Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2022-09-25 21:14:43 * ቅዱሱ አምላክ ያልተቀደሰ መስዋዕት
አይቀበልም *

እግዚአብሔ ቅዱስ ነው ! ሕዝቡም ቅዱስ ነው ! የተቀደሰ ምስዋዕት ይፈልጋል ! እግዚአብሔር በስብከት በዝማሬ በልሳን በሙዚቃ በመሳርያ ጋጋታ በጉባኤ ብዛት አይሸወድም :: የምናደርገው ምንም ነገር ከቅድስና ውጪ በርሱ ዘንድ ተቀባይነት የለውም ! ከዚህ የተነሳ እርሱ እንዲሆን ያዘዘውን ለዕርሱ የሚደረገውን :-
1,ዝማሬ ተቃወመ :- የዘማሪዎች ዝማሬ በእግዚአብሔር ፊት መቅረብ ያለበት ህይወታቸውን ለእግዚአብሔር በቀደሱ መዘምራን ነው ! ካልሆነ ግን :-
"የዝማሬህንም ጩኸት ከእኔ ዘንድ አርቅ፤ የመሰንቆህንም ዜማ አላደምጥም። " ነው የሚለው ።(ትንቢተ አሞጽ 5:23)

" እንደ ሙቀት በደረቅ ስፍራ የኀጥአንን ጩኸት ዝም ታሰኛለህ፤ ሙቀትም በደመና ጥላ እንዲበርድ እንዲሁ የጨካኞች ዝማሬ ይዋረዳል። "(ት. ኢሳይያስ 25:5) አየህ ለርሱ ተቀድሰህ የምታቀርበው መሰዋዕት እንጂ የሕዝቡ መጨፈር እግዚአብሔር መመለኩን አያረጋግጥም።
" ዓመት በዓላችሁንም ወደ ልቅሶ፥ ዝማሬአችሁንም ወደ ዋይታ እለውጣለሁ፤ ማቅንም በወገብ ሁሉ፥ ራስ መንጨትንም በሁሉ ላይ አመጣለሁ፤ እንደ አንድያ ልጅም ልቅሶ፥ ፍጻሜውንም እንደ መራራ ቀን አደርገዋለሁ።"(ትንቢተ አሞጽ 8:10)

2, የእግዚአብሔር ጉባኤ የተቀደሰ ጉባኤ ነው ! በፊቱ ያልተቀደሰውን ጉባኤ እግዚአብሔር ተቃወመ :-
" ምናምንቴውን ቍርባን ጨምራችሁ አታምጡ፤ ዕጣን በእኔ ዘንድ አጸያፊ ነው፤ መባቻችሁንና ሰንበታችሁን በጉባኤ መሰብሰባችሁን አልወድድም፤ በደልንም የተቀደሰውንም ጉባኤ አልታገሥም።"(ት. ኢሳይያስ 1:13) የሕዝብ በብዛት መሰብሰብ የእግዚአብሔርን መገኘት አያረጋግጥም ።
*እግዚአብሔር በኤርሚያስ አታላይ ጉባኤን ተቃወመ :-
" ሁሉም አመንዝሮች፥ የአታላዮች ጉባኤ ናቸውና ሕዝቤን እተዋቸው ዘንድ ከእነርሱም እለይ ዘንድ በምድረ በዳ የመንገደኞች ማደሪያን ማን በሰጠኝ? "(ት. ኤርምያስ 9:2)

* እግዚአብሔር ዋዘኛ ጉባኤን ተቃወመ :- የመድረክ ላይ ማሳቅ በቀልድ ሕዝቡን ማስፈንደቅ እንደ ኮሚዲ ሕዝብን ማዝናናት የእግዚአብሔር አጀንዳ እንዳይመስልህ ።
" በዋዘኞችና በደስተኞች ጉባኤ አልተቀመጥሁም፤ ቍጣን ሞልተህብኛልና በእጅህ ፊት ለብቻዬ ተቀመጥሁ። "(ት. ኤርምያስ 15:17)

*ጌታ ይሙት ይሰቀል እያለ ከአመፀኞች ጋር ያውጅ የነበረ የክፉዎች ጉባኤ ነው ! በኖሕ ዘመን አልሰማ ብሎ በጥፋት ውሃ የተሰናበተው ብዙ ሕዝብ ነው ። " ብዙ ውሾች ከብበውኛልና፤ የክፋተኞች ጉባኤም ያዘኝ፤ እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ።"(መዝ 22:16)

ማስተዋል አለብን በቃሉ እውነት እና መሠረት ላይ ልንቆም ይገባል ። የዝንጉዎች ጉባኤ ለጥፋት ይሆናል አለ !
ይህ እንዳለ ሁሉ የቅኖች ጉባኤ አለ ! የቅዱሳን ጉባኤ አለ ! የእነርሱ አምልኮ በእግዚአብሔር ፊት ደስ የሚያሰኘው
ቅዱስ መሰዋዕት ነው ።በመ ሆኑም በእውነት ከሚያመልኩት እውነተኛ ቅዱሳን ጉባኤ እድል ፈንታ ያድርገን ።

1ኛ,እግዚአብሔር ቅዱስ ነው ። ሕዝቡም እንደ አምላኩ ሊቀደስ ይገባል ። (1ጴጥ 1:-14-15)

2ኛ,ለእግዚአብሔር የሚቀበለው መሰዋዕት ምስጋና አምልኮ ውዳሴ ከተቀደሰ ሁለንተና የሚወጣ መሆን አለበት ። (1ተሰ 5:-23)

3ኛ, የአምልኮ ዝማሬ ጋጋታ ፣ የተዓምራት ጋጋታ ፣ የስብከት ጋጋታ ፣ በኛ ኑሮ ሕይወት እና አገልግሎት ተገልጦ በፍሬው ከልታየ ከክህደት ተለይቶ አይታይም ።(ቲቶ 1:-16)

4ኛ, የአምልኮ፣ ዝማሬ ፣ የስብከት ፣ በኛ ኑሮ ሕይወትና አገልግሎት ተገልጦ ጌታን ካላስከበረ የአምልኮ መልክ መያዝ እንጂ የአምልኮ ሕይወት ሊባል አይችልም ።
“የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ።”(2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥5)

ስለዚህ ሕያው ቅዱስ መሰዋዕት ሆኖ ከተሰጠና ከተቀደሰ ሁለንተና በሚወጣ እውነተኛ የተሰበረ መንፈስ ጌታን ልናመልከው እና ልናገለግለው ይገባል ።( ሮሜ 12:-1-2)ጌታ ይባርካችሁ !
7 views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 06:31:31 ጆሮ ያለው ይስማ !

" መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ። "( ራእይ 2:11)

ለፈቃዱ ለስሜቱ ለምኞቱ ለተድላው ለስኬቱ ...ወዘተርፈ እንጂ መንፈስ ቅዱስ ለሚናገረው እውነት ብዙዎች ጆኖ የላቸውም ።
ያለንበት ዘመን የሕይወት ምሪት የኑሮ ጥራት የአገልግሎት መከናወን መመስረት ያለበት መንፈስ ቅዱስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን በመስማት ላይ መሆን ይኖርበታል ።
ይህ መልዕክት ለሁሉም አብያተ ክርስቲያናት የተነገረ ተደጋጋሚና ወሳኝ የሆነ አንድ አይነት መልዕክት ነው ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ ።

መችም ጠላት ሰዎች የእግዚአብሔን እውነት ፈቃዱን የማዳን እቅዱን እንዳያስተውሉ የልቡናቸውን አይኖች አሳውሮአል ። " ለእነርሱም የእግዚአብሔር ምሳሌ የሆነ የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን እንዳያበራላቸው፥ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን አሳብ አሳወረ።"
(2ኛ ቆሮንቶስ 4:4) እውነቱ ብዙዎች ያስመስላሉ እንጂ አይሰሙም ። መንፈስ ቅዱስ በቃሉ ከሚናገራቸው እውቀት የራቁ ናቸው። የሚገርመው ደግሞ የመለኮትን እቅድ በሰው ሀሳብ ለመከወን መነሳታቸው ነው ።

ብዙዎች ጆሮ ላይ የሚያስተጋባው ድምጽ የሰይጣን ፣ የዓለም ፣ የሥጋ ምኞት ...ድምጽ ነው ። ጌታ ደግሞ ደጋግሞ ለሁሉም አብያተክርስቲያናት ማንን መስማት እንዳለባቸው በግልጽ አስቀምጧል። ጆሮ ያለው ይስማ ብሎ ተናግሯል ። ብዙዎች ብዙ ነገር ለመስማት ጆሮ አላቸው ። የህይወታቸውን ፍጻሜ ለሚወስነው የመንፈስ ቅዱስ እውነት (ህያው ቃል) ግን ጆሮ የላቸውም ። አይገርምም ???

ቤተ ክርስቲያን ወደ ታቀደላት ግብ የምትደርሰው መንፈስ ቅዱስ በቃሉ የሚላትን ስትሰማ ብቻ ነው ! ያኔ ነው ምሪትን ድልን ቅድስናን ፅናትና ኃይልን ተጎናፅፋ ለአምላኳ ፈቃድ እስከሞት ታምና በፅናት መቆም የምትችለው ! እስቲ አስተውሉ ልንሰማቸው ጆሮዎቻችንን የከፈትንላቸው ፣ ሥፍራን የሰጠናቸው በሕይወታችን ያመጡት ለውጥ ወይም በጎ ተፅኖ ምንድ ነው ? ክፋታቸውን ተንኮላቸውን አመጻቸውን እንጂ አንግዲህ መንፈስ ቅዱስ በቃሉ እውነት የሚገልጠውን ምሪት ጆሮአችን ተከፍቶ ልንሰማ ልንኖርበትና ልንገልጠው ይገባል ። የቤተክርስቲያንና የተልዕኮውን ባለቤት መስራቹ ኢየሱስን ክርስቶስን ከመስማት ሌላ ምን አማራጭ አለ ?
“ደመናም መጥቶ ጋረዳቸው፥ ከደመናውም፦ የምወደው ልጄ ይህ ነው፥ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።”
— ማርቆስ 9፥7

መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ ያለን በእግዚአብሔር አብ የተወደደ ፣ አብ የተደሰተበት፣ እንድንሰማው የታዘዝነው ጌታ ኢየሱስ የነገረን እውነት ነው።
ማንኛውንም የመለኮት ፈቃድ ለመገናኘት ለፍሬያማነትና ለስኬት ለመከናወን እርሱን መስማት ይገባል :: ቃሉ የሰሙቱ ሕይወትን ሲጎናጸፉ በአንጻሩ ያልሰሙቱ " ከደቀ መዛሙርቱም ብዙዎች በሰሙ ጊዜ። ይህ የሚያስጨንቅ ንግግር ነው፤ ማን ሊሰማው ይችላል? አሉ።"(ዮሐንስ 6:60)
ማን ሊሰማው ይችላል ያሉ ሁሉ ጊዜው ሲደርስ ተገለበጡ ! ወደ መጡበት ተመለሱ "ከዚህም የተነሣ ከደቀ መዛሙርቱ ብዙዎች ወደ ኋላ ተመለሱ፤ ወደ ፊትም ከእርሱ ጋር አልሄዱም።" (ዮሐንስ 6:66)

ጊዜው ሲደርስ የሚገለበጥ ህዝብ ይዞ መዝናናት መኩራራት ምንም ጥቅም የለውም። የሰሙት ግን ካንተ ሌላ ምን አማራጭ አለን ብለው ወደ እርሱ ተጠጉ ። ፈፅመውም ተከተሉት።(ዮሐንስ 6:-67-69)
ኢየሱስም ለአሥራ ሁለቱ። እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን? አለ።ስምዖን ጴጥሮስ። ጌታ ሆይ፥ ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ሕይወት ቃል አለህ፤ እኛስ አንተ ክርስቶስ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆንህ አምነናል አውቀናልም ብሎ መለሰለት። በመከራ በስደት በእጦት ጥሪው አባል ማከማቸት ሳይሆን ከኢየሱስ ሌላ ምርጫ የለኝም የሚል እውነተኛ ደቀ መዛሙር ማፍራት ነው ።

" መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ።"(ራእይ 2:29) መንፈስ ቅዱስ ምንድነው ከኔ የሚፈልገው ?
1ኛ, መንፈስ ቅዱስን የሚሰማ ጆሮ
ይኑርህ መሪህ ነውና!1ሮሜ 8:-14
2ኛ,የመለኮት መርህ የሆነውን ቅዱስ
ቃሉን ተቀበል ተቀደስ ጸልይ ትጋ !
3ኛ, ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ስበክ !
4ኛ, እግዚአብሔር አምላክህን በፍጹም
ልብ በፍጹም ሐሳብ በፍጹም ኃይል
ውደድ !
5ኛ, ባልንጀራህን እንደ እራስህ ውደድ !
እግዚአብሔርን ማወቅ ፣ በርሱም መኖር ፣የተፈጠርክበት ዓላማ በሕይወትህ እንዲፈጸም መፍቀድ በመለኮት ከታቀደልህ የተትረፈረፈ ሕይወት ጋር ከማገናኘቱም በላይ
ለሥጋህ እረፍትን ፣ ለነፍስ መታደስን ፣ ለመንፈስህ እርካታ ይሆንልሐልና ። ተባረኩልኝ !
16 views03:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 13:33:59 #አታልቅስ/ሺ !

ራእይ 5፥3-5

"በሰማይም ቢሆን በምድርም ላይ ቢሆን ከምድርም በታች ቢሆን መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው ማንም አልተቻለውም። መጽሐፉን ሊዘረጋ ወይም ሊመለከተው የሚገባው ማንም ስላልተገኘ እጅግ አለቀስሁ።
ከሽማግሌዎቹም አንዱ። አታልቅስ፤ እነሆ፥ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል አለኝ። "

በዚህ ክፍል ሐዋርያው ዮሐንስ ያየው ራዕይ እጅግ ከባድ አስጨናቂ መጽናናትም የማይቻልበት ነው ። መፅሐፍን ሊዘረጋው ወይም ሊመለከተው ማንም ስላልተገኘ እጅግ ሲያለቅስ እንመለከታለን። የመጣለት የመፅናናት ቃል "አታልቅስ" አታልቅስ/ሺ !
የሚል ነው ! ማንም ሊፈታው ቀርቶ ሊመለከተው የማይችለው የታተመ የማይፈታ የተዘጋ ነገር አለ። የሚያስለቅስ ጉዳይ ነው።የሚገርመው ግን በአልቃሽ እና በአስላቃሽ ጉዳይ መሐል ጣልቃ የሚገባ የመፍትሔ አምላክ አለ።

ስለዚህ በሁሉ ላይ ስልጣን ያለው ጌታ እግዚአብሔር ምን አለ? አታልቅስ/ሺ !
ለምን ? ለሰው ልጅ ደህንነት ፣ መፍትሔ ለጠፋለት ጉዳይ፣ ለሚያስጨንቅህ ለሚያውክህ ለሚያስለቅስህ ጉዳይ መፍትሔ አግኝቷል ። አሜን !

ይህ ባዶና በቃል ብቻ የሆነ መፅናናት አይደለም ። ሥጋን ነፍስን መንፈስን የሰውን ሁለንተና ጠልቆ የሚፈውስ የማጽናናት ድምጽ እንጂ። እንዴት ? ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ ማንም ሊፈታ ሊከፍት ሊዘረጋ ሊመለከተውም ያልተቻለውን ማድረግ ተችሎታልና።

ወገኖቼ ዛሬ አዋጅ አለኝ የማልቀሳችን ምክንያት የሆኑ፣ ከኛ ቁጥጥር ውጭ የሆኑ፣ ብዙ ነገሮች አሉ ። ነገር ግን ለናንተ ያልተቻለው የሚቻለው እንባችንን የሚያብስ ፣የመከራውን፣የሰቆቃውን ታሪክ ቀያሪ ጌታ ተገልጧል። ወገኖቼ ሆይ አታልቅሱ። አፍቃሪው ጌታ ማልቀስህን መየት አይችልም።ጌታ በብዙ ክብር ፣በብዙ ፈውስ፣ በብዙ በጎነት ፣ በብዙ ቸርነት፣ በብዙ መልካምነት፣ በብዙ ርህራሄ አቅፎ የሚያጽናና እውነተኛ ወዳጅ ነው። ስለዚህ ከርሱ ከጌታ የተነሳ በፊትህ የሚቆም ምንም የለም ። ለዚህ ነው ጌታ ቆስሎ የፈወሰህ ፣ተሰቃይቶ ያሳረፈህ ፣ ታስሮ ያስፈታህ ፣ተጥሎ ያነሳህ፣ ሞትህን ሞቶ ከሞት ያስነሳህ ኦኦኦኦ ጌታ እውነተኛ ወዳጅ ። ከችግርህ ጋር ከመከራህ ጋር ከስቃይህ ጋር ከምሬትህ ከለቅሶ ጋር ጥሎህ/ሽ አይሔድም ።

ለመሆኑ ለቅሶ ምንድነው? ሰው ለምን ያለቅሳል? በምድር ላይ ለሰው ልጅ የለቅሶ ምክንያት የሚሆኑት ነገሮች ብዙ ናቸው ። እጅግ ብዙ ልብን የሚሰብሩ ፣ አስደንጋጭና መራራ የሆኑ ፣ከሰው ልጅ አቅም በላይ ሆነው የሚያስጨንቁ ፣ እጅግ ብዙ የለቅሶ ምክንያቶች አሉ ።
ስለዚህ ማህተሙን የሚፈታ የተዘጋውን የሚከፍት የመፍትሔ ጌታ አታልቅስ ይልሐል።

በክርስቶስ አሸናፊ ድል ነሺ ታሪክ ቀያሪ ተደርገሐል ።ልታለቅስ ሳይሆን እንባን ሊታብስ ተጠርተሐል። ምክንያቱም ሞትህን በሞቱ ቀየሮ ሕወትን የሰጠህ ፣ በጨለማህ ላይ ብረሀን ይሁን ያለ ፣ በጥፋት ላይ ድህነትን ያወጀ ፣በጉስቁልናህ ላይ ብልጽግና ያወጀ ፣ በመከራህ ላይ በሰቆቃህ ላይ ተገልጦ የምስራች ያለ ጌታ የእንባህ አባሽ ሆኖ ተገልጧል ።

ለቅሶ ሰው ስሜቱን ከሚገልፁባቸው የተለያዩ መንገዶች አንዱ ነው። ሰው ሲያዝንም ሲደሰትም ሊያለቅስ ይችላል ። ሰለዚህ ለቅሶ ሰዎች መጎዳታቸውን፣ ሐዘናቸውን፣ ደስታቸውን፣ ውድቀታቸውን፣ ተስፋ መቁረጣቸውን የሚገልጹበት ስሜታዊ ቋንቋ ነው። ለቅሶ ሰዎች ከውስጣዊ ስሜት በመነጨ ሐዘን በእምባቸው የነፍሳቸውን ብሶት የሚገልጹበት መንገድ ነው ። ኢዮብ ከሚሆንበት ነገር የተነሳ "ፊቴ ከልቅሶ የተነሣ ቀላ፤ የሞት ጥላ በዓይኖቼ ቆብ ላይ አለ" (ኢዮብ 16:-16) ብሎ ሲናገር ዳዊትና ኤርምያስም እንባቸውን እንዳፈሰሱ ይናገራሉ (መዝ 80:-5 , ኤር 9:-1)

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም እንዲሁ ሰው ሆኖ በምድር ላይ ሲመላለስ ስለ ኢየሩሳሌም አልቅሷል። የሚወደው አልአዛር በሞተ ጊዜም አልቅሷል።ሐ/ጳውሎስም በሮሜ መልዕክቱ " ደስ ከሚላቸው ጋር ደስ ይበላችሁ፥ ከሚያለቅሱም ጋር አልቅሱ።"( ሮሜ 12:-15) አንዱ የሌላውን ሐዘን መካፈሉ እንዲሁም አንዱ የሌላውን ደስታ መካፈሉ ሰብዓዊነት ነው። ደስም የሚያሰኝ ነገር ነው። ነገር ግን ሌላው በሐዘን ተመትቶ እንዲያለቅስ ምክንያት መሆን ግን አሳዛኝ ነው ። በሀዘን የተመታም ያለቅሳል። ያልጠበቀው ደስታም ሲፈጠር ሊያለቅስ ይችላል ። ይሁን እንጂ የሚያለቅስ ሰው ስላነባ ማልቀሱ ከሀዘን መግለጫነት ያለፈ መፍትሔ ያስገኝለታል ማለት አይደለም። አፅናኝና እንባ አባሽ ያስፈልጋል።

መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ እግዚአብሔር ከሚታወቅባቸው ከፍቅርና ከርህራሄ መግለጫዎቹ አንዱ እንባ አባሽነቱ ነው ።" (በራዕ:21:-4 ) "...እርሱ እንባዎችን ሁሉ ከአይናቸው ያብሳል " ይላል ። " በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና፥ ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና፤ እግዚአብሔርም እንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል። " (በራዕ 7:-17) (በሉቃ_6_21) ላይም " የሚያለቅሱ ብፁአን ናቸው መፅናናትን ያገኛሉና " በማለት ለቅሶን ወደ መፅናናት ስለ ሚለውጠው እግዚአብሔር ይናገራል ።
ሐዋርያው ዮሐንስ ባየው ራዕይ መፅሐፍን ሊዘረጋው ወይም ሊመለከተው ማንም ስላልተገኘ እጅግ እንዳለቀሰ ይነግረናል። በሽማግሌው "አታልቅስ" ብሎ የመጣለት የመፅናናት ቃል ግን ልብን የሚያሳርፍ ነበር ። የሚያፅናናው ጌታ ኢየሱስ ክርሰቶስ መፅሐፍን ሊዘረጋ ሊመለከተውም ማንም ሊያደርገው ያልተቻለውን ችሎአልና ተባለ ።አሜን !

በጌታ ስንሆን ! በርሱ ስንኖር ! እርሱን ስንከተል ! የጌታ ነን ስንል እምባ አባሽ ወዳጅ አባት አፍቃሪ አለን ። እኛ በርሱ ተጽናንተን አጽናኞች እንሆናለን እርሱን ስንከተል ለብዙዎች የመልካም ነገር ሁሉ ምሳሌዎች እንሆናለን ።

"አታልቅስ" የማልቀሳችን ምክንያት ከኛ ቁጥጥር ውጭ ሊሆን ይችል ይሆናል ። ነገር ግን እግዚአብሔር ይቻለዋል ! እርሱ እንባችንን ያብሰዋል ! ወገኖቼ እናት አባቶቼ እህት ወንድሞቼ አታልቅሱ ! ለእግዚአብሔር የሚሳነው ምንም የለም ። ጌታ ኢየሱስ የመፍትሔ ሁሉ ምንጭ የጥያቄዎቻችሁ ሁሉ መልስ ነው ።
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ ! ስለ ምናለቅስበት ጉዳይ ነጋሪ አያሻህም ! ሁሉንም አንተ ታውቀዋለህ ። ስለአገራችን ሰላም ስለሕዝቦቿ ሁሉ እና ስለ መሪዎቿም ደህንነት ሁሉን ለአንተ አሳልፈን ሰጠን ። ሰላም ይሁን ያዘኑ ወገኖቼ እንባ ይታበስ ። አሜን ! አሜን ! አሜን !
22 views10:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 05:43:37
27 views02:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 05:35:59
28 views02:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-20 05:35:00 የእግዚአብሔር አብሮነት በልዩነት ያኖራል !

(መዝሙር 124 :- 1 - 8)

የእግዚአብሔር አብሮነት ሚስጥር እጅግ ታላቅ ነው። በክብር፣ በሞገስ፣ በመፈራት ፣ በድል፣ በኃይል ፣ በእረፍት፣ በሰላም፣ በልዩነት ያኖራል ።ይህ ክፍል የእግዚአብሔር ከእኛ ጋር መሆንና አለመሆን ውጤት የሰው ልጅ መናገር እንዳለበት የሚገልጽ መዝሙር ነው ።

ዛሬን በህይወት የመገኘታችን ሚስጥር ዛሬን የማየታችን ሚስጥር የእግዚአብሔር አብሮነት ነው። በምድር ላይ በሕይወት እንድንገኝ የማይፈቅዱ ከአቅማችን፣ ከችሎታችን ፣ከጉልበታችን በላይ የሆኑ የማንቋቋማቸው እጅግ ብዙ ነገሮች አሉ። ነገር ግን ከእግዚአብሔር አብሮነት የተነሳ በምህረቱ፣ በጥበቃው ፣ በፍቅሩ ፣በርህራሔው፣ በቸርነቱ፣ በጥበቃው፣ በፍቅሩ...ወዘተርፈ ውስጥ ተይዘናል ።

ከዚህ የተነሳ ሊያጠፋን የዛተው አላጠፋንም፣ ሊገለን የመጣው አላገኘንም፣የተጠመደልን፣ የተመከረብን፣ የታሰበብን፣ የተወሰነብን አልሆነብንም። ተዘልለን ፣ በሞገስ፣ በመፈራት፣ በክብር የመኖራችን ምክንያቱ የእግዚአብሔር አብሮነት ነው። ምክንያቱም ለሰዎች ቁጣ ዛቻ እና ማስፈራራት ለጥርሳቸው ንክሻ ያላደረገን እግዚአብሔር ነውና።

ወገኖቼ ስንት ጊዜ ለሞት ወጥመድ ተዘረጋ ፣ጦርና ቀስት ተወረወረ ? ያስመለጠን፣ ያዳነን፣ የደረሰልን፣ አቅማችን፣ ዘራችን ጉልበታችን ፣ ሐብታችን፣ ችሎታችን...ወዘተርፈ አይደለም የእግዚአብሔር አብሮነት ነው እንጂ።

አስቲ ማዳኑን እዩ ወጥመድ ስውር ነው ፣ ድብቅ ነው ፣ ሳይታሰብ ደርሶ የሚነድፍ ፣ አስሮ ለጠላት አሳልፎ የሚሰጥ ፣ አልያም የሚገድል ነው ። ነገር ግን ከተሰነዘረው ጦር ፣ ከተወረወረው ቀስተ ፣ ከተጠመደው ወጥመድ ለመዳን ለማምለጥ የቻልንበት ሚስጥር የእግዚአብሔር አብሮነት ብቻ ነው። ከብር ለእግዚአብሔር ይሁን ። ለዚህ ነው ዳዊት ነፍሳችን እንደ ወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች፤ ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን ያለው። የተጠመደውን የሰበረ የተመከረውን ያፈረሰ የጠላትን ሐሳብ ከንቱ አድርጎ በክብር ያቆመን እግዚአብሔር ነው። አሜን ! አሜን ! አሜን !

ረድኤታችን ሰማይንና ምድርን በሠራ ፣በሁሉ ላይ ሥልጣን ባለው ፣ሁሉን በሚገዛ ፣ የጌቶች ጌታ የኃያላን ኃያል ፣ የነገሥታት ንጉስ በሆነው በእግዚአብሔር ስም ነው።
ስለዚህ :-
1ኛ, በእግዚአብሔርን አብሮነት እመን ታመንም
ይህ ባይኖር በልዩነት መኖር ከወዴት በተገኘ ?
ስለዚህ እንደ ዳዊት ማዳኑን ክብሩን ጥበቃውን
አውጅ አመስግን ! ጥበቃውና እና ማዳኑ ልዩ ነው !

2ኛ, ለጠላት ፈቃድ ተላልፎ ያለመሰጠቴ ምክንያት
የእግዚአብሔርን አብሮነት ነው በል ጥበቃው ልዩ
ነውና ። ስለዚህ በእግዚአብሔር ታመን ።

3ኛ, ለሞትህ የተጠመደ ወጥመድ ሰብሮ ያስመልጣል !
የጠላት እቅድ ፕሮግራም በሕይወትህ
እንዲከናወን ያልፈቀደው እግዚአብሔር ነው።
ስለዚህ እግዚአብሔርን አመስግን !

4ኛ, እግዚአብሔር ያደረገላችሁን አውሩ አውጁ ተናገሩ
እስራኤል እንዲህ ይበል እንደተባለ በል ተናገር !
ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን ። የታሰበው ፣
የታቀደው ፣ የተመከረው ፣ የተመተተው፣የተጻፈው ፣
የተደገመው አልሰራም አይሰራም አይከናወንም ።

5ኛ, መኖሪያችን ፣መታመኛችን ፣መጠጊያችን ፣እረኛችን፣
ረዳታችን፣ አለኝታችን፣ ክብራችን ፣ሞገሳችን ለእኛ
ሁሉን በሁሉ ሆኖ ያኖረንና የሚያኖረን እግዚአብሔር
ነው ። አሜን ! ክብር ሁሉ ለርሱ ይሁን ! ቅዱሳን ሁላችሁ
ስለ እኛ እና ከእኛ ጋር እግዚአብሔርን አመስግኑ !!!
90 views02:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 07:02:44 አሁንም ብዙ ጊዜ መሠረታችን ስሜት እንጂ ዕቀት አይደለም ያለብን ችግር ይህ ነው፡፡ ስሜትን እንጂ እውቀትን መሰረት ያደረገ የሕይወት ጉዞ የለም ለዚህ ነው ያየነውን የሰማነውን በቅጽበት አግንነን በቅጽበት የምንጥለው ። እንዲህ ዓይነት አካሄድ ደግሞ ከውድቀት ውጪ ውጤት የለውም፡፡ይልቅ በትዕግስት፣በፍቅር ፣ በይቅርታ፣በእርቅ፣ በመመካከር፣ በመተራረም፣ በመቀራረብ፣በመወያየት በተሻለ ዕውቀትት እና የሐሳብ ልዕልና በመረዳዳት፣ በመመካከር፣ በመሸካከም፣ በመተሳሰብ፣ በመተጋገዝ፣ በፍጹም ቅንነት ተያይዘን መጓዝ እና መሥራት ይገነባናል፡፡ይህ ማለት ግን አጥፊ በተገቢዉ መንገድ አይወቀስ፣አይታረም፣ አይገሰጽ ወይም አይተች ማለት አይደለም፡፡ ይልቅ በሳል በሆነ መንገድ እንደ በሳል ማህበረሰብ ችግሮቻችንን በጥበብ በመፍታት ወደ ተሻለ የሕይወት ምዕራፍ እንገስግስ ።
ስለዚህ አንደ ግለሰብ ፣እንደ ቤተሰብ፣ እንደ አንድ አካባቢ ማህበረሰብ፣ እንደ ሀገር ያለንበት መከራ እና ጉስቁልና የሚያበቃበት፣የህዝብ ስደት የሚያቆምበት ፣ጦርነት ተሽሮ፣ መጠላላት ቀርቶ ፣መነቃቀፍ መገዳደል አብቅቶ የተሻለ ባህል እሴት ለሀገር ግንባታ በጋራ የመቆም ኃላፊት አለብን። ግጭት ቀርቶ ሰላም ፣ጦርነት ቀርቶ መረዳዳት ፣መገዳደል ቀርቶ መደጋገፍ ፣ መነቃቀፍ ቀርቶ መከባበር ፣ መበታተን ቀርቶ መሰባሰብ ፣ሐዘን ጠፍቶ ደስታ ፣ ኡኡታ ቀርቶ እልልታ ፣የሚሆነው መቼ ይሆን ብሎ ያልናፈቀ ማን አለ ? እንግዲያውስ:-
1ኛ, መልካሙን ከክፉ በመለየት ለመልካም
እሴቶቻችን እናስቀድም !
2ኛ,በቀደሙት አባቶች በተሰሩት ክፉ
ስራዎች ንሰሐ እንግባ ለይቅርታ ለአርቅ ለፍቅርና!
3ኛ, ለሐገር ሰለም እንጸልይ ክፉን በመልካም በማሸነፍ
የድርሻችንን እንወጣ !
50 views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 07:02:44 ለመልካም እሴቶቻችን ቅድሚያ እንስጥ !

እንደ ማህበረሰብ ዛሬ ያለንበት ሁኔታ ሁላችንንም እጅግ ያሳስበናል፡፡ በእርግጥ አንድ ማህበረሰብ የሚገነባዉ ከቀደሙት አባቶች የወረሳቸዉንና አሁን ያሉትን መልካም እሴቶች (values) መሠረት በማድረግ እንደሚገባ ማክበርና እርሱ ደግሞ ለመጪው ትውልድ ከቀደሙት በተሻለ መገንባት እና መጠቀም ሲችል ብቻ ነው፡፡ማንኛውም ማህበረሰብ በዘመኑ እሴት ብሎ የሚቀርጸው የሚገነባው እና የሚይዘው እርሱ በደረሰበት የእውቀት ደረጃ ነው። እጅግ ጠቃሚው እውነታ ግን እሴቶችን አክብሮ መያዝ ራስንና የራስን ማህበረሰብ ከመገንባት አንጻር እጅግ ከፍተኛ ሚና አለው።

ነገር ግን ለውጥ እድገት የሌለበት የሰው ልጅ የሕይወት ምዕራፍ ፣ የአኗኗር ዘይቤ ፣ የዕውቀት ደረጃ ... የለም ። ይሁንና ዕውቀት፣ ለውጥ ፣ አድገት ፣ ስልጣኔ ፣ የባህል ቅብብሎሽ... አንድን ማህበረሰብ ወደ ተሻለ የሕወት ደረጃ ፣ የአኗኗር ዘይቤ ፣ ወደ ተሻለ ስልጣኔ ፣ እድገት የማያደርሰው ከሆነ በአንጻራዊ ሆኖ በአሉታዊ መልኩ ትውልድን ወደ አመጽ ፣ ወደ ጥላቻ ፣ ወደ በቀል የሚመራ ከሆነ በደልን የሚያስቆጥር ፣ የተደረገውን ክፉ ነገር የሚያሳይ ብቻ ሆኖ ትውልድን በማነጽ ፋንታ ወደ መጠፋፋት የሚመራ ከሆነ ይህ የእድገት ጠላት፣ ወደ ሞት የሚነዳ ሰይጣናዊ አጀንዳ እንጂ ለእድገት እና ለአንድ ማህበረሰብ የተሻለ ህይወት የሚጠቅም አይደለም ።ከፍጥረት ጀምሮ በዚህ ዓለም በኖሩ የሰው ልጆች ታሪክ ብዙ ጠቃሚ የስው ልጆችን መሰረታዊ ችግር ሊፈቱ የሚችሉ መልካም ነገሮች ተሰርተዋል በአንጻሩም እርስ በእርስ ለመጠፋፋት ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ብዙ መሠረቶችም ተጥለዋል።

መጽሐፍ ቅዱስ የዕቀት ምንጭ ፣ የኃይል ምንጭ ፣ የመልካምም ሆነ የክፉ ነገር ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ሁለት የኃይላት ምንጮች እንዳሉ ይገልጻል ። እግዚአብሔር እና ሰይጣን የሚጠቀሙት ደግሞ የሰው ልጅን ነው ። የሰው ልጅም ከፈጠራቸው መልካምና ክፉ ነገሮች በምሳሌነት ኒኩለር እና አውሮፕላን መጥቀስ እንችላለን ኒኩለር የሰው ልጅ እርስ በርሱ የሚጠፋፋበት ሲሆን አውሮፕላን ደግሞ የሰው ልጅ ከአንደኛው የዓም ክፍል ወደ ሌላኛው ማድረስ የሚችል ነው ጠቃሚ መጓጓዣ ነው።እነዚህ የሁለት ኃይላት ምንጮች በሰው ልጅ ታሪክ ላይ የራሳቸውን አሻራ አሳርፈዋል ።

እግዚአብሔር ልጁን በመስጠት ለሰው ልጆች አመጽና ጠላትነት ፍቅርን ምህረትን የቸርነትን የበገነትን ምላሽ ሲሰጥ በአንጻሩ ደግሞ ሰይጣን የሰው ልጅ እርስ በርሱ እንዲጠፋፋ የሞት የጥፋት የሰው ልጅ የውድቀት ምክንያት ሆኖአል ።ስለዚህ የሰው ልጅ ወደደም ጠላ ከነዚህ የኃይል ምንጮች በአንዱ ሥር ነው ። ለዚህ ነው የሰው ልጅ ፍቅርን እያለ በጥላቻ ፣ ሕይወት እያለ በሞት ፣ አንዱ ለሌላው በጎ ማድረግ ሲችል በክፋት ፣ እርቅ እያለ በቂም ፣ይቅርታ እያለ በበቀል ፣ ደስታ እያለ በሐዘን ወዘተርፈ...የሚሰቃየው።
ከቅም አያቶች የወረስነው በመጽሐፍ ቅዱስ ካልተፈተሸ ነገር ሁሉ አንጻራዊ በመሆኑ እነርሱ ከኛ ቀድመው ስለኖሩ በመከባበር ታሪክ ብቻ ሁሉም ነገር ትክክል ነው ብሎ ጠቅልሎ መጉረስ ተገቢ አይደለም ። ከአባቶች የውድቀት ታሪክ አደጋ ለመጠበቅ የውድቀት ምክንያቶቻቸውን አውቆ መጠንቀቅ እንዲሁም ከአባቶች መልካም እሴት በመማር እኛ ደግሞ ለትውልድ የተሻለ የሚጠቅም የሚያንጽ የሚገነባውን መሥራት ነው የሚጠበቅብን ።ስለዚህ አባቶች የሰሩት ሁሉ ልክ ነው በሚል አባዜ ክፉውን ከመልካሙ ሳንለይ ሁሉንም አግበስብሰን በመሔድ ከነርሱ የተሻለ ለትውልደ ትውልዶች መልካም ምሳሌነት የተሻለ እሴት መሠረት ጥለን የምናወርስ አያደርገንም።

ከፋት ፣ጥላቻ፣ አመጽ፣ ሞት፣ ጉስቁልና ፣መጠፋፋት እየተስፋፋ በሰው ልጆች መሃከል ፍቅር እንዲጠፋ የሆነበት ሚስጥር መልካሙን ከክፉ ለይተን መያዝ ስለተሳነንና የቀደሙትን ጠፋት ለመድገም ስለምንጣደፍ ነው ።
እርግማን ፣ በአመጽ በጦርነት መክበር ፣ ሌላውን ጠልፎ ጥሎ ለራስ በመቅደም ፣ ሌላውን ገድሎ በሕይት ለመኖር ፣ ቀምቶ ለመበልጸግ ፣ ሌላውን እያጣጣሉ መክበር ፣ የራስን ትቶ የሌላውን በደል መቁጠር... ዘዘተርፈ የሰው ልጅ የውድቀት መጥፎ ታሪክ ያፈራው ፍሬ ነው ። መከባበር ሲቻል መነቃቀፍ ፣ መተናነጽ ሲቻል መፈራረስ ፣ አንዱ ለሌላው መዳን መስራት ሲችል መገዳደል ፣ በእኩል ደረጃ አብሮ መኖር ሲቻል አንዱ ሌላውን አጥፍቶ ለመኖር ....ወዘተርፈ አሳዛኝ ልብ ሰባሪ ያለፈው ትውልድ ያላየው የክፋት ጥግ እያየን ነው።

አንዱ በአንዱ ላይ ሰይፍ ይመዝዛል ሰብዓዊነት ያለኀጠረበት አውሬ ትውልድ ለአባቶች ፣ ለእናቶች ፣ ለሕጻናት የማይራራ አመጸኛ ትውልድ እያየን እየሰማን ነው።የዓለም ታሪክ ሁሉ መራራ ሆኗል የሚያፈርስ እንጂ የሚገነባ የለም ፣ የሚናናቅ እንጂ የሚከባበር የለም ፣ አንዱ ለሌላው ወድቀት ክፋት የሚጎጉን እንጂ ለመተናነጽ የሚመካከር የለም፣የሚጠፋፋ እንጂ በመተራረም ለተሻለ ሥራ የሚተጋ የለም ። በኛስ ዘመን ሊሆን የሚገባው ይህ ነውን ?

እንደማንኛዉም ሕዝብ እስካሁን ድረስ ሁላችንም የመጣንባቸው መንገዶች ለታሪክ የሚሆኑ የራሳቸው አሻራ አላቸው፡፡ አያት ቅድመ አያቶቻችን፣ ኖረውት ያቆዩልን ቤተሰባችንን፣ ማህበረሰባችንን፣ ሀገራችንንና እኛንም የገነቡ መልካም እሴቶች እንዳሉ ሁሉ ባልተከሰቱ የምንላቸው የመናናቅያ ፣ የመሰዳደቢያ፣ የመገፋፊያ ፣ መጠፋፊያ ሊሆኑ የሚችሉ የእርግማን ውጤቶችም አሉ፡፡ ያለመታደል ሆኖ ግን ዛሬ ላይ ሁሉም እንዳሻዉ የሚመላለስበት፣ ለጋራ መልካም እሴቶቹ የሚሰጠዉ ግምትና አክብሮት ዝቅተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት በማይጠቅሙ ታሪኮች ቂም በቀል ለመፈጸም የዘረኝነት ነቀርሳ የተለከፍንበት ሁኔታ ላይ እንገኛለን ፡፡

ለዚህ ሁኔታ መከሰት ምክንያቶቹ ብዙ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከመልካምና ክፉ ኃይላት ምንጮች በተጨማሪ የፍትህ መጓደል፤ ራስ ወዳድነት፣የፍጻሜ ዘመን ክፋት እየጨመረ መሄድና ሌሎችም ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ምንም ሆነ ምን ግን ስላለንበት ሁኔታ ሁላችንም ኀላፊነትም ተጠያቂነትም እንዳለብን ማወቅ ያስፈልጋል። የሁሉንም ሥራ የሚዳኝ ፈጣሪ አለ። ዛሬ ላይ ያለንበት ሁኔታ ነገሮች ሁሉ መያዣ መጨበጫ በሚያሳጡበት ወቅት ላይ ነው ያለነው፡፡ ሁላችንም በዘመናችን ለራሳችን ለመጪው ትውልድ በምንገነባው መልካም እሴቶች ድርሻ ቢኖረንም ለዚህ እየተጋን ያለን አንመስልም። ስለዚህም ግለሰብ እንደ ግለሰብ ፣ማሕበረሰብ እንደ ማህበረሰብ በየደረጃው የድርሻውን መወጣት ስላልቻለ ለሁሉም እየከበደ ያለዉ እንደ አንድ ማህበረሰብ መተማመንና አብሮ ለረጅም ጊዜ መጓዝ እጅግ አስቸጋሪ እየሆነ የመምጣቱ ጉዳይ ነው፡፡

በመሠረቱ የራስን ድርሻ ሳይወጡ በማሳበብ ብቻ ነገሮችን እንዲሁ እንደ ቀላል አሳንሶ ወይም ቀለል አድርጎ በራሳቸው ጊዜ እንደሚስተካከሉ ማሰብ ስህተት ነዉ፡፡ ለዘመናት የተበላሹ ነገሮች ቢኖሩ እንኳን በጋራ ተመካክሮ ተወያይቶ በማስተካከል፣ ለተሻለ ሕይወት እራስንም ማህበረሰብንም ማዘጋጀት ይቻላል ። ይህ ክፉ በሰለጠነበት ዓለም ውስጥ መልካም እሴትን መገንባት ከፍተኛ መሰዋዕትነት ፣ ብዙ ትዕግስትን፣ ሌት ተቀን መስራትን: ተያይዞ በፍቅር መነሳትን፣ መቀባበልን ፣ የክፋትን ወጤት በጋራ ጠራርጎ ማስወገድን ይጠይቃል ፡፡ ነገር ግን ዕውቀትን መሠረት ያላደረገ ስሜታዊ ጋጋታ የተፈለገዉን ፍሬ ማፍራት እንደማይችል ከብዙ ታሪካዊ ክስተቶች መማር ይቻላል፡፡
42 views04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-14 21:53:55
#ተመልክታችሁ
መንቃት ይሁንላችሁ ::
39 views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-10 18:41:20 ውድና ክቡር የሆናችሁ ቅዱሳን በሙሉ እንኳን ለ2015 አዲስ ዓመት በሠላም እና በጤና ከመላው ቤተሰባችሁ ፣ ጎሮቤቶቻችሁ እና የሥራ ባልደረቦቻቹ ጋር በሠላም አደረሳችሁ !

መጪዉ አዲስ ዓመት (2015 ዓ.ም):-
የሰላም ፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የአንድነት፣ የጤና፣ የልማት፣ የብልፅግና እንዲሆንላችሁ እና ሐገራችንም ኢትዮጵያ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ ግኑኝነት ፍጹም የሆነ የሰላም አየር የሚሰፍንበት የምትረጋጋበት እና የፍቅር የይቅርታ እና የእርቅ መንፈስ በምድራችን ላይ የሚሰፍንበት ለሰው ልጅ ሁሉ በመልካም በረከት የሚትረፈረፍበት፣ ጦርነት እና የጦርነት ወሬ ከምድራችን ላይ የሚቆረጥበት እና ከሁሉ ላይ የእግዚአብሔርን ክብር በምድራችን ላይ የሚገለጥበት ፣ እኛም ስንለምን የኖርነውን ከእግዚአብሔር እጅ የምንቀበልበት ፣ የፈለግነውን የምናገኝበት ፣ ስናንኳኳ የኖርነው ደጅ ለኛ የሚከፈትበት ምርኮ የሚመለስበት ዓመት ይሁንልን ! አሜን።

Baga bara haaraa 2015 nagaan,fayyummaani fi badhaadhinaan maatii keessan,ollaa keessan maamiltoota keessan waliin isin gahe ! Barri haaraa kan badhaadhinaa, kan nagaa fi kan injifannoowwan dachaa itti gonfatan isiniif haa ta'u !!!
58 views15:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ