Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2022-05-15 06:13:41 ክርስትና ክርስቶስ በኛ የሚኖረው ሕይወት ነው !

“እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ፥ ኃጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ በሰማያት በግርማው ቀኝ ተቀመጠ፤”
( ዕብራ 1፥3)

“እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን።”
(2ኛ ቆሮ 3፥18)

ክርስትናን የኖረ ዛሬም መኖር የሚችል ወደፊትም መኖር የሚችል ክርስቶስ ብቻ ነው።ጌታ በኛ የሚኖር ከሆነ በኛ ለመገለጡ ምንም ጥርጥር የለም። ምክንያቱም በኛ የመኖሩ ሚስጥር እኛን በራሱ መልክ መግለጥ ነው።ክርስትና ጌታ በኛ የሚኖረው ሐይወት አንጂ እኛ የምንኖረው ሕይወት አይለም ።
ከኛ የሚጠበቀው እርሱን መቀበል፣በርሱ ማመን፣በደሙ ከኃጢያት መንጻታችንን አምኖ መቀበል ። እርሱ በኛ እንዲኖር መፍቀድ ፣ ለርሱ የተሰጠ ሁለንተናን መያዝ ነው ።

ክርስቶስ ሁሉን በመስቀል ላይ ጨርሶ ይህንን ሕይወት ባንተ እንድኖረው ፍቀድልኝ ብሎ ጀመረ ። እኛ በራሳችን ለመትከል የምንታገለው ጽድቅ የሚገልጠው እኛን እንጂ እርሱን አይደለም ። ደግሞስ ቃሉ ጽቃችን እንደ መርገም ጨርቅ ይል የለ ።

የክርስትና ሕይወት ለውጥ የሚጀምረው ክርስቶስ ባንተ እንዲኖር ከመፍቀድ ነው።
“ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።”(ገላትያ 2፥20)

ክርስትና የምናወራው፣ የምንሰብከው፣ የምንዘምረው፣ የምንጸልየው ሕይወት ሳይሆን ክርስቶስ በኛ የሚኖረው የተገለጠ ሕይወት ነው ።

እውነቱ ብዙዎች ክርስትና አልገባቸውም ።ለዚህ ነው ከመጽሐፍ ቅዱስ ጌታ የፈጸመውን እና የጨረሰውን ሕግጋት እየለቀሙ የራሳቸውን ጽድቅ ለማቆም የሚታገሉበት ።ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው አስርቱን ሕግጋት ጭኜበችኃለሁና እነርሱን ይዛችሁ ጽድቃችሁን ፈልጉ አላለንም ። የሰው ልጅ በመውደቁ ሕግጋቱን መፈጸም አልቻለምና ።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለው እንለዋወጥ ነው። ይኸውም ባንተ ልኑር አንተም በኔ ኑር ፣ ራስህን ስጠኝ ራሴን ልስጥህ ፣ ኩነኔህን ወስጄ ጽድቄን ልስጥህ ፣ የዕዳ ጽሕፈትህን ወስጄ ነጻነቴን ልስጥህ ፣ ፍርድህን ልቀበል በነጻነት ኑር.. ወዘተርፈ የሚል ነው ።ብዙዎች ክርስትናን በራሳቸው ሊኖሩት ስለሚታገሉ ስልችት ድክም የሚያደርግ መራራ የእስር ቤት ሕይወት ያደርጉትና እየቆዩ ሲሄዱ ፍቅራቸው ይቀዘቅዛል፣ እምነታቸው ይዝላል፣ ግለታቸው ይቀዘቅዛል፣ ሩጫቸው ወደ ፊት መሆኑ ቀርቶ የኃልዮሽ ይሆንባቸዋል ከዚያም የእምነታቸው ሞተር ይጠፋባቸዋል።

እውነቱ ግን በእነርሱ ያለው ክርስቶስ በነርሱ መኖር ስለደከመው አይደለም ።
ይቁንም ያልሆነ መረዳት የያዙ እነርሱ ናቸው ።

ከዚህም የተነሳ ብዙ ክርስቲያኖች ዱሮ ጠንካራ አገልጋይ ነበርኩ፣ እጅግ የምተጋ ጸሎተኛ ነበርኩ፣ በልዩ ስጦታ የተካንኩ ዘማሪ ነበርኩ፣ ግሩም ሰባኪ ነበርኩ፣ ነበርኩ ! ነበርኩ ! ነበርኩ ! እያሉ የነበሩበትን እንጂ አሁን ያሉበትን የማያወሩ ልባቸው እምነታቸው ሕይወታቸው ይደበዝዝባቸዋል ።

ዛሬስ ሕይወት እንዴት ነው ስትሏቸው ነበርኩን ማውራት ይጀምራሉ ። ቋንቋቸው ሁሉ ነበርኩ.....ነበርኩ ነው።
ከኃጢያት ወደ ኃጢያት ፣ ከእርኩሰት ወደ እርኩሰት ፣ ከበደል ወደ በደል እየሄዱ የሚያወሩት የሚሰብኩት የሚያውጁት ፣ የሚያስተምሩት፣ የሚዘምሩት ሰው በሂደት መቀደስ እንደሚችል ሆኖ ሳለ እነርሱ ከድካም ወደ ድካም የሚገሰግሱት ይሆናሉ ።

በመሰረቱ ቅድስና ሦስት ደረጃዎች አሉት
1ኛ, እንዳመኑ በክርስቶስ ቅድስና መቀደስ ! ( ኤፌ2:-8-9)
2ኛ, ሰው ካመነ በኃላ በሒደት በሕይወቱ የሚጀምረዊ ሒደታዊ የቅድስና ሕይወት ! “... ትቀደሱም ዘንድ ፈልጉ፥ ያለ እርሱ ጌታን ሊያይ የሚችል የለምና።” (ዕብራ 12፥14)
3ኛ, አሁን ካለንበት ሥጋ ተለይተን ወደ ጌታ ሥንሔድ ! (1ጴጥ 1:-8-9)


እውነቱ ግን ክርስቶስ በኛ ሳለ በኛ እየኖረ ከክብር ወደ ክብር ፣ ከኃይል ወደ ኃይል ፣ ከከፍታ ወደ ከፍታ ፣ ከመገለጥ ወደ መገለጥ ፣ ከሞገስ ወደ ሞገስ ወዘተርፈ እንገሰግሳለን ።

“የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ።”( 2ኛ ጴጥ 1፥2-3 )

ችግሩ ቤተክርስቲያን ሰይጣን አብያተ ክርስቲያትያናትን " በኒቆላዊያን" ትምህርት፣በኤልዛቤል ትምህርት፣ በተለያየ የሐሰት ትምህርት መጥለቅለቋ ነው። ሁሉም ትምህርቱን መፈተሽ ይኖርበታል ። እኛ አዲስ የተባለን አስተምሮ እንድንሰበስብ አልተጠራንም ቅዱሱ ቃል :-

“ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥16

ዛሬ ዛሬ ላይ ስለ ደህንነት፣ ስለ እግዚአብሔር ጽድቅ፣ ስለ ኢየሱስ የማዳን ሥራ ፣ ስለኃጢያት፣ ስለሞት፣ ስለትንሳዔ፣ ስለ ዳግም ምጸዓት ፣ስለደሙ መስማት እያቆመው ።አሁን ላይ ትምህርቶች ሁሉ ስለቁሳዊ በረከት ፣ ስለሥጋ ፈውስ ፣ስለተዓምራትና ስለገንዘብ ችግር...ወዘተርፈ ሆነዋል ። እነዚህ እይታቸው በምድር ላይ የተተከለ፣ ልባቸው እየደነደነ ፣ እኔ ያልኩት ካልሆነ በማለት የጌታ አካል የሆነችውን ቤ/ክ ለመበታተን ቆርጠው የተነሱት።

ስለዚህ የቤተክርስቲያናችንን አስተምህሮ መጠበቅ፣ የሕዝቡን የአኗኗር ዘይቤ ፣ የአውነተኛ ክርስቲያኖችን አቋም፣ የሕይወትና የአገልግሎታችንን ጥራት በቃሉ ብረሃን በመፈተሽ ልንጠብቅ ይገባል።

@alexkhc
@alexkhc
133 viewsedited  03:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 20:49:24 ወደታሰበው ግብ ለመድረስ መሪም ሆነ ተመሪው ኃላፊነት አለበት !

ክፍል አንድ

በክርስቲያኑ ማህበረሰብም ውስጥ ሆነ በመደበኛው ዓለም ውስጥ ለስኬት ሆነ ለውድቀት ፣ለድል ሆነ ለሽንፈት፣ ለውጤታማነት ሆነ ለኪሳራ ...የመሪዎች ድርሻ ትልቁን ድርሻ መውሰዱ እሙን ነው ።

"በእስራኤል ውስጥ መሪዎች ስለ መሩ፥ ሕዝቡም ነፍሳቸውን በፈቃዳቸው ስለ ሰጡ፥ እግዚአብሔርን አመስግኑ።" (መሳፍንት 5:-2)

ይሁን እንጂ መሪ ውጤታማ የሚሆነው ሕዝቡ መሪው ወደሚያሳየው ግብ ለመድረስ አመራሩን ተቀብሎ በተሰጠ ሁለንተና መረባረብ ሲችል ብቻ ነው ።

" ልቤ ወደ እስራኤል አለቆች ነው፥ በሕዝቡ መካከል ነፍሳቸውን በፈቃዳቸው ወደ ሰጡት፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ።(መሳፍንት 5:-9)

መሪ ሲነሳ ሕዝብም አብሮ መነሳት፣ መሪ ሲመራ ሕዝብም ለመመራት መፍቀድ ፣ መሪ ሲናገር ሕዝብ መስማት፣ መሪ ሲሰራ ሕዝብም አብሮ መስራት አለበት ።

በአንድነት በጋራ በተሰጠ ሁለንተና በመቀባበል በመረዳዳት በመመካከር በእግዚአብሔር ወደ ታየልንን ግብ መገስገስ ይገባናል ።

ከላይ በተመለከትነው የመጽሐፍ ቅዱስ መሪ በትክክል መምራት ሕዝብም ነፍሱን በፈቃዱ ሲሰጥ ለታላቅ ድልና ውጤት እንበቃለን ።

በሁሉ አንጻር ማመካኘት ማሳበብ መካሰስን መነካከስን ትተን ለጣፋጭና ያማረ ድል፣ ለዕድገት ፣ ስኬትና መከናወን ለመጎናጸፍ በአንድነት በፍቅር በመቀባበል በመተጋገዝ በጋራ እንነሳ ።

ተባርካችኃል !

......ይቀጥላል !
110 views17:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-23 18:55:22 ውድ የአባቴ ቅዱሳን እንኳን ለትንሳኤው መታሰቢያ ቀን ፋሲካ በሰላም አደረሳችሁ !

"ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ? ተነስቷል እንጂ በዚህ የለም ።"(ሉቃስ 24 :5)

የክርስትና እምነት ከሌሎች እምነቶች ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር ትንሳኤው ነው ፥የብዙ ሃይማኖቶች መሥራች እና መሪዎች ከመቃብር በታች ሲሆኑ ፥ የክርስትና እምነት ጀማሪው እና ፈጻሚው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሞትን ድል ነስቶ በክብር በአብ ቀኝ በክብር ተቀምጧል ያመኑበትንም ባዘጋጀውም የክብር ሥፍራ ሊያኖራቸው እንደገና ተመልሶ ልጆቹን ለመውሰድ የሚመጣ አልፋና ኦሜጋ የሆነ ጌታ መሆኑ ነው ።

እግዚአብሔር ሆኖ ሳለ የአምላክነቱን ክብር መቀማት እንደተገባው ሳይቆጥር ከሰማየ ሰማያት ቃል ሆኖ ወርዶ ስለ ሰው ሰው ሆኖ ተወልዶ መለኮት ሆኖ ሳለ ሰው ሆኖ በአካል በመገለጥ :- ኃጢያታችንን ወስዶ ቅድስናውን ሊሰጠን ፣የኃጢያት ኩነኔያችንን ወስዶ ጽድቁን ሊሰጠን ፣ የሞት ቅጣታችንን ወስዶ የዘላለም ሕይወትን ሊሰጠን ፣በደሙ አጥቦ፣ በጽድቁ አሳምሮ ፣ ሂሊናን ከሞተ ሥራ አንጽቶ የክብሩ ማደርያ መቅደሱ ሊያደርገን ፣ ሞታችንን በሞቱ ሽሮ ሕያውያን ሊያደርገን ስለ አኛ በመስቀል ላይ ተንጠልጥሎ የሞትን ጽዋ ተጎነጨ።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚል ሞተ ተቀበረ በሶስተኛው ቀን ከሙታን ተነሳ በሰው እና በእግዚአብሔር መከካል የነበረውን የኃጢያት ግርግዳ አፈረሰው ፣የኃጢያት ዕዳችንን ከፈለ፣በኛና በእግዚአብሔር መከካል የነበረውን የኃጢያት መጋሪጃ ከላይ እስከ ታች ቀደደው :: ክብር በዓርያም ላለ ለሠራዊት ጌታ ለእግዚአብሔር ይሁን ! አሜን !

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ከአብ ጋር ፣ ሰው ከራሱ ጋር ፣ሰው ከሰው ጋር የሚያስታርቅ መካከለለኛ የሆነ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ሆኖ የተገለጠ በመሆኑም ያለንበት ወቅት የታላቅ እርቅ ሥራ በመስቀል ላይ የተከናወነበት የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት እና ትንሳኤ መታሰቢያ በዓል ላይ ነን ::

ኢየሱስ በመሞቱ በመቀበሩና ከሙታን በመነሳቱ !
በሞት ላይይ ሥልጣን የነበረውን ዲያቢሎስ ድል ነስቷል ሽሮታልም !
(ዕብራ 2:-
ሞታችንን በሞቱ ሽሮ ሞታችንን ድል ነስቶ መውጊያውን ሰብሮታል !
ኃጢያትን ድል ነስቶ ኃይል አልባ አድርጎታል !
ሲኦል ድል ነስቶ ገነትን ለሚያምኑበት በደሙ ክፍት አድርጓል !
የዕዳ ጽህፈታችንን ደምስሶ ነጻ አውጥቶናል !

በአብና በሰው ልጅ መሐከል የማይሻር አዲስ ኪዳን ቆሞዋል ማንም ሊሽረው ሊለውጠው አይችልም ። ይህም የሰው ልጅ በወንጌሉ የምስራች በመስቀሉ ላይ ለሰው ልጆች ሁሉ ድህነት በኢየሱስ ክርስቶስ ተሰርቶ ባለቀለት የማዳን ሥራ አምኖ ይድን ዘንድ ነው ::

ኢየሱስ ከመቃብር በመነሳቱ ምክንያት ክርስትና የአሸናፊነት እምነት ነው ።
ምናልባት ሁኔታዎችን እያያችሁ ግራ የተጋባችሁ ፥ በሃዘን የምትቆዝሙ ፥ በህመምና በሥቃይ የምትንገላቱ ወንድሞቼና እህቶቼ ዛሬ ለእናንተ የምስራች አለኝ ። ኢየሱስ ከሙታን በመነሳቱ የዘለዓለም ሞታችሁ (ከእግዚአብሔር ተለይታችሁ መኖራችሁ) ተሽሮአል። ዛሬም ለነገራችሁ ሁሉ ትንሳኤን ይሰጣል ። ተስፋ እንደሌላቸው አልተዋችሁም ብሎ ላይተወን ተስፋን የሰጠን ጌታ ዛሬም ሕያው ነው ። ዛሬም የትንሳኤውን ጌታ በሁሉም ነገር ላይ በምስጋና ሆናችሁ ጥሩት ይደርሳል ጣልቃ ይገባል ታሪክን ይቀይራል የማይገመተውን የማይመረመረውን ድንቅ ታዓምራት ያደርጋል። አምላካችን የትንሳኤ አምላክ ነው ።

ሌላው ከፊታችሁ የሚጠብቃችሁን ዘላለማዊ ክብር እያያችሁ ብድራታችሁን ትኩር ብለን በመመልከት በምድር ላይ የገጠማችሁን መከራ እንደምንም ቁጠሩት። በመጨረሻ እንዲህ ልበላችሁ የትንሳኤው ዘር ፥ የማይጠፋው ዘር በውስጣችሁ ስላለ ምንም ነገር ቢገጥማችሁ ተስፋ አትቁረጡ ። እግዚአብሔር ሁል ጊዜ በመንፈሱ ከሁላችንም ጋር ነው ።
ተባረኩልኝ !

አገልጋያችሁ አሌክስ ነኝ !!!

መልካም ፍሲካ !
122 views15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 13:31:45
124 views10:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 11:14:54
77 views08:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-20 08:03:02 "ሻሎም"Shalom (שלום)

Shalom ሻሎም ብዙዎች ይህንን ቃል ለሰላምታ ይጠቀሙታል ። በመሆኑም ይህ ቃል ለአብዛኞቻችን እንግዳ አይደለም። ብዙ ጊዜ እንሰማዋለን ጥያቄው ግን ተናጋሪውም ሆነ ተቀባዩ የሚጠቀመው የቃሉ ፍቺ ገብቶት ወይስ ሳይገባው የሚለው ነው። Shalom ሻሎም ማለትስ ምን ማለት ነው ?

Shalom (שלום) የእግዚአብሔር ሰላም
የሻሎም ትርጉም "ሰላም ወይም የጦርነት አለመኖር" ብለን እንል ይሆናል ነገር ግን የቃሉ ትርጉም ከዚህም እጅግ የላቀ ነው።

Shalom የሚለው ቃል በብዙ ቋንቋ ተናጋሪዎች ዘንድ በሥራ ላይ ይውላል ። በትርጉም እና በቃላት እጅግ የበለጸገ ቃል ነው ። ከዚህ የተነሳ በተለያዩ አውዶች ውስጥ የተለያየ ትርጉም አለው ጥቅምም ላይ ውሏል፡፡በሰላምታ፣ በመልካም ምኞት መግለጫ፣ በባርኮትና አልፎም በተለያዩ የውጭ ፊልሞች ወይም ዘፈኖች ውስጥ ብዙውን ጊዜ “ሻሎም”ን ማግኘት የተለመደ ነው ፡፡

ሻሎም የሚለው ቃል መሰረቱ S - L - M (ሰ-ላ-ም) (shin-lamed-mem ፣ ש.ל.ם) ነው ፡፡ የቃሉ መሠረት በብዙ ሴማዊ ቋንቋዎች የሚገኝ ሲሆን የጤና እና ሙላት ትርጉም አለው ፡፡ በአይሁድ ማህበረሰብ ውስጥ ይህ ሰላምታ በየትኛውም የዓለም ክፍል ውስጥ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን የግል ግኑኝነት፣ ትውውቅ፣ ስብሰባዎች፣ ውይይቶች ሁል ጊዜም በእሱ ይጀምራል፡፡
በዚህ መንገድ ሰላምታ ለመስጠት ፣ አይሁዶች ሁል ጊዜ አንዳቸው ለሌላው ሰላምን ፣ ብልጽግናን እና መልካም ምኞት ይመኛሉ፡፡

ሻሎም በአንድ ወቅት ከዕብራይስጥ ቋንቋ የመጣ ጥንታዊ ቃል ነው ፡፡ የእስራኤል ነዋሪዎች እርስ በእርስ ሲገናኙ ሁል ጊዜ ‹ሻሎም› ከሚለው ቃል የተፈጠረ ሐረግ ይናገራሉ፡፡ ለምሳሌ ለአንድ ወንድ ንግግር ሲያደርጉ “ማ ሽሎምሃ?” ብለው ይጠይቃሉ ፣ ሴትንም ሲጠይቁ “ማ ሽሎሜህ?” ይላሉ ፡፡ ስለዚህ እርስ በርሳቸው “እንዴት ነሽ? እንደምን ነህ?" በማለት ደህንነታቸውን የሚጠያየቁበት ነው ።

ሻሎም ማለት ሰላም ፣ ደህንነት እና በአይሁዶች መካከል የሰላምታ ወይም የስንብት ዓይነት ነው ፡፡ ቃሉ ሻሎም መነሻው ከዕብራይስጥ ቋንቋ ፣ שלום እና ለ ጤና ፣ ስምምነት ፣ ውስጣዊ ሰላም ፣ መረጋጋት እና መረጋጋት ለአንዱ ወይም ሰላምታው ለተነገረለት ፡፡ ቃላቱ
በዕብራይስጥ ቃላት ከተነገረ ቃል በላይ ናቸው ነገር ግን ስሜትን ፣ ዓላማን እና ስሜትን ያጠቃልላሉ ፡፡ ለዚያም ነው ቃሉ በበርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ የሚገኝ ሲሆን ሻሎም ማለትም ሰላም ማለት በሰዎች መካከል ደህንነት የመፈለግ ፍላጎት ፣ አሕዛብን ወይም በእግዚአብሔር እና በሰው መካከል የሚኖረውን ሰላምም ገላጭ ተደርጎአል።

ሻሎም አለይኩም፣ ብዙ ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚጠቀመው ሰላምታ ሲሆን ትርጉሙም “ሰላም ለእናንተ ይሁን” ማለት ነው ፡፡ የአረብኛ ስሪት የሻሎም ነው ሰላም እና በእስራኤል ውስጥ እንኳን በመደበኛነት ጥቅም ላይ ይውላል ፡፡

ሻሎም የተሰኘው የዕብራይስጡ ቃል መሰረታዊ ትርጉም በሁሉም የሕይወት መስክ የስምምነትን፣ የምሉእነትን፣ የስምረትን፣ የደህንነትንና የስኬትን መኖር ያመለክታል።ይህ ሙሉ የሆነ ሰላም ደግሞ በዕብራይስጥ " ሻሎም "ተብሎ ተጠርቷል። በመሆኑም ይህ ሻሎም የተባለ ቃል፤

1ኛ.ቤተሰባዊ(አገልግሎታዊ) ሰላም ደስታ እና ከመለኮት የሚሰጠውን ያመለክታል ።ለአሮንና ለልጆቹ ንገራቸው። የእስራኤልን ልጆች ስትባርኩአቸው እንዲህ በሉአቸው።
እግዚአብሔር ይባርክህ፥ ይጠብቅህም፤
እግዚአብሔር ፊቱን ያብራልህ፥ ይራራልህም፤እግዚአብሔር ፊቱን ወደ አንተ ያንሣ፥ ሰላምንም ይስጥህ።( ዘኍልቍ 6:23-26)

2ኛ.በነፍሳችን ውስጥ የተገለጠ ውስጣዊ ሰላም እርካታና መረጋጋት
"በልቤ ደስታን ጨመርህ፤ ከስንዴ ፍሬና ከወይን ከዘይትም ይልቅ በዛ።በሰላም እተኛለሁ አንቀላፋለሁም፤ አቤቱ፥ አንተ ብቻህን በእምነት አሳድረኸኛልና።" (መዝሙረ ዳዊት 4:7-8)

3ኛ.በማይመች ሁኔታ እያለን ያለንን ውስጣዊ ሰላም መረጋጋት ደስታ በያህዌ ከመለኮት የሚገልጠውን ወይም የሚሰጠንን ሰላም እና ተስፋን ያመለክታል ።

4ኛ.ምንም አይነት ችግር ሌለበት ሕዝብ በሰላም በብልፅግና ውስጥ የሚታየውን መረጋጋት እና ሰላም ያሳያል።ሰላም ለዓለም ሁሉ ይሁን ለሰው ልጆችም ሁሉ በጎ ፈቃድን መመኘት ነው።
207 viewsedited  05:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 01:25:36 ለወንጌል መስፋት የአብያተ ክርስትያናት መደጋገፍ ያለውን አስፈላጊነት የገልጻል ።

ጥናት ሰላሳ :-

1 ቆሮንቶስ ምዕራፍ 16 ለወንጌል መስፋት የአብያተ ክርስትያናት መደጋገፍ

#ዓላማ ፦ ለወንጌል መስፋፋት የአብያተ ክርስትያናት መደጋግፍ እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ ማስገንዘብ 

መግቢያ 1ቆሮ 16 እንደምናውቀው የመጨረሻ ምዕራፍ ሲሆን በጥቅሉ ሶስት ነገሮችን ያስተምራል። እነዚህም ሶስቱ ዋና ነገሮች፦ ለወንጌል ሥራ ስለ አብያተ ክርስትያናት በገንዘብ መደጋገፍ (1ቆሮ 16፡1-4) ፣ የሐዋርያውን እቅድ ማስተዋወቅ (1ቆሮ 16፡5-18) እና የመሰናበቻ መልዕክት ናቸው (1ቆሮ 16፡ 19-24)።

የክፍሉ አጭር ማብራሪያ

1. የአብያተ ክርስቲያናት መደጋገፍ፦ 1ቆሮ 16:1-4 እንደሚያስረዳን ሐዋርያው ጳውሎስ በአካይያ አውራጃ ላለች ለቆሮንቶስ ቤ/ክ የገላትያና የመቄዶንያ አብያተ ክርስቲያናት ሌሎችን እንደሚረዱ እነዚህም ለኢየሩሳሌም አማኞች ገንዘብ አሰባስበው እንዲልኩ ይጠይቃቸዋል። ይህ እርዳታ ያስፈለገው እንደሚታወቀው በኢየሩሳሌም የነበሩ አማኞች ራሳቸውን ከአይሁድ ኃይማኖት ከለዩ በኋላ ብዙ ስደት እና ችግር ደርሶባቸዋል (ሐዋ 8:1)። ስለዚህ አብያተ ክርስቲያናት መደጋገፍ እንዳለባቸው ያሳስባቸዋል። አብያተ ክርስቲያናት ይረዳዱ እንደነበሩም መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይነግረናል “ከእነርሱም አጋቦስ የሚሉት አንድ ሰው ተነሥቶ በዓለም ሁሉ ታላቅ ራብ ሊሆን እንዳለው በመንፈስ አመለከተ፤ ይህም በቀላውዴዎስ ቄሣር ዘመን ሆነ። ደቀ መዛሙርትም እያንዳንዳቸው እንደ ችሎታቸው መጠን አዋጥተው በይሁዳ ለሚኖሩት ወንድሞች እርዳታን ይልኩ ዘንድ ወሰኑ፤” (ሐዋ 11:28-29)። ይህንንም የሚያዘው እንደየሰው የገቢ መጠን እንዲሆንና እሁድ እንዲሰበስብ ነው (16:2)።

2. የሐዋርያው የአገልግሎት እቅድና ተቀባብሎና ተያይዞ የጌታን መንግስት ማስፋፋት (16:5-18)፦ ሐዋርያው ኑሮው እና ህይወቱን በሙሉ ለእግዚአብሔርና የእርሱን ሥራ ለመሥራት አስረክቧል። በመለኮታዊ ሥራው እርሱ አብሮት የሚሰራ ቢሆንም የሌሎችን አብሮ መሥራት እጅግ ጠቃሚ መሆኑን አይክድም። ለዚህ ደግሞ ቁ.6 ላይ ለጉዞው እንዲረዱት በግልጽ ይጠይቃል (2 ቆሮ 6:1)። ኢየሱስ ክርስቶስንም ሴቶች በገነዘባቸው ያገለግሉት ነበር “አሥራ ሁለቱም ከእርሱ ጋር ነበሩ፥ ከክፉዎች መናፍስትና ከደዌም ተፈውሰው የነበሩ አንዳንድ ሴቶች፤ እነርሱም ሰባት አጋንንት የወጡላት መግደላዊት የምትባል ማርያም፥ የሄሮድስ አዛዥ የኩዛ ሚስት ዮሐናም ሶስናም ብዙዎች ሌሎችም ሆነው በገንዘባቸው ያገለግሉት ነበር” ( ሉቃስ 8:2-3)። ወንጌል አብሮ የሚሰራ አገልግሎት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ይነግረናል። ከዚህም ጋር አያይዞ ታላቅ የወንጌል በር እንደተከፈተ እና ተቃዋሚዎችም እንዳሉበት ይገልጻል (16:9)።

16፡13 ላይ ብዙ ዓይነት የተሳሳቱ ትምህርቶችና የሥነ ምግባር ጉድለቶች ቢኖሩም ጠንክረው እንዲቆሙ ይጠይቃቸዋል። ቁ. 14. በስህተት ትምህርት ባይበከሉም ከሁሉ በፊት በፍቅር መኖር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነ መልዕክት ያስተላልፋል። የአንደኛ ቆሮንቶስ መልዕክት ከምዕራፍ አንድ ጀምሮ እስከ ምዕራፍ አሥራ ስድስት የሚመራው ቁልፍ ቃል “ፍቅር” ነው። ለምሳሌ እንዲሆን ለዚህ መስዋዕትነት ለተሞላ አገልግሎት አብረውት ከሚሰሩት ከጠቀሳቸው ቤተ ሰብ አንዱ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰብ ነው (16:10)።

3. ሰላምታና ስንብት (1 ቆሮ 16:19-24)፦ ይህ ክፍል የሚናገረው የሌሎችን አብያተ ክርስቲያናት የልባቸውን ትስስር በሰላምታ ያቀርባል። በተለይም የቤት ለቤት ቤተ ክርስቲያን ብሎ በጊዜው የነበረውን መሰብሰቢያ ቦታ ይናገራል።

የመወያያ ጥያቄዎች
1. 1ቆሮ 16:1-4 ዋና መልክት ምንድ ነው? ምን ያስተምረናል?

2. ሐዋርያው ጳውሎስ ለወንጌል አገልግሎት “ሌሎች የሚሰጡ ብሎ ምሳሌ የሚጠቀመው የየት ሀገሮችን አማኞችን ነው? የስጦታው ዓላማ ምንድ ነው?

3. ከ1ቆሮ 16:6 ከሉቃስ 8:2-3 ምን እንማራለን?

4. 1ቆሮ.16:5-7 ዋና መልዕክት ምንድ ነው?

5. በሐዋርያው አገልግሎት አብረውት ከሚሰሩት ቤተ ሰብ አንዱ የእስጢፋኖስ ቤተ ሰብ ነው (16:10-18)። ክፍሉን አንብባችሁ ተወያዩ። ከእነዚህ አማኞች ህይወት እና አገልግሎት ምን እንማራለን?

6. 1ቆሮ 16:18 ላይ “እንደነዚህ ያሉት መታወቅ አለባቸው” የሚለው እነ ማንን ነው? ለምን?

7. ከዛሬው ጥናት በልባችን የቀረውን መልዕክት እናካፍል?

8. ዛሬም እንደዚህ የተሰጡ ወገኖችን ጌታ እንዲያስነሳ እንጸልያለን።

9. በመጨረሻም ከዚህ ጥናት የተጠቀማችሁት ነገር ካለ በመሪዎቻችሁ በኩል አሳውቃችሁ በቤ/ክናችን ባሉት ፕሮግራሞች መመስከር ትችላላችሁ።

መደምደሚያ
ይህ ምዕራፍ የጌታ መንግስት አብሮ በፍቅር እና በመረዳዳት የሚሰራ እንደሆነ ያስተምራል። እግዚአብሔር አብሮን የሚሰራ ቢሆንም እኛም አብረን ወይም የአንዱ ሀገር አብያተ ክርስቲያናት ከሌሎች አብያተክርስቲያናት ጋር አብረው እንዲሰሩ ጌታ የፍቅር ኃላፊነት ሰጥቶናል።

ቅዱሳን ሆይ ተባርካችኃል ውሎአችሁ የሰላም የጤና የበረከት የስኬት የመከናወን ይሁን።ቤታችሁ፣ ኑራአችሁ እና አገልግሎታችሁ ሁሉ የተባረከ ይሁን!! ተፈፀመ !
83 views22:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 01:18:16 የትንሣኤ አካል

ጥናት ሃያ ዘጠኝ
1ቆሮ 15:35-58

ዓላማ፦በክርስቶስ ያመነ ሰው አማኝ የትንሳኤ አካል እንዳለ በእምነት መቀበል እና ለሌሎችም የትንሳኤን አካል እውነት መመስከር እንዳለበት ማስገንዘብ  መግቢያ፦ የሰው ልጅ በምድራዊ እውቀቱ ስለ ብዙ ነገሮች ወይም ፍጥረታት ተንትኖ ማወቅ እንደማይችል ሁሉ የትንሳኤ አካልም በምድራዊ እውቀቱ ሊያብራራ እንደማይችል በማወቅ የአማኝ የትንሣኤ አካል በእምነት በእግዚአብሔር ችሎታ ሊሆን እንደሚችል በማመን መቀበል እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ነው። ሙታን የሚነሱ ከሆነ በምንስ ዓይነት አካል ይመጣሉ? የሚል ጥያቄ በወቅቱ ከነበሩት አሳሳች ወይም የሥጋ እውቀት ጥያቄዎች አንዱ ነበር። የትንሣኤን አካል በተመለከተ፣ የሚነሣው ጥያቄ በአንዳንድ የግሪክ ፍልስፍና ትምህርት ቤቶች በነበረ በሥጋዊ አካል ላይ ካለ አሉታዊ አተያይ የተነሳ ጥያቄ ነው። አንዳንድ ግሪኮች ዘወትር ቁስ-አካልን (ለምሳሌ ሥጋን) እንደ ክፉ ይመለከቱ ነበር። ሥጋ የንጹህ ነፍስ እስር ቤት ነው ብለውም ይናገራሉ። ሐዋርያው ጳውሎስ ለእንደዚህ ዓይነት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል (15፡35-57)። ይህንንም መቀበል የምንችለው በመንፈሳዊ እውቀት ነው ይላል። ስለዚህ በዚህ ክፍል ሐዋርያው ስለ ትንሳኤ አካል ባህርይ ሲያስረዳ የትንሳኤን አካል ከተክሎች (36-38)፣ከሥጋ ለባሽ ከሆኑ ፍጡራንና (ቁ.39) ከሰማያዊና ምድራዊ አካላት ጋር ያነጻጽራል (40-41)።

የመወያያ ጥያቄዎች
1. 1ቆሮ 15:35-45 “ሙታን እንዴት ይነሣሉ” የሚሉ ሰዎች ዋናው ችግራቸው ምንድ ነው?
2. የትንሳኤ ሙታንን እውነት ለማስረዳት ሐዋርያው ጳውሎስ የተጠቀማቸው ምሳሌዎች ምን ምንድ ናቸው? ምንስ ያስተምራሉ?
3. 1ቆሮ 15:42-50 በማንበብ በዚህ ክፍል ጸኃፊው የአዳምና የክርስቶስን ምሳሌን ማነጻጻሩ ለምን አስፈለገ?
4. 1ቆሮ 15:42-50 መሠርት ሐዋ ጳውሎስ ስለ ትንሳኤ አካል ለማስተማር የተጠቀማቸው ተቃራኒ ነገሮችን ተወያዩ። እነዚህ ተቃራኒ ነገሮች መጠቀሳቸው ለምን ያስፈልጋል?
5. በ1ቆሮ 15፡51-57 ባለው ከፍል የጌታ ቃል እንደሚነግረን ትንሳኤ መቼ እና እንዴት እንደሚሆን ተወያዩ?
6. በ1ቆሮ 15:35-58 የዚህ ክፍል ጥናት ዋና መልእክት ምንድ ነው? ተወያዪ
7. በ1ቆሮ 15:58 ያለውን ምክር ተወያዩ አሁን ለእኛ ምን ይጠቅማል?
8. በአጠቃላይ ከዚህ ጥናት ምን ተረዳችሁ። ለቡድኑ አካፍሉ።

መደምደሚያ
የትንሣኤው አካል አዲስ ዓይነት አካል ነው። በሚጠፋ ምትክ የማይጠፋ፣ በተዋረደ ምትክ የከበረ፣ ከደካማ ይልቅ የበረታ፣ ከሥጋዊ ይልቅ መንፈሳዊ እንደሚሆን በዚህ ክፍል ተገልጿል። ስለዚህ ትንሳኤ ሙታን የአማኞች በአካል የሚሆን እውነት ነው።

ቅዱሳን ሆይ ተባርካችኃል ውሎአችሁ የሰላም የጤና የበረከት የስኬት የመከናወን ይሁን ። አሜን !
69 views22:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ