምርኮዋችንን፣ ብልጽግናችንን፣ ክብራችንንና ሞገሳችንን የሽፈነ ድቅድቅ ጨለማ ጠራርጎ የሚያስወግድ ።

እግዚአብሔር በብዙ በረከት በፊታችን ስለወጣ የግዞት የባርነት የመከራና የስቃይ ዘመን እበቃ ። ብረሃን በፊትችሁ ከወጣ ከጨለማ ጋር ትግል የለም። ከመለኮት የብረሃኑ ክብር ኃያልነት እና ከተገለጠው ክብር የተነሳ ታላላቅ የተባሉ ሁሉ ከእግራችን ሥር ሆንዋል ።አንገት የመድፋትና በጨለማ የመጓዝ ዘመን እበቃ ። ታሪክ ተቀየረ ።የምስራች ለድቅድቁ ጨለማ የብረሃን ዘመን መጣ ! በዚህን ሰአት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ነኝ ለምትሉ ፣ ከመከራው ብዛት መነሳት ላቃታችሁ ፣ አበቃልኝ ብላችሁ የሞታችሁን ቀን ለምትጥብቁ ፤ ትናትና ካለፈው የእስራት ትዝታ መላቀቅ ላቃታችሁ፣ ማልቀሳችሁን ተውና ተነሱ አብሩ ይላችኋል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ።

ያለንበት ምዕራፋ የመነሳት ነው እንጂ አንገት የመድፋትና አይደለም። የመሳቅ እንጂ የማልቀስ አይደለም ። ባስጨነቃችሁ ጨለማ ላይ በመለኮት በብርሀን ልትስቁበት ዘመን መጥቷል ፣ አሁን ሰአቱ የመነሳት እንጅ የመተኛት እይደለም ፣ በብረሃን የመጓዝ እንጂ ግራ የመጋባት አይደለም። ጉዞአችንም በፊታችን የወጣውን አምላክ በመከተል ነው፣ የሚመራሃን የመለኮት ብረሃን አምላክ ካወቅህ ለመድረሻው ስጋት አይግባህ ።ወቅቱ ጨለማውን ፈርቶ የመተኛት ሳይሆን ተነስቶ የማብራት ዘመን ነው። የጨለማው ዘመን አልቆ የብርሃን ዘመን መጥቷልና።ተነሱና አብሩ ውረሱም።እግዚአብሔር በፊታችሁ ወጥቶአልና ። መጪው ዘመን በእግዚአብሔር ብሩህ ነው ። እናንተ የብረሃን ልጆች እንኳን ደስ አላችሁ መልካም አዲስ አመት ! ተባርካችኃል ።
41 views04:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 05:44:29
15 views02:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 05:42:24 በእግዚአብሔር አብ ፊት የሚሆን ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ !

“ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው፤ ወላጆች የሌላቸውን ልጆች ባልቴቶችንም በመከራቸው መጠየቅ፥ በዓለምም ከሚገኝ እድፍ ሰውነቱን መጠበቅ ነው።”
— ያዕቆብ 1፥27

ንጹሕ የሆነ ነውርም የሌለበት አምልኮ በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ይህ ነው ፤ መችም እግዚአብሔር አብ ደስ የሚሰኝበትን አምልኮ ማምለክ የማይፈልግ የለም ። አምልኮ መዘመር እልል ማለት ማሸብሸብ መስገድ ብቻ የሚመስላቸው ስፍር ቁጥር የላቸውም።

ለመሆኑ ድሆች ከቤ/ክ ያላቸው ድርሻ ምንድነው ? ከኔ ከቤቴ ከኑሮዬስ ያላቸው ድርሻ ምንድነው ?

ድሆች ጌታ ኢየሱስን ተክተው ነው ወደ ቤ/ክ ፣ወደ ቤትህ ፣ ወደ እኔ እና ወደ እናንተ የሚመጡት ስለዚህ በየቀኑ ከቤተክርስቲያን ከአንተ ካንቺ ድርሻ እንዳላቸው አስበህ ታውቃለህ ? አስበሽ ታውቂያለሽ ?" ተርቤ አላበላችሁኝምና፥ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝምና፥ እንግዳ ሆኜ አልተቀበላችሁኝምና፥ ታርዤ አላለበሳችሁኝምና፥ ታምሜ ታስሬም አልጠየቃችሁኝምና።"(ማቴዎስ 25 :-42-43)

ጌታ ተርቦ ፣ ተጠምቶ ፣ እንግዳ ሆኖ ፣ ታሞ ወደ እናንተ መጥቶ ያውቅ ይሆን ? እናንተስ አበላችሁት ወይስ አሳደዳችሁት ? ፣ ከጥማቱ አረካችሁት ወይስ ከነጥማቱ ውጣ ብላችሁ ከፈታተራችሁ በራችሁን ዘጋችሁበት ? ታርዞ አለበሳችሁት ወይስ ራቁቱን ሰደዳችሁት ? በእንግድነቱ ተቀበላችሁት ወይስ አባረራችሁት ? ታሞ አስታመማችሁት ወይስ በሕመሙ እንዲሞት ፈረዳችሁበት ? አያችሁ ይህ ጌታ ከክብሩ ያጠገባችሁ ፣ ከመንፈሱ ያረካችሁ የክብሩን መጎናጸፊያ ያለበስችሁ ፣ ከነ ኃጢያታችሁ ተቀብሎ በደሙ አጥቦ በጽድቁ ወልውሎ ሰው ያደረጋችሁ፣ ሕመማችሁን ታም ከሞት ያዳናችሁ ጌታ ነው ።

ራሱን አሳልፎ በሰጣችሁ ጌታ ላይ እንዴት ጨከናችሁ ? ተርቤ ሲላችሁ፣ ተጠምቻለሁ ብሎ ሲያለቅስ ፣
እንግዳችሁ ሆኜ መጥቻለሁ ተቀበሉኝ ሲላችሁ ፣ታምሜያለሁ ድረሱልኝ ሲላችሁ፣ ታስሬያለሁ ዋስ ሆናችሁ አስፈቱኝ ሲላችሁ ኧረ ስንቱ ምላሻችሁ እንዴት የጭካኔ የአረመኔነት ሆነ ?
ነው ወይስ እንደ እነዛ ይህንን ለመጠየቅ ነው የተዘጋጃችሁት "እነርሱ ደግሞ ይመልሱና፦ ጌታ ሆይ፥ ተርበህ ወይስ ተጠምተህ ወይስ እንግዳ ሆነህ ወይስ ታርዘህ ወይስ ታመህ ወይስ ታስረህ መቼ አይተን አላገለገልንህም? ይሉታል።ያን ጊዜ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ለአንዱ ስላላደረጋችሁት ለእኔ ደግሞ አላደረጋችሁትም ብሎ ይመልስላቸዋል " (ማቴዎስ 25 :-44-45)

የሚገርመው የምናከብረው የበዓል አበዛዝ ቀን እየቆጠርን ፣ ወር እየቆጠርን ዓመታት እየቆጠርን ለበዓላት ስም ሰይመን በቅዱስ ቃሉ ላይ ቢኖርም ባይኖርም አመሳስለን ፈጥረን ቀናትን ፣ በዓላትን ለማክበር የሚወዳደረን የለም ።

የድሆችን በዓል አክብር እናውቃለን ወይ
ጌታን እንደመጋበዝ እነርሱን ለመጋበዝ በዓል አድርገን እናውቅ ይሆን ? መች አይቼህ የት አግኝቼህ ትክክለኛ ምክንያት ሊሆን አይችልም ። ወገኔ ንቃ ንሰሐ ግባ የድሆችን በዓል አክብር ድሆችን የሚመገቡበት ቀን አዘጋጅ ወደ ቤትህ ጥራቸው ከረሐባቸው አጥግባቸው ፣ እርቃናቸውን ሸፍን ፣ ከጥማታቸው ይርኩ ፣ በእንግድነት ተቀበላቸው ፣ ከሕመማቸው አስታማቸው ፣ ካሉበት ባርነት ፍታቸው ። በእግዚአብሔር ፊት አውነተኛ ንጹህ ነውር የሌለበት አምልኮ ይህ ነውና።
አየህ ቅዱሱ ቃል “ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።”
— ምሳሌ 19፥17
ለእግዚአብሔር ያበድራችሁት ይከፈላል እግዚአብሔር ታማኝ ነው ። ለአንተ ለትውልድህ ለዘርህ ይከፍለዋል ይባርክሃል ።

እኛ ለበዓል ለግብዣ በልደት በሰርግ በማህበር የምንጠራው ነገ ብድራቱን የሚመልሱልንን ነው :- ቃሉ ግን እንዲህ ይላል “የጠራውንም ደግሞ እንዲህ አለው፦ ምሳ ወይም እራት ባደረግህ ጊዜ፥ እነርሱ ደግሞ በተራቸው ምናልባት እንዳይጠሩህ ብድራትም እንዳይመልሱልህ፥ ወዳጆችህንና ወንድሞችህን ዘመዶችህንም ባለ ጠጎች ጎረቤቶችህንም አትጥራ።”
— ሉቃስ 14፥12
ድሆችን ችግረኞችን መርዳት ስንፈልግ የምናደርገው ሳንፈልግ የምንተወው አይደለም ይህ ከጌታ የሆነ ትዕዛዝ ነውና
“ድሆች ከምድሪቱ ላይ አያልቁምና ስለዚህ እኔ፦ በአገርህ ውስጥ ላለው ድሀ ለተቸገረውም ወንድምህ እጅህን ትከፍታለህ ብዬ አዝዝሃለሁ።”
— ዘዳግም 15፥11

እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነው“ለድሃ አደጉና ለመበለቲቱ ይፈርዳል፥ መብልና ልብስም ይሰጠው ዘንድ ስደተኛውን ይወድዳል።”
— ዘዳግም 10፥18
እግዚአብሔር እውነተኛ ለድሀ አደጎች አባት አና ዳኛ ነው “እግዚአብሔር በቅዱስ ቦታው ለድሀ አደጎች አባት፥ ለባልቴቶችም ዳኛ ነው።”
— መዝሙር 68፥5

እስቲ በዚህ ቃል መስታወት ደግሞ ህይወታችንን እንቃኝ :-
1ኛ,ድሆች ከኔ፣ ከቤቴ፣ ከኑሮዬ ያላቸው ድርሻ ምንድነው ?

2ኛ,ለመሆኑ ድሆች ከቤ/ክርስቲያንስ ያላቸው ድርሻ ምንድነው ?

3ኛ, ልቴቶችን ወላጅ የሞቱባቸውን ልጆች በመርዳት ስንት እሁድ ስንት ቀን እግዚአብሔርን በእውነትና በመንፈስ በንጹህና ነውር በሌለበት አምልኮ ስንት ጊዜ አምልከን ይሆን ?

ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር አድርጉት ።
ተባረኩ !
16 views02:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 05:07:49
46 views02:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 05:07:15 ጽድቅ የሚገኘው እንዴት ነው ?

"…. አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል"(ማቲ 6፥33)፡፡

ጽድቅ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሁሉ አስቀድመን አንድንፈልጋቸው ካስተማረን ሁለት ነገሮች መካከል አንዱ ነው። ስለዚህ ጽድቅን መፈለግ ስለሆነ ጽድቅ ምን አንደሆነ ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡
ክርስቶስ በዚህ ትምርቱ ጽድቅን ፈልጉ ያለን ከመብልና ከልብስ አስቀድሞ ነው፡፡ ምግብና ልብስ ለመኖር ከሚያስፈለጉ መስረታዊ የሰው ልጆች ፍላጎቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በጌታ ፊት ግን ለኛ የተመረጠው ቀዳሚ ነገር ምግብና ልብስ መኖሪያም አይደለም። በመሆኑም ጌታ በተናገረው እውነት ለኛ ቀዳሚ መሆን ያለበት ጽድቅን ስለማግኘት ሊኖረን የሚገባው ፍላጎት ዕውቀት እና መርህ ነው። ይህ ለምግብ ለልብስ ለመኖርያ ካለን ፍላጎት ሊቀድም አንደሚገባው ጌታ በአጽንኦት ነግሮናል፡፡

የሚገርው ነገር ግን በኛ በሰዎች ዘንድ ነገሩ የተገላቢጦሽ ነው።ሰው ከጽቅ ይልቅ ምግብን ልብስን ስለማግኘት ብትነግረው ነው ደስ የሚሰኘው። ሌት ተቀን መትጋት ያለ ዕረፍት ቢሮጥ ዋጋ ቢከፍል ደስ የሚለውም ለምግብ ለልብስ ለቤት ነው።

በጌታ እይታ ግን ለሰው የተመረጠው ቀዳሚው ነገር ጽድቅን ለማግኘት የሚኖረን ትጋት በልጦ መገኘቱ ነው። ይህ ከሆነ ክርስቶስ በዚህ ደረጃ በቀዳሚነት አንድንፈልገው ያስተማረንን እውነት ጽድቅን ለማግኘት ያለን ፍለጋና ናፍቆት ምን ያህል ነው ? ስለ ጽድቅስ ምን ያህል አናውቅ ይሆን?

ጽድቅ ምንድን ነው?
ጽድቅ በመጽሐፍ ቅዱሰ ገለጻ እንከን አልባ ሕይወት ማለት ነው። በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም የሚያበቃ ፍጹምነትን መጎናጸፍ ማለት ነው።ስለዚህ ይህ ደግሞ በሰው ዘንድ የሚታሰብ አይደለም ። ከእግዚአብሔር ካልተሰጠ በቀር ሰው በራሱ ከራሱ ሊያገኘው የሚችለው አይደለም ። ለዚህ ነው መጽሐፍ ቅዱስ “ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሆነናል፥ ጽድቃችንም ሁሉ እንደ መርገም ጨርቅ ነው፤ ሁላችንም እንደ ቅጠል ረግፈናል፥ በደላችንም እንደ ነፋስ ወስዶናል።” (ት.ኢሳይያስ 64፥6)

ታዲያ ጌታ ከየት እንድናገኘው ነው ፈልጉ የሚለን ? “ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።”(ሮሜ 5፥9)
“እንግዲህ በእምነት ከጸደቅን በእግዚአብሔር ዘንድ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን እንያዝ፤” (ሮሜ 5፥1)
ጽድቅ የሚገኘው ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በሰራልንን ስራ በማመን ነው ። ኃጥያትህን ወስዶ ተቀጣ የዕዳ ጽሕፈትህን ደመሰሰው ። ክርስቶስ ሞትህን ወስዶ ሞቶ ሕይወት ይሰጥሃል። ያኔ በክርስቶስ ሆነህ አዲስ ፍጥረት አንከን አልባ የጽቅ ሕይወትን ትጎናጸፋለህ ።ስለዚህ ጽድቅን መፈለግ ኢየሱስ ክርስቶስን መፈለግ በርሱም አምኖ መዳን ነው።“... በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።”(1ኛ ቆሮ 6፥11)

የጽድቅን ደረጃ ክብር ከፍ የሚያደረገው ጸድቅ ከእግዚአብሔር በኢየሱስ ክርስቶስ የሚሰጥ መሆኑ ነው፡፡ ክርስቶስ አስቀድማችሁ ፈልጉ ያለን ጽድቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የገነነ ዋጋ የሚሰጠው በርሱ ዘን ለዘላለማዊው ሕይወት ተቀባይነት እንዲኖር የሚያደርግ ነው ።

ጌታችን ጽድቅ ስለሚገኝበት መንድ በምሳሌ ያስረዳበትን ሁኔታ ሉቃስ አንዲህ ሲል በወንጌሉ አስፍሮታል "ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል፦ ሁለት ሰዎች ሊጸልዩ ወደ መቅደስ ወጡ፥ አንዱ ፈሪሳዊ ሁለተኛውም ቀራጭ። ፈሪሳዊም ቆሞ በልቡ ይህን ሲጸልይ፦ እግዚአብሔር ሆይ፥ እንደ ሌላ ሰው ሁሉ፥ ቀማኞችና ዓመፀኞች አመንዝሮችም፥ ወይም እንደዚህ ቀራጭ ስላልሆንሁ አመሰግንሃለሁ፤ በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ እጦማለሁ፥ ከማገኘውም ሁሉ አሥራት አወጣለሁ አለ። ቀራጩ ግን በሩቅ ቆሞ ዓይኖቹን ወደ ሰማይ ሊያነሣ እንኳ አልወደደም፥ ነገር ግን፦ አምላክ ሆይ፥ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ እያለ ደረቱን ይደቃ ነበር። እላችኋለሁ፥ ከዚያ ይልቅ ይህ ጻድቅ ሆኖ ወደ ቤቱ ተመለሰ፤ ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳልና፥ ራሱን ግን የሚያዋርድ ከፍ ይላል›› (ሉቃ 18፣ 9-14)፡፡

በዚህ ምሳሌ ጌታ ያስተማረው እውነት ሰው በራሱ መመዘኛ ራሱንም ማጽደቅም ሆነ ሌላውን ማጽደቅ እንደማይችል ነው።
በዚህ ምሳሌ ተመጻዳቂው አንዴት እራሱን አንዳጸደቀ ሌላውን ግን እንደኮነነ የሚያሳይ ሲሆን ጽድቅ ከሚያጸድቅ ከእግዚአብሔር ብቻ ሊሰጥ የሚችል ነው

በሌላ መልኩ ሰው ጽድቅ ስለሚገኝበት መንገድ ያለውን እውቀት እና እግዚአብሔር ጽድቅን የሚሰጥበት መንገድ ምን ያህል የተራራቀ እንደሆነ እናያለን ። ይህ ሰው እራሱን ለማጽደቅ እራሱን የመዘነበት መስፈርትና የእግዚአብሔር መስፈርት ልዩነት ፡፡ ወገኔ ስለአንተ ክርስቶስ ተመዝኖ በድቅ ብቃት ሚዛኑን ደፍቶ አለፎአል። ለመዳንህ የሚያስፈልግህ የኢየሱስ ክርስቶስ ጽድቅ ነው። ካንተ ባንተ ላንተ የሆነ ምንም የለም
በመሆኑም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመናችሁ ብቻ “....በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም በአምላካችንም መንፈስ ታጥባችኋል፥ ተቀድሳችኋል፥ ጸድቃችኋል።”(1ኛ ቆሮ 6፥11)

ስለዚህ :-
1ኛ, ጽድቅን ከኛ በኛ ለኛ ማግኘት
አንችልም !
2ኛ, በቃሉ መርህ ቅድሚያ ሊሰጠው
ለሚገባው ጽድቅ ቅድሚያ በመስጠት
መፈልግ ይገባናል!
3ኛ, ለሰው ልጅ መዳን የሆነው ጽድቅ
የሚገኘው በኢየሱስ ክርስቶስ
በማመን ብቻ እንደሆነ ማወቅ
ይገባል !
19 views02:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 04:10:32 አዲስ ፍጥረት ሆነሃል !

ኢየሱስ ክርስቶስን በእምነት የግል አዳኝ አድርህ ስትቀበል በእግዚአብሔር አስራር እና እይታ ከደሙ የማንጻት እና የመቀደስ እንዲሁም ሕይወት የመስጠት ጉልበት የተነሳ እንደገና በመፈጠር ዳግመኛ ተወልደህ አዲስ ፍጥረት ሆነሐል ማለት ነው ። መችም አዚህ ጋ የኒቆዲሞስን ጥያቄ እንደማትጠይቅ ተስፋ አደርጋለሁ ከሆነም ዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሦስትን አንብብ ።

ለዚህም ነው መጽሐፍ ቅዱስ :-"ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል"(2 ቆሮ 5:17)

ስለዚህ አዲስ ፍጥረት የሚያደርግህ ፣ አሮጌ ነገርህን አውልቆ ጥሎ፣ የኃላ ሰውኛ የእርኩሰት ኃይልን አስወግዶ መንፈስህን ነፍስህን ሥጋህን ቀድሶ እንከን አልባ ሁሉን አዲስ የሚያደርገው የክርስቶስ የልውውጥ ሥራ ነው ።አሜን !
“የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።”( 1ኛ ተሰሎንቄ 5፥23)

ስፍራህ ተቀየረ ክርስቶስ ኃጢያትህን ወሰደው የርሱን እንከን አልባ ቅድስና ሰጠህ ! ሞትህን ወስዶ ሕይወት ሰጠህ ፣ቅጣትህን ወስዶ አሳረፈህ ፣ እርሱ ስለአንተ ኃጢያት ሆኖ ተቀጣ እንጂ ኃጢያተኛ አይደለም ።“እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።” (2ኛ ቆሮ 5፥21)

" በክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔርን የክብሩን እውቀት ብርሃን እንዲሰጥ በልባችን ውስጥ የበራ። በጨለማ ብርሃን ይብራ ያለ እግዚአብሔር ነውና።መንፈስ ቅዱስ በሚገዛበት በእግዚአብሔር ፍጹም አዲስ ዓለም ውስጥ የሚኖሩ አዲስ ፍጥረት ይሆናሉ"(2 ቆሮ 4:6) አሜን !
ስለዚ በእግዚአብሔር አጠራር እና አሰራር አዲስ ፍጥረት ተደርገሃል ጸድቀሃል ፣ ተቀድሰሃል ፣ በራስህ ሳይሆን በክርስቶስ ፍጹም እንከን አልባ ተደርገሃል የሞት መውጊያ የኃጢያት ጉልበት ተሰብሮ አምልጠሃል ድነኃል ።

" በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።"(ሮሜ 8:14) አኗኗርህ ተቀይሮአል የሚመራሕ የሚያኖህ አንተም የምትኖርበት ዓላማ ተቀይሮአል።" በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።"(ገላ 5:25)

" እኛ ፍጥረቱ ነንና እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።" አዲስ ፍጥረት የተደረግነው በዓላማ ነው። ከእንግዲህ ሥጋችን ሥሜታችን ኃጢያተኛ ማንነታችን በሚመራን መኖር አንችልም ። የገዛን የዋጀን ያዳነን ለክብሩ የሚኖረን ቀድሶ የሚያኖር ድንቅ መሪ አለን።

ጌታን የግል አዳኙ አድርጎ የተቀበለ አዲስ አማኝ አዲስ ስው ሆኖአል። የርስቱ መያዣ በሚሆን መንፈስ የእግዚአብሔር ንብረት ሆኖ ታትሞአል ፣ በደሙ ተገዝቶአል ከእንግዲህ የራሱ ሊሆን አይችልም ። (1ቆሮ 6:-19)

" በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና።"(ገላ 6:15)
አስራሩ ውስጣዊ እንጂ ውጫዊ ሥርዓትን መፈጸም አይደለም ከወስጥ የጀመረው ውስጣዊና መንፈሳዊ ለውጥ ሁለንተናን በሚያጥለቀለቅ የመለኮት ብረሃን የሚያኖር ይሆናል መልኩ ፈጽሞ ይለውጣል ።

ጌታን ካመንክባት ጌዜ ጀምሮ በሚረዳህ የመለኮት ጸጋ፣ በተለወጠ ማንነት፣ ኢየሱስ ክርስቶስን በመምሰል ለክብሩ የምትኖር ተደርገሃል ። " ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።"(ኤፌ 4:24)

ሁለንተናህ እግዚአብሔርን ለመመሰል ይታደሳል !

" እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።(2ቆሮ3:18)

አሮጌው የኃጢያት ባርነት ኑሮ አብቅቶ በሞተልህ ሞትህን በሻረው የኃጢያት ዕዳህን በቀደደው ጌታ አርነት ወጥተህ በነጻነት ትኖራለህ። ስለዚህ “በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።” ( ገላትያ 5፥1)
9 viewsedited  01:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 08:35:30 መመኪያህ እግዚአብሔር ይሁን !
******
“ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር።”
— ኤርምያስ 9፥24

እግዚአብሔር የሚደሰትበትና የሚናገርህ እውነት ይህ ነው። በዘርህ ፣በብሔርህ፣ በዝናህ፣ በሐብትህ እና ከምድር በሚሆን ምድራዊ ነገር ሁሉ አትመካ ። የሰው ልጅ ጉልበት ይከዳዋል፣ ዝናም ያልፋል፣ ሀይልም ይደክማል፣ ገንዘብም ይጠፋል፣ ስልጣንም ይሻራል፣ እውቀትም ይዘነጋል፣ አጃቢም ይበተናል፣ በምድር ያለ ሁሉም ነገር ከንቱ ነው።

በእግዚአብሔር የሚመካ እርሱ ጠቢብ ነው።ወገኔ "እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም "
" አቤቱ፥ በአማልክት መካከል እንደ አንተ ያለ ማን ነው? በምስጋና የተፈራህ፥ ድንቅንም የምታደርግ፥ በቅድስና የከበረ እንዳንተ ያለ ማን ነው?"( ዘጸአት 15 ፡11 - 14) የተባለለት
ሙሴ እግዚአብሔር ን ስለሚያውቀው ኃይሉን፣ ሥልጣኑን፣ ክብሩንና ማዳኑን ስላየ በሀይል በችሎታ በሞገስ በስልጣን ...እንዳተ ያለ ማነው ብሎ ተናገረ።

የእግዚአብሔርን ክብር ፣ግርማ ፣ማንነት መግለጽ ማን ይችላል ? እግዚአብሔር ታላቅ ነው! ብሎ ከማለፍ ውጪ። ሰውም ልግለጠው ስለ እርሱ ልናገር ቢል በሙሉ ማንነቱ ሊገልጠው አይችልም። ስለ እግዚአብሔር ልናገር ልግለጠው እንኳ ቢል በስራውና በተግባሩ ነው።

ነብዩ ኤልያስ " ሰምቶ በእሳት የሚመልስ እርሱ አምላክ ተብሎ ይመለክ አለ። "ንጉስ ዳዊት " እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ በአምላካችን ከተማ በተቀደሰ ተራራ ምስጋናው ብዙ ነው።አለ"(መዝ 48:1)
ዓለም እንኳን እግዚአብሔርንየእጁን ሥራ እንኳ መርምራ ልትደርስበት አልቻለችም።
“አቤቱ፥ ሥራህ እጅግ ትልቅ ነው፥ አሳብህም እጅግ ጥልቅ ነው።” (መዝሙር 92፥5)
ባለጸጋው ኢዮብ " እነሆ፥ እግዚአብሔር ታላቅ ነው፥ እኛም አናውቀውም። የዘመኑም ቍጥር አይመረመርም። "አለ ( ኢዮብ 36:-26)

አንተስ ማን ትለዋለህ ?
የዚህ ታላቅ አምላክ ክብር ፣ገናናነት ፣ሁሉን ማወቅ፣ የጽድቅ ፍርድ፣ ተዓምራት ፣ ማዳኑ ፣ ለአንተ ያለው ፍቅር ካላስመካህ በምድር ምን ሊያስመካህ ይችላል ?
በአምላካችን በእግዚአብሔር በማምለክህ ፣ እርሱ ወደ ያዘጋጀልህን የከበረ የማዳን ሥራ የማይመረመረውን ድንቅ ፍቅሩ ቸርነቱ በጎነቱ ታማኝነቱ እርሱን በጊዜውም አለጊዜውም እንድታመልከው እንድታከብረው እንድትወድሰው እንድትመካበት ካላደረገህ ሌላ ሊያስመካህ የሚችል በምድር ላይ ምን አለ ?

" ይሹሩን ሆይ፥ በሰማያት ላይ ለረድኤትህ፥ በደመናትም ላይ በታላቅነት እንደሚሄድ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማንም የለም ።" (ዘዳግም 33: 26) የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ! ኃይል የእግዚአብሔር ነው።ሁል ጊዜ እግዚአብሔርን አስቀድም! እርሱ በፊትህ ሲሄድ
1,ተራራ ትክክል ይሆናል !
2,የናሱ ደጅ ይሰበራል !
3,የብረት መወርወሪያ ይቆረጣል !
4,የተሰወረ ሀብት ይገለጣል !...ወዘተርፈ (ት. አሳያስ 45:2) እግዚአብሔር ከሰማይ በሚሆን ሰማያዊ በረከት ከምድርም በሚሆን ምድራዊ በረከት አትርፎ አትረፍርፎ ይባርክሃል !

ፍለጋህ “ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።”(ማቴዎስ 6፥33)
እግዚአብሔር አምላኬ ! አባቴ ! አዳኜ ! መመኪያዬ ! አለኝታዬ ! መሸሸጊያዬ ! መኖርያዬ ! ክብሬ ! ሞገሴ ! አመሰግንሃለሁ አከብርሃለሁ አመልክሃለሁ እወድስሃለሁ ለኔ እንደ አንተ ያለ አፍቃሪ እውነተኛ ወዳጅ በሰማይም በምድርም የለም ! አንተ ለኔ ትምክህቴ ነህ !!!
21 views05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 20:40:57 " ስለዚህ የማይናወጥን መንግሥት ስለምንቀበል በማክበርና በፍርሃት እግዚአብሔርን ደስ እያሰኘን የምናመልክበትን ጸጋ እንያዝ፤"
(ወደ ዕብራውያን 12:28)
" ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።"(ዮሐ 20:31)

1ኛ, ለሚሻለው ለአዲሱ ኪዳን ዋስ የሆነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ 7:-17 -22)

2ኛ, ወደ አብ የሚያደርስ እውነት ሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ( ዮሐ 14:-6)

3ኛ,ለሚታዘዙት ሁሉ የዘላለም መዳን ምክንያት የሆነ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ 5:-10)

4ኛ,የአዲስ ኪዳን መካከለኛ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ 9:-15)

5ኛ,የዘላለም ቤዛነት ያስገኘ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ 9:-12)

6ኛ,በእግዚአብሔር ፊት አሁን ስለ እኛ የሚታይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ 9:-24)

7ኛ,የእምነታችን ራስና ፈፃሚ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (ዕብ12:- 2)
30 views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 20:40:57 ቀኑ እንደሌባ ድንገት ሳይደርስባችሁ አማራጭ ወደ ሌለው በእግዚአብሔር ወደ ተዘጋጀው የደህንነት መንገድ ግቡ !

ሰው ለመዳን በራሱ ለራሱ ሊያዘጋጀው የሚችለው የህንነት መንገድ የለም። የሰው ልጅ በኃጢያቱ እንዳይጠፋ አንዲያ ልጁን ኢየሱስ ክርስቶስን የሰጠው እግዚአብሔር አብ ነው። በእግዚአብሔር ለኛ የተዘጋጀው የመዳኛ መንገድ አንድ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከርሱ ውጪ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
(ሐዋ ሥራ 4፥12 )
ለሰው ልጅ ኃጢያት በመስቀል ላይ ተሰቅሎ የሞተ ፣ የተቀበረ፣ በሶስተኛውም ቀን የሞትን ጣር አጥፍቶ የተነሳ ለሚያምኑበትም የትንሳኤ በኩር ሆኖ የዘላለም ሕይወትን ያወጀ ብቸኛ እውነት ሕይወት እና መንገድና አዳኝ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው ።

ሌላ አዳኝ ሌላ አስታራቂ ሌላ መካከለኛ አያስፈልገንም በቃ አለቀ የስውን ልጅ ወደ አብ ለመድረስ ብቸኛ መንገድ ከአብ ጋር ለመታረቅ ብቸኛ አስታራቂ ለኃጢያት ሥርየት የሞተ ብቸኛ አዳኝ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው። ይህ መጽሐፍ ቅዱስ የሚናገረው እውነት ነው ። “ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”( ዮሐንስ 14፥6)

በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን እግዚአብሔር አብ ነው።
" ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ"(2ኛ ቆሮ 5:-18-19)ስለዚህ ለመዳን የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እናት ማርያምን ፣ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ መልዓክቶችን ወዘተርፈ ለነርሱ ታላቅ አክብሮት ቢኖረንም እንዲያማልዱን የምንማጸንበት ምክንያት የለም ። ምክንያቱም ለመዳን የተሰጠን ሌላ ሥም ከሰማይ በታች የለምና።

ታዲያ ይህን የወንጌል የምስራች ለዓለም ሁሉ ስበኩ ብሎ ያዘዘንም አዳኙ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው ።“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”(ማቴ 28፥19-20)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በማዳኑ ልዩ የሚያደርገው እርሱ እኛን የሰው ልጆችን ለማዳን አምላካዊ ዙፋኑን ጥሎ የወረደ ፣ ሰው ሆነ ፣ ጸጋና እውነትን ተሞልቶ በኛ አደረ ፣ ስለ ሰው ልጆች ኃጢያት የመስቀል ሞትን ተቀብሎ ኃጢያታችን ያመጣብንን ሞት በሞቱ ሻረው ፣ በአንዴ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ሆኖ መካከለኛ ሆኖ ከአብ ጋር አሰታረቀን። ሌላ በዚህ መልኩ ተገልጦ የመጣ አዳኝ በሰማይም በምድርም የለም። ለዚህ ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ብቸኛ አዳኝ የምንለው።

ለመሆኑ ስበኩ የተባልነው ወንጌል ምንድነው ? ማነው ? “ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።” (ሮሜ 1፥3-4)
ምክንያቱም ነብያት የተነበዩለት ፣በወንጌላት የተገለጠ ፣ በሐዋርያት የተሰበከ ፣ በመልዕክቶች በርሱ የተገኘው በረከት የተብራራ በዮሐንስ ራዕይ በክብር የተገለጠ የሙሉ መጽሐፍ ቅዱስ መልዕክት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ነው ። “ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።”(ሮሜ 11፥36)

ከነብያት ነቢዩ ኢሳያስ ይጠየቅ “ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”
— ኢሳይያስ 7፥14

1ኛ, ከጻድቃን ሰመዕታት እስጢፋኖስን ጠይቁ :-

"መንፈስ ቅዱስንም ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት የእግዚአብሔርን ክብር ኢየሱስንም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፦እነሆ፥ ሰማያት ተከፍተው የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ አለ።"(ሐዋርያት 7:-55-56)

2ኛ, የጌታችን እናት ማርያም ትጠየቅ:-

“ማርያምም እንዲህ አለች፦ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች፥ መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች፤(ሉቃስ 1:-46-47)

3ኛ, ሐዋርያት ይጠየቁ :-

“እኛስ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም ማለት አንችልም አሉአቸው።” (ሐዋርያት 4፥20)
“መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
— ሐዋርያት 4፥12

4ኛ, መላዕክቶችን ጠይቁ:-

"መልአኩም እንዲህ አላቸው፦ እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና" (ሉቃስ 2:-10-11)

5ኛ, እግዚአብሔር አብን ጠይቁ :-

“እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።”(ማቴዎስ 3፥17)

እነዚህ ሁሉ የኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት ሕያው ምስክሮች ናቸው ። እኛም የርሱን ብቸኛ አዳኝ ምስክሮች እንድንሆን ተልከናል። ነገር ግን የወንጌሉን እውነት ለመበረዝ ለመሸቃቀጥ ሰይጣን ሌት ተቀን ይተጋል። አንዳንዶችን የራሳቸውን የመዳን መንገድ ወሳኝ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል። ሌሎችን ደግግሞ የደህንነትን የወንጌል እውነት እንዳያስተውሉ መንፈሳዊ አይኖቻቸውን ያሳውራል።

"ወንጌላችን የተከደነ ቢሆን እንኳ የተከደነባቸው ለሚጠፉ ነው።ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።(2ኛ ቆሮ 4:-3-4)
ሌሎችን ደግሞ አንደ ፈሪሳወያንና እንደሰዱቃውያን በሌሉበት ሕይወት ራሳቸውን እንዲቆልሉ በማድረግ ከማዳኑ የወንጌል እውነት እንዲጎድሉ ያደርጋል ።

እውነተኛው የወንጌል ማዳን ሲሰበክ የማይወደው ሰይጣን ብቻ ነው ምክንያቱም ምርኮ ያመልጠዋል ፣ ሰዎች እውነቱን አውቀው ከሲኦል ያመልጣሉ ፣ አምነው ይድናሉ የኃጢያታቸውን ሥርየት ያገኛሉ ፣በርሱ ከአብ ጋር ይታረቃሉ ፣ከሞት ወደ ሕይወት ይሻገራሉ ፣ሰዎች ከሰይጣን እስራት ይፈታሉ እግዚአብሔር በስረዓትና በወግ ሳይሆን በእውነትና በመንፈስ ይመለካል፣ታዲያ ሰይጣን ይህ ካላበሳጨው ምን ሊያበሳጨው ይችላል ??? ታዲያ እኔ በኢየሱስ ክርስቶስ አምኛለሁ ድኛለሁ የሚል ሰው ሌላው በእርሱ አምኖ ሲድን ደሥ ይለዋል እንጂ ምን ያበሳጨዋል ? ወንጌል እኮ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በቃ ሌላ ወንጌል የለም ! ወገኔ ፍጠን “በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”( 2ኛ ቆሮ 6፥2) ነገ ያንተ አይደለምና ጌታን እንደ ግል አዳኝህ ተቀብለህ ዳን ። ከተቀበልክና ከዳንክ ደግሞ ወንጌሉን ስበክ ።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰው ልጅ መዳን ብቸኛው የአዲስ ኪዳን ዋስ ነው ።
54 views17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 07:20:47 ለመሆኑ በቤታችን ብዙ መንፈሳዊ ቻናሎች እያሉ ለምን ወደ ቤ/ክ እንሄዳለን ???

ባለንበት ዘመን ይህ የብዙ ክርስቲያኖች ጥያቄ እየሆነ እንደመጣ ያውቃሉ ? ከዚህ የተነሳ እቤቴ ሆኜ አስደናቂ ፕሮግራም በቴሌቪዥን እከታተላለሁ ሲሉ ይደመጣል ። በአንጻሩ ደግሞ ማምለክ ማለት ቤ/ክ መሄድ ብቻ የሚመስላቸው እና ጌታ ጸሎት ቤት ሲመጡ እንጂ ቤታቸውን የማያውቅ ማለትም በቤታቸው ጌታን የማያመልኩ ስፍር ቁጥር የላቸውም። በሌላ መልኩ ደግሞ ሲመቸኝ ቸርች እሄዳለሁ በቤቴም ሲመቸኝ ጊዜ ሲኖረኝ እጸልያለሁ የሚሉ አሉ። ይህ አመለካከት ምን ያህል የሚያዋጣ ነው።

እነዚህ እሳቤዎች በማንኛውም ሰው ውስጥ አራት ወሳኝ ጥያቄዎችን ያጭራሉ ።
1ኛ, ጌታ የሚመለከው በቤት በቻናል ብቻ ነው ወይ ?
2ኛ,ጌታ የሚመለከው በሳምንት አንድ ቀን እሁድ ቸርች ሲኬድ ብቻ ነው ወይ ?
3ኛ,ጌታ የሚመለከው ሲመቸን ጊዜ ሲኖረን ብቻ ነው ወይ ? የሚሉት ወሳኝ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሹ ጥያቄዎች ናቸው።
4ኛ, ወደ ቤ/ክ የሚሄደው ለማምለክስ ብቻ ነው ወይ ?

“ኢየሱስም እንዲህ አላት፦ አንቺ ሴት፥ እመኚኝ፥ በዚህ ተራራ ወይም በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል።”
— ዮሐንስ 4፥21

ጌታ በዚህ ተራራ ወይም በኢየሩሳሌም ለአብ የማትሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አለ። እግዚአብሔርን ማምለክ በስፍራ ሁሉ ፣ በጊዜ ፣ በዘር ፣ በሐገር ፣ በቦታ ሁሉ ሳይወሰን ይመለካል ።

" ነገር ግን በእውነት የሚሰግዱ ለአብ በመንፈስና በእውነት የሚሰግዱበት ጊዜ ይመጣል አሁንም ሆኖአል፤ አብ ሊሰግዱለት እንደ እነዚህ ያሉትን ይሻልና፤
²⁴ እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።"(ዮሐንስ 4:-23-24)

በእውነት እና በመንፈስ ለእግዚአብሔር ይመለካል ለእርሱም ይሰገዳል።
የቤተክርስቲያን መስራችና ባለቤት እግዚአብሔር ነው ።“እኔም እልሃለሁ፥ አንተ ጴጥሮስ ነህ፥ በዚችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሉአትም።”
— ማቴዎስ 16፥18

ስለዚህ ቤ/ክ ለመሪዎና ለአገልጋዮች ይጠብቋትና ያገለግሏት ዘንድ አደራ ተሰጥቶአቸው እንጂ ባለቤት አይደለም።
“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
— ሐዋርያት 20፥28

ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር ዓላማው ጠርቶ የለያቸው ቅዱሳን ናቸው። በጌታ አምነው የዳኑ ቅዱሳን ህብረት ነው። ጌታ በሕብረት እንዲያመልኩ ፣ አብረው እንጀራን እንዲቆርሱ ፣ሁሉም በተሰጠው ጸጋ እርስ በርሱ እንዲተናነጽ ታዟል፡፡
ወደ ቤተክርስቲያን የምሄደው ለማገልገል ብቻ ሳይሆን ለመገልገልም ጭምር ነው ። እያንዳንዱ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል በሆነችው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የአካሉ ብልት ነው። በህብረት ፣በአንድነት ፣በፍቅር ፣ በመተጋገዝ ፣ በመረዳዳት የበረታው የደከመውን በመሸከም .... ወዘተርፈ አንዱን አካል (የክርስቶስ አካል በሆነችው በቤተ ክርስቲያን) ለማነጽ በተሰጠው ጸጋ ይተጋል ፣ ያገለግላል ለጌታው ክብር ሌት ተቀን ይሮጣል።

ማንኛው አማኝ ክርስቲያን ነኝ የሚል ሁሉ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ላለው ሁለንተናዊ ዕድገት በርሱ ያለው ጸጋ ለሌሎች መታነጽ እና በሌላው ሰው ያለው ጸጋ እርሱ እንዲታነጽበት የተሰጠ መሆኑን ማወቅ ይኖርበታል ፡፡ በቅዱስ አጠራሩ ያዳንን ጌታ በተሰጠን ጸጋ ምን አንደሰራንበት ይጠይቀናል ። ጸጋው ያለው በኛ ቢሆንም የተሰጠው ለቤ/ክ መታነጽ መሆኑን መረዳት ይኖርብናል ።

ወደ ቅዱሳን ህብረት መምጣት ያለብህ ስለታዘዝክ ነው።እግዚአብሔር ቅዱሳን ሕብረት እንዲያደርጉ አዞአል ። በዚያም በረከትን አዟል ። ደግሞም አንተ አንድ ሰው ነህ በቅዱሳን ሁሉ ያለውን ጸጋ መካፈል ለመንፈሳዊ ሕይወትህ ወሳኝ ነው።

ከቅዱሳን ሕብረት መቅረት ከበረከት መጉደል ነው ። ደግሞም በመጨረሻው ዘመን ይህ እንደ ልማድ እንደሚታይ ቃሉ ይናገራል ።

"ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደ ሆነው፥ መሰብሰባችንን አንተው እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ፤ ይልቁንም ቀኑ ሲቀርብ እያያችሁ አብልጣችሁ ይህን አድርጉ።"(ዕብራ 10:-24 - 25) ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን የምንተያየት ህብረት ስለሆነ ነው ።
በመጨረሻው ዘመን መገለጫ ምልክቶች ከመሆን ይጠብቀን።በመንም መልኩ መርህ ስለሆነ ከቅዱሳን ሕብረት መጉደል የለብንም።

እግዚአብሔር በቅዱሳን ሕብረት እንደሚገኝ ተስፋንም ሰጠ “ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።”
— ማቴዎስ 18፥20 እግዚአብሔር በሚገኝበት መገኘት እንዴት ደስ ያሰኛል ።

በቅዱሳን ሕብረት በመመካከር በመማማር በመተነናነጽ በመበረታታት ከድካም የምወጣበት የምንበረታታበትና ፀጋ የምቀበልበት ቤት ስለሆነ ነው ።

ከቅዱሳን ሕብረት ከሚያስቀሩ ምክንያቶቼ ይልቅ እጅግ የሚጠቅመኝ ሕብረት እንዳደርግ የሚያደርጉኝ ምክንያቶቼ ስለበለጡ ነው፡፡ ቤተክርስቲያንን ሰው ቢመራትም የተመሰረተችው በጌታ ከመሆኑም በላይ የእግዚአብሔር እንጂ የሰው እንዳልሆነች መረዳት ይኖብናል፡፡

ከቅዱሳን ሕብረት ከቤተክርስቲያን የሚበልጥ ቦታ የለም ምክንያቱም እግዚአብሔርን የምናመልክበት፣ ከታዘዘው በረከት የምንካፈለው በዚያ ስለሆነ ። ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ መልካምና ያማረ ስለሆነ ነው። በሕብረት መካከል ለዘላለም የተወሰነውን በረከትና ሕይወት አለ። በክርስቶስ አካል ላይ እኛ ያለ ወንድሞች ህብረት ሙሉ አንሆንም።

ከህብረት መጉደል ከለላ ማጣት ፣ ከበረከት መጉደል ፣ትህዛዝን መተላለፍ ነው ።ከህብረት መጉደል የሌላውን ፀጋ አለመቀበል ነው ።ከህብረት መጉደል ለጠላት መጋለጥ ነው
ከህብረት መጉደል ምኞትን መከተል ነው

" ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።...
... በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና። "(መዝሙር 133 :-1-4)

1ኛ,ከቅዱሳን ከህብረት ከሚያርቅህ ነገር ራስህን ጠብቅ
ተጠንቀቅ (ዕብራ 10:-24-25)

2ኛ,እግዚአብሔርን በስፍራ ሁሉ አምልክ ኑሮህ ሥራህ ድርጊትህ ሐሳብህ መውጣት መግባትህ ...ወዘተርፈ ያምልከው ! በቤትህም በቤተክርስቲያንም የቤትህ ራስ የሆነው እግዚአብሔር ይመለክ ! (ዮሐንስ 4:-23-24)

3ኛ,የሚመራህ መንፈስ ቅዱስ ምልልስህም ለእግዚአብሔር ክብር ... ይሁን “በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።”(ሮሜ 8፥14)

4ኛ, የአካል ብልቶች ተለያይተው መኖር እንደማይችሉ እግር ለእጅ አይን ለጆሮ አንዱ ለሌላው አስፈላጊ የሆነውን ያህል አንተም ለሌላው ሌሎችም ለአንተ አስፈላጊ እንደሆኑ እወቅ ። (1ኛ ቆሮ12:-14-26)
53 viewsedited  04:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ