Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-03-28 21:20:26 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid028kJdk4hadqoDPiK8CWuV2kK3VUUCkVmdpZKjgvfVZoSJwkiAUvCTbiNPytetpaTYl&id=100003254673767&mibextid=irwG9G
18 views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 08:35:02 ኤርምያስ 29
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።
¹² እናንተም ትጠሩኛለችሁ፥ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፥ እኔም እሰማችኋለሁ።
¹³ እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ።
¹⁴ ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ ምርኮአችሁንም እመልሳለሁ፥ ከአሕዛብም ሁሉ ዘንድ እናንተንም ካሳደድሁበት ስፍራ ሁሉ እሰበስባችኋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እናንተንም ለምርኮ ወዳፈለስሁበት ስፍራ እመልሳችኋለሁ።

“እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ሣራን አሰበ፤ እግዚአብሔርም እንደ ተናገረው ለሣራ አደረገላት።”
— ዘፍጥረት 21፥1

“እግዚአብሔርም የለቅሶአቸውን ድምፅ ሰማ፥ እግዚአብሔርም ከአብርሃምና ከይስሐቅ ከያዕቆብም ጋር ያደረገውን ቃል ኪዳን አሰበ።”
— ዘጸአት 2፥24
4 viewsedited  05:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 13:15:50 ሁላችንም ማወቅ የሚገባን መሰረታዊ የጤና እውቀት

ጤናማ #የደም_ግፊት መጠን ― 120/80

ጤናማ #የደም_ሥኳር መጠን ― ከ 70 እስከ 120

ጤናማ #የልብ_ምት በደቂቃ ― ከ 60 እስከ 80

ጤናማ #የኮሌስትሮል_መጠን በሚሊ-ግራም ― 200

ጤናማ #የሰውነት_ክብደት ከቁመት ጋር ያለው ንጽጽር (BMI) ― ከ 20 እስከ 25

ሰውነታችን በሳምንት ውስጥ የሚያስፈልገው #የእንቅስቃሴ_መጠን በደቂቃ ― 150 ደቂቃ

በቀን ውስጥ የሚያስፈልገን #የመጠጥ_ውሃ መጠን በሊትር ― ከ 2 እስከ 3 ሊትር

በቀን ውስጥ ማግኘት ያለብን #የእንቅልፍ_ሠዓት ― ከ 7 እስከ 9 ሠዓት

“ጤና ይብዛልዎት”
ምንጭ ካነበብኩት
16 views10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 05:01:26
#የሚያውቁህ_ያገኙህ_ያዩህ_በመሰጠት_ያመልኩሐል...
#በቃልህ_ውስጥ_ሕልውናህ_አለ
#በመገኘትህ_ውስጥ_ሐሴት_አለ
#ክብር_ሞገስ_ኃይል_መፈታት_አለ
#ነፍሴ_መገኘትህ_ያሳርፋታል_ቸርነትህ_በጎነትህ_ታማኝነትህ_ያስፈነጥዛታል !
#የሚያውቁህ_ያገኙህ_ያዩህ_በመሰጠት_ያመልኩሐል

#በሁለንተናቸው_አልፈህ_ስጋቸውን_ነፍሳቸውን_መንፈሳቸውን_ታረሰርሳለህ
#ዋውውው_ጌታ_ሆይ_በመንፈስህ_እና_ከመንፈስሀ_በሆነ_ሕያው_አምልኮ_አመልክህ_ዘንድ_ከህልውናህ_ከመገኘትህ_አታውጣኝ
#አንተ_ካለህበት_የመንፈስህ_መገኘት_ከወረሰው_ስፍራ_አግኝቼህ_ሳመልክህ_ልኑር
#መንፈሴ_ነፍሴ_ስጋዬም_ለክብርህ_ለታላቅነትህ_ለገናናነትህ_ይስገድ_ይገዛልህ#ለአንተ_ያልተገዛ_ማንነቴ_በክብርህ_ይወረስ#በብረሃንህ_ክብር_ተገናኘው_ግዛው_አንበርክከው_ፍቃዴን_በፈቃድህ_ስሜቴን_በስሜትህ_ዕውቀቴን_በዕውቀትህ_ቀይረው !#ነፍሴ_ለክብርህ_ትገዛ

#በአምልኮዬ_በአገልግሎቴ_በኑሮዬ_የእኔ_ማንነት_ተሰውሮ_የአንተ_ሕልውና_ይገለጥ...#ሁሌም_መገኘትህ_ይሰማኝ_ሕያው_መቅደስህ_ልታደርገው_በወደድከው_ሰውነቴ_በመንፈስህ_ማደሪያነት_ይታወቅ_የክብርህ_እሳት_የሞገስህ_ብርታት_የኃይልህ_ታላቅነት_ይገለጥበት
#የበጎነት_ሁሉ_ምንጭ_ህልውናህ_ነውና#ያለ_ህልውናህ_ያለ_መገኘትህ_አምልኮ_አገልግሎት_ባዶ_ድካም_ነው። #ዝማሬ_ስብከት_እልልታ_ሽብሸባ_ጭብጨባ_ባዶ_የድምጽ_ጋጋታ_ብቻ_ነው..
#ያለ_ህልውናህ_ንግግር_ብቻውን_ባዶ_ፊደል_ነው#ለንግግራችን_ትርጉም_የሚሰጠው_ዜማችን_ለበረከት_የሚያደርገው_አምላኬ_ያንተ_ህልውና_ነው#ሕልውናህ_ይማርካል_ሕልውናህ_ይገዛል_ሕልውናህ_ያንበረክካል_ሕልውናህ_የተገናኘ_ነፍስ_አይቀርለትም_አመስግኖህ_አይጠግብም_አክብሮህ_አያባራም_አንተካለህበት_መውጣት_ከምትገኝበት_መራቅ_ለርሱ_ሞት_ነው#አምላኬ_ሆይ_ሁሌም_በሕልውናህ_ውስጥ_በመገኘትህ_ውስጥ_አኑረኝ!!
37 views02:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 19:32:57 መለሰን !

“እንዲህም አልሁ፦ አምላኬ ሆይ፥ ኃጢአታችን በራሳችን ላይ በዝቶአልና፥ በደላችንም ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ ብሎአልና አምላኬ ሆይ፥ ፊቴን ወደ አንተ አነሣ ዘንድ አፍራለሁ፥ እፈራማለሁ።” — ዕዝራ 9፥6
ቆም ብረን ራሳችንን እንድናይ ኃጢያታችንንም እንድናስተውል ንሰሐ እንድንገባ ለፍቅር ለእርቅ ለሰላም ይቅርም ለመባባል እድል የሰጠ እና የሚሰጥ እግዚአብሔር ይመስገን ።

ከአፋችን የኩራት የትዕቢትም ቃል አይውጣ የደረሰልን እግዚአብሔር ይቅር ባይ መሐሪም ነውና ። በፊቱ ለሚጮሁ ፣ፊቱን ለሚፈልጉ፣ ንሰሐ ለሚገቡና ለሚያለቅሱ ደራሽ የሆነ ፣ ምድራችንን ከእልቂት፣ ከደም መፋሰስ፣ ከጥፋት የታደገ እግዚአብሔር ይመስገን ። ማረን ብለን ጮኸን ያላሳፈረን ፣ ይቅር በለን ብለን አልቅሰን ያየንና የሰማን እንባችንን ከአይናችን ያበሰ ፣ ጦርንና የጦርን ወሬ ከምድራችን ላይ የቆረጠ ፣ ኢትዮጵያን ዳግመኛ በምህረት አይኑ የጎበኘ አምላክ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ይመስገን ።

አሁንም ለፍቅር ለአንድነት ለምህረት ለልማት ለእድገት በአንድ ልብም የእግዚአብሔርን ፊት በመፈለግ በንሰሐ እንውደቅ ለሁሉም ነገር የመፍትሔ አቅጣጫ የእግዚአብሔርን ፊት መፈለግ ነውና ።ለአገር ሰላም ለሕዝብ ደህንነት ማሰብ መልካምነት ነው ። አገር ሰላም ብትሆን ሕዝብም ደህንነቱ የተጠበቀ ቢሆን ሁሉም ተጠቃሚ ይሆናል። ሽብር ፣ ጦርነት ፣ ክፉ ዜና መዝራት ብሔርን ከብሔር ፣ ሕዝብን ከሕዝብ ማጋጨት አይጠቅምም ፣ ሕዝብ መሪውን ሲያከብር መሪም ሕዝቡን ሲያከብር ሁሉም አባቶች በሁሉ ሲከበሩ መየት እንዴት ደስ ይላል ?

ትዕቢት የት ያደርሳል ? እግዚአብሔር በምህረቱ ተመልክቶናል እንደ ጠላት ዛቻም አላደረገብንም “አንተ የተጠቃውን ሕዝብ ታድናለህና፤ የትዕቢተኞችን ዓይን ግን ታዋርዳለህ።” — 2ኛ ሳሙኤል 22፥28
ስለዚህ ምህረት ከእርሱ ዘንድ ነውና “ሁላችሁ ቅዱሳኑ፥ እግዚአብሔርን ውደዱት፤ እግዚአብሔር እውነተኞችን ይፈልጋል፥ ትዕቢተኞችንም ፈጽሞ ይበቀላቸዋል።”— መዝሙር 31፥23
እግዚአብሔርን በመፍራት በተዋረደ እና በተሰበረ ልብ በፊቱ እንሁን “ዓለሙን ስለ ክፋታቸው ክፉዎቹንም ስለ በደላቸው እቀጣለሁ፤ የትዕቢተኞችንም ኵራት አዋርዳለሁ።”— ኢሳይያስ 13፥11 ያለ እግዚአብሔር ሁሉን ይመለከታልና ።

ወገኖቼ እኛ እንኳን በጥላቻ በፍቅርም ለመኖር ጊዜው አጭር ነውና ፍቅር እያለ ሰው እንዴት ለመገዳደል ይሯሯጣል ? እንዴትስ አንዱ በሌላው ሞት ይደሰታል?እንዴትስ በሌላው ጉስቁልና ይዝናናል ? እንዴት ያደገበትን ማህበሰሰብ ይጎዳል ? ሰው እንዴት የኖረበትን ፣ የተማረበትን ያፈርሳል ? ሰው እንዴት የኖረበትን ቤት ያቃጥላል ? እንዴትስ የጎረሰበትን እጅ ይሰብራል ? አሁንም እንመለስ የመፍትሔ ሁሉ ምንጭ የሆነውን አምላክ የእግዚአብሔርን ፊት እንፈልግ ። እርሱ እግዚአብሔር ምህረቱን ቸርነቱን በጎነቱን በምድራችን ላይ ያፍስስ ።

በአባቶች ባህል በመከባበር ቁጭ ብሎ ሐሳብን ማጋራት ማስተማር መወያየት ወደ ጋራ ሐሳብ እና ተጠቃሚነት መምጣት እየተቻለ ሰው እንዴት የገዛ ወንድሙን ለማጥፋት ያነሳሳል ? ቆም እንበል የጣልነውን ፍቅር አንድነት መከባበር እናንሳ ፤ በትዕግስት በእርጋታ ወደሚያሳድገን ፣ ወደሚያፋቅረን ፣ በአገራችን በጋራ ወደምንኖርበት አስተሳሰብ እንምጣ ። ለትውልድ እናስብ ሰው ሙሉው ሐገር የርሱ ሆኖ እንዴት መንደር ይናፍቃል ? የኔ ሐሳብ ካልተፈጸመ ብሎስ ለትውልድ የሚቀረውን ቅርስ ማፍረስ ምን ይሉታል ? እስቲ ራሳችንን እንጠይቅ አሁንም እውነተኛውንና የመፍትሔ ምንጭ የሆነውን የእግዚአብሔርን ፊት እንኀልግ ።

ሰላም እያለ ጦርነት፣አብሮነት እያለ ልዩነት፣ ፍቅር እያለ ጥላቻ ፣ ልማት እያለ ጉስቁልና ለምን ? አንዱ ለሌላው እድገት በማሰብ ወንድሜ ከኔ የተሻለ ነው የምንልበትን ባህል ምን ወሰደው ? በትህትና ለታላቅ ወንድም ተነስተን አጎንብሰን እጅ የምንነሳበት ክቡር ባህል እና ሥርዓት ምን ዋጠው ? እኛ ኢትዮጵያውያን ሌሎች ሊጋሩት የሚገባቸው የዳበሩ የከበሩ የፍቅር የአብሮነት የአንድነት የመተሳሰብ ...ወዘተ እስቶች አሉን ።

በዝርፊያ ለማደግ ጦር ከመማዘዝ ለጋራ አድገት እና ተጠቃሚነት ብንሰራ የት በደረስን ። ዘረኝነት ነቀርሳ ጎሰኝነት መርዝ ነው። ልዩነት ምን ይጠቅማል ? እኛ ኢትዮጵያውያን ዛሬ ዛሬ ላይ መቻቻልን የሚጠይቁን ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ተፈጥረውብናል። በፖለቲካው፣ በሀይማኖት ፣ በባህል ፣ በቋንቋ ፣ በሰንደቅ ዓላማ ፣ በብሔር የተከለሉ ድንበሮች... ወዘተርፈ ! መናናቅ ትዕቢት ጦረኝነት ስድብ አይጠቅመንም።
እኛ የአንድ ሐገር ሕዝቦች ፣የተጋባን ፣ የተዋለደን ፣የተሳሰረን፣ አብረን የምንኖር ፣አብረን የምንበላ ፣አብረን የምንጠጣ ፣ በመሆኑ በአብሮነት ሕይወት የተጋመደ ብዙ የጋራ እሴቶች ያለን ሕዝቦች ነን ።

ስለዚህ በፖለቲካው መስክ ያላችሁ ሴረኞች ተመለሱ ከስሜታዊነት ውጡ አርቃችሁ እና አስፍታችሁ ተመልከቱ ፣
በሀይማኖት ያላችሁ አክራሪዎች ጥቂት ልዩነቶች ቢኖሩም እርስ በርስ ጠላቶች ሊያደርገን የሚችል ነገር አንደሌለ አስተውሉ ፣ በባህል በኩል ያላችሁ ልዩት ውበት እንደሆነ አስቡ ፣በቋንቋ ሕዝብን ከሕዝብ የምታባሉ ቋንቋ መግባቢያ እንጂ ጦር የሚያማዝዝ አለመሆኑን አስተውሉ ፣
የሰንደቅ ዓላማ ልዩነትን የምታራግቡ በጋራ የምንስማማበት አንድ የልብ የቃል ኪዳን ማሰሪያ እንዲኖረን ጣሩ ፣
የዘረኝነትን ነቀርሳ የምታባዙ ፍቅርን ስበኩ ያ በኤደን ገነት የሌለ የሰው ብልሐት የፈጠረው ተረት ነውና ፣በተከለሉ ድንበሮች ደም ለማፋሰስ የምትሯሯጡ የሰው ልጅ የከበረ ፍጥረት መሆኑ ይሰማችሁ ፣ የጋራ እሴቶችን ለማጥፋት ሌት ተቀን የምትሰሩ ሆይ ተመለሱ የእግዚአብሔር እጅ በናንተ ላይ ነው ።

በአጠቃላይ ሕዝቡ በአብሮነት ሕይወት የተዛመደ የተጋመደ አብሮ የኖረ የተጋባ የተዋለደ ሕዝብ ነውና ። አሁንም እግዚአብሔር በሁሉ አንጻር ፍቅርን እርቅን እና ሰላምን ያብዛልን !

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ !
8 views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-20 04:26:22 ጥምቀት ለደህንነት(ለዘላለም ሕይወት) ያስፈልጋል ብሎ ማመንና ማስተማር የክርስቶስን መስቀል ከንቱ ማድረግ ነው፡፡ወንጌልን ልሰብክ እንጂ ለማጥመቅ ክርስቶስ አላከኝምና አለ። (1ቆሮ 1፡17) በውሃ ጥምቀት እና በአፈጻጸሙ ላይ የሚነሱ የተለያዩ አመለካከቶች ቢኖሩም የውሃ ጥምቀት ለደህንነት ወይም ለኃጢአት ሥርየት አስፈላጊነቱ ወሳኝ ነው ባንልም የማዳኑ ሚስጥር በግልጽ በሚታይ ሥረዓት የምንገልጽበት የከበረ ስርዓት ነው ። ለደህንነታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሰራልን ሥራ በቂ ነው።ትክክለኛው የጥምቀት በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም የሚደረገው የጥምቀት ሥርዓት ነው። ተባረኩ !
46 views01:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-20 04:26:22 የውሃ ጥምቀት ምንነት እና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጉም !

ጥምቀት፡ በግሪክ “ባፕቲዞ” (Baptism:- Immersion) ሲባል የቃሉ ትርጉም ሙሉ በሙሉ ወደ ውሃው መስመጥ እና መሸፈን (ከእይታ ውጭ መሆን) የሚያመለክት ነው፡፡ ሞልቶ በሚሲፈስ ነገር መሸፈን በዚያ ነገር ቁጥጥር ውስጥ መሆን የሚለውን ሐሳብ ይይዛል።

የሚታይ የጥምቀት ሥረዓት ከክርስቶስ ጋር በሁሉ መተባበራችንን የምንገልጠበት ምሳሌያዊ ምስክርነት ነው።
የምንጠመቀው በክርስቶስ የዳንበትን አዳዳን በተግባራዊ ስረዓት ለመግለጽ ነው። ከክርስቶስ በሞቱ እና በትንሳኤው መተባበራችንን በመግለጥ ዓለምንና ዓለማዊነትን መሰናበታችንን በሁሉ ፊት እንመሰክራለን። ከክርስቶስ ጋር በሞቱ እና በትንሳኤው መተባበራችን የሚገለጠው ወደ ውሃው ስንገባ መሞታችንን ፣ስንጠልቅ መቀበራችንን፣ ከውሃው ስንወጣ ለአዲስ ሕይወት መነሳታችንን ለመመስከር የጥምቀት ሥርዓት የምንፈጽመው።

መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር :-
" እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን" (ሮሜ 6:-4-6)

እኛ ብዙ ጊዜ "ጥምቀት" የሚለውን ቃል የምናያይዘው ከ"የውሃ" ጥምቀት ጋር ብቻ ነው። ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ተለያዩ ጥምቀቶች ይናገራል ። የተለያዩ የጥምቀት አይነቶች አሉ፦
1) የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፦
2) የውሃ ጥምቀት፦
3) የእሳት ጥምቀት፦
4) በመከራ መጠመቅ ስለ እያንዳንዱ ማብራራት ዓላማችን ስላልሆነ ወደ ውሃ ጥምቀቱ እንግባ ።
የውሃ ጥምቀት በክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ በማመን መዳናችንን በምሳሌነት የምናሳይበት እውነት መሆኑን ካየን ( 1ጴጥ 3፡20-21 )

የጥምቀት ከመፈጸሙ በፊት የሚያስፈልገው መንድነው ? የሚለውን እንመልከት :-በ (ሐዋ. 8:28-37 ) ሲናገር
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባው በውሃ ከመጠመቁ በፊት በት.ኢሳ 53 ያለውን ክፍል አንብቦ ስለ ማን እንደሚናገር ግራ ተጋብቶ ሳለ በፊሊጶስ ጥያቄ ቀረበለት :-
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
" ሲመለስም በሰረገላ ተቀምጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር።መንፈስም ፊልጶስን፦ ወደዚህ ሰረገላ ቅረብና ተገናኝ አለው።ፊልጶስም ሮጦ የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ሲያነብ ሰማና፦ በውኑ የምታነበውን ታስተውለዋለህን? አለው። እርሱም፦ የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል? አለው። ወጥቶም ከእርሱ ጋር ይቀመጥ ዘንድ ፊልጶስን ለመነው። ያነበውም የነበረ የመጽሐፉ ክፍል ይህ ነበረ፤ እንደ በግ ወደ መታረድ ተነዳ፥ የበግ ጠቦትም በሸላቹ ፊት ዝም እንደሚል፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በውርደቱ ፍርዱ ተወገደ፤ ሕይወቱ ከምድር ተወግዳለችና ትውልዱንስ ማን ይናገራል? ጃንደረባውም ለፊልጶስ መልሶ፦ እባክህ፥ ነቢዩ ይህን ስለ ማን ይናገራል? ስለ ራሱ ነውን ወይስ ስለ ሌላ? አለው። ፊልጶስም አፉን ከፈተ፥ ከዚህም መጽሐፍ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ወንጌልን ሰበከለት።

ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የወንጌልን እውነት ተረድቶ ጌታ ኢሱስ ክርስቶስን የመስቀል ላይ ሥራ አንብቦ የማዳኑ ሚስጥር ገብቶት :-
“በመንገድም ሲሄዱ ወደ ውኃ ደረሱ፤ ጃንደረባውም፦ እነሆ ውኃ፤ እንዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድር ነው? አለው።”
— ሐዋርያት 8፥36
አየህ የማዳኑ ሚስጥር ከገባህ ፣ በመስቀል ላይ የተሰራልህ አስደናቂ የማዳኑን ስራ በልብህ ከመንክ እንዳትጠመቅ የሚከለክልህ ነገር የለም ።
“ፊልጶስም፦ በፍጹም ልብህ ብታምን፥ ተፈቅዶአል አለው። መልሶም፦ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ አለ።”
( ሐዋርያት 8፥37 )

ከውሃ ጥምቀት በፊት አንድ ሰው በክርስቶስ እየሱስ በመስቀል ላይ የተደረገለትን እና እየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢያአቱ እንደተቀጣ ማወቅ እና ማመን መቀበል ይኖርበታል። ጃንደረባውም አንባቢ ነበር ታስተውለዋለህ ሲባል እንዴት እንዲህ ታስበኛለህ አላለም ፊሊጶስን ጠራው በጎኑ አስቀመጠ ከርሱ ተማረ ጠየቀ ተረዳ ኢየሱስ ክርስቶስን በሙሉ ልቡ አመነ ተጠመቀ ።

በውሃ የመጠመቁ ትርጉም :-
1) አማኙ በጌታ በኢየሱስ ሲያምን ከክርስቶስ ጋር መሞቱን ፣ አብሮ መሰቀሉን በሞቱ መተባበሩን ይገልጻል።

2) አማኙ ከጌታ ኢየሱስ ጋር በመቀበሩ መተባበሩን ወደ ውሃ ውስጥ በመጥለቅ ነው። በዚህም ለአሮጌው የሕይወት ስርዓት መሞቱን ይገልጽበታል፡፡ ይህም ከጌታ ጋር በመቀበር መተባበሩን ይገልጻል፡፡( ሮሜ 6፡4፣ ቆላ 2፡12.)

3) ከኢየሱስ ትንሳዔ ጋር መተባበሩንና ለአዲሱ የሕይወት ስርዓት በትንሳኤው የክርስቶስን ህይወት ተካፍሎ መነሳቱን ያሳል፡፡ (ሮሜ 6፡4-5, 1ጴጥ 3:21.) ይህም ከውኃው በሚወጣበት ቅጽበት ይገለጻል፡፡

4) ከዚያ በኋላ በሚኖሩበት ዘመን ሁሉ የትንሳኤ ሕይወት እየተገለጠበትና የንሰሐ ፍሬን በማፍራት በአዲስ ሕይወት መመላለስ ይገባል ፡፡ (ሮሜ 6፡7-11)

ደህንነት ወይም የዘላለም ሕይወት የሚገኘው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለኃጥያታችን መሞቱን እና መነሳቱን እንዲሁም ለደህንነታችን በመስቀል ላይ የተፈጸመልንን ሥራ አምኖ በመቀበል ነው፡፡

አንድ ሰው የውሃ ጥምቀትን ለመውሰድ የተሰጡ አራት መርሆች :-
1). ወንጌል ሊመሰከርለት ይገባል !
2). በሙሉ ልቡ አምኖ መቀበል ይኖርበታል /እምነት/
3). በንሰሐ በክርስቶስ ደም ሕሊናውን ተረጭቶ መቀደስ
4). ስሙን እየጠራ መጠመቅ ይኖርበታል !

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል:-
ጌታ ኢየሱስ ለአጥማቂዎች በማን ስም ማጥመቅ እንዳለባቸው በታላቁን የወንጌል ተልዕኮ ሲገልጥ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቁ መመሪያ ሰጥቷቸዋል " እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ። (ማቴዎስ 28:-19-20 )

ተጠማቂው የሚጠመቀውን ሰው ደግሞ የጌታ የኢየሱስን ስም እንዲጠራ ይደረጋል ምክንያቱም የመጀመሪያዎቹ አይሁዶች በዚያን ዘመን አብንና መንፈስ ቅዱስን ቢያወቁም ኢየሱስ ክርስቶስን ግን አይቀበሉትም ነበር ይህ ደግሞ የመዳናቸውን እውነት መጣል ስለሆነ ማመናቸውን ለማወቅ እየጠሩት እንዲጠመቁ ይደረግ ነበር።“አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።”አለው ( ሐዋርያት 22፥16)

ለምሳሌ ሐዋርያው ጴጥሮስ በበዓለ ሀምሳ ወንጌል የሰበካቸውንና ያመኑትን ሰዎች የጌታን ስም እየጠሩ እንዲጠመቁ ያዛቸዋል።ጴጥሮስም፡— ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ። (ሐዋ. ሥራ 2 :-38)

በአጠቃላይ ጥምቀት አማኙ ኢየሱስን በማመን ብቻ የዘላለም ሕይወት ተስፋ ከተቀበለ በኋላ ከክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ ጋር መተባበሩን በመመሥከር የቤተክርስቲያን አባል ለመሆንና እንደሌሎች ወንድሞቹ ሁሉ ለኃጥያት መሞቱንና ከጌታ ኢየሱስ ጋር መቀበሩን፣ መነሳቱን እንዲሁም በአዲስ ሕይወት ለመመላለስ መወሰኑን የሚያሳይበት ምሳሌ ነው፡፡
176 views01:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 08:38:44 በኦርቶዶክስ ስነ-መለኮት ምሁራን እና በፕሮቴስታንት ስነ-መለኮት ምሁራን መካከል ያለ የቤተክርስቲያን ታሪክ ምልከታ አንድነት እና ልዩነት !

በኦርቶዶክስ ስነ-መለኮት ምሁራን እና በፕሮቴስታንት ስነ-መለኮት ምሁራን መካከል ያለ የቤተክርስቲያን ታሪክ ምልከታ አንድነት እና ልዩነት ምን ይመስላል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ወደ አንድ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት መደብር ጎራ አልኩኝ። ለዚህ ጥያቄዬ መላሽ ሊሰጠኝ ይችላሉ የምላቸውን ሁለት ተከታታይ መጽሐፍት መረጥኩ መጽሐፉ :- የእግዚአብሔር መንግስት ታሪክ በምድር ላይ በቀ/ዶ/ር ምክረ ሥላሴ ገ/አማኑኤል በ2000 ዓ.ም የተጻፉ ሲሆኑ ሁለት መጽሐፍት ናቸው ።አንደኛ መጽሐፍ እና ሁለተኛ መጽሐፍ ንባቡን ጀምሬ ከገጽ 1 - 19 ካለው የተረዳሁት እነሆ :- ጸሐፊው በአገር ውስጥ እና በውጭ አገርም ሄጄ ላደረጉኝ ለውድ የመንፈስ ቅዱስ አባቴ ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያረክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ዘኢትዮጵያ መታሰቢያ አድርጌ ሳበረክት በታላቅ ትህትና ነው ይላሉ።

የቤተ ክርሶቲያን ታሪክ የእግዚአብሔር መንግስት ታሪክ ነው። በመሆኑም የቤተ ክርስቲያን ታሪክ የእግዚአብሔር መንግስት በምድር ላይ እንዴት እንደተመሠረተና ኦንደተስፋፋ የሚገልጽ ሐተታ ነው። የመንግስቱ ዜጎችም በብሉይና በአዲስ ኪዳን ያሉ አማኞችን የሚጠቀልል ነው። ብሉይ ኪዳን እንደ መቅድም የሚታይ ቢሆንም መንግስቱ በሙላት የተገለጸው ቃል ሥጋ ለብሶ በኛ ካደረ በኃላ ነው።የቤተክርስቲያን መስራች የራሷ አካል ራስ ንጉስ የሆነው የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በርሱም አካል የመለኮት ሙላት የታደሰው ሰብዕና እና መላው የሰው ልጅን የማዳን እቅድ እንዲሁም ሰው በእግዚአብሔር መልክ እና አምሳል ከተፈጠረበት ጀምሮ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ያለው የሰው ልጅ ታሪክ ነው።

የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ክርስቲያኖች በክርስትና ሕይወታቸው ያደረጉትን ያሳለፉትን መከራ እና ሥቃይ እንዲሁም በእምነቱ መስፋፋት ያገኙትን ደስታ በኃጢያት ላይ የተጎናጸፉትን ድል ይገልጻል። የቤተክርስቲያን ታሪክ ዋናና ማዕከላዊ ነጥብ የዓለም መድህን ሆና የኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ምድር መምጣት የሚገልጽ ሲሆን የታሪኩ ማዕከል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህም ታሪክ የዘመናትን ቀመር እንደምንመለከተው ከክርስቶስ በፊት እና ከክርስቶስ በኃላ ተብሎ ይገለጻል። ከክርስቶስ በፊት የነበረው ጊዚ ለክርስቶስ መምጣት የመዘጋጀት ጊዜ ሲሆን ከክርስቶስ በኃላ የእግዚአብሔር መንግስት መገለጡን የምናይበት ነው ።

"የቤተ ክርስቲያን ዋና ዓላማ ወንጌልን ለዓለም ሁሉ መስበክ እና ብዙዎችንን የክርስቶስ ተከታይ ማድረግ ነው ። ወንጌል መሰበክ ያለበት ለአይሁድ እና ለአህዛብ ፣ለወንድ እና ለሴት ፣አርነት ለወጡ እና ላልወጡት ነው።" ገጽ 19 ይመልከቱ ።

እስካሁን ባነበብኩት በኦርቶዶክስ እና ፕሮቴስታንት አማኞች አመለካከት ያገኘሁት የሐሳብ ልዩነት የለም ንባቡን እንቀጥላለን ።
28 views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 05:29:52 መንፈሳዊ ውጊያ !

እውነተኛው መንኀሳዊ ሰው ከመናፍስቱ ዓለም ጦረኞች ጋር ዕለት ዕለት የሚፋለም ነው።

መግቢያ

የመንፈሳዊው ዓለም ጦርነት የተጀመረው በሰማይ ነው። በዚያ በተደረገው ጦርነት ሰይጣን ከሲሶ መልዓክቱ ጋር ወደ ምድር ተጣለ።“በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉ። ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ፥ አልቻላቸውምም ፥”( ራእይ 12፥7)
ይኸው ከእግዚአብሔር መልዓክት ጋር የነበረ ጦርነት በምድር ደግሞ ከሰው ልጆች ከአዳምና ከሔዋን ጋር ቀጠለ ። ሰይጣን በሰማይ ተሸንፎ ሲወድቅ በምድር ደግሞ አሸነፈ ። በዚህም የሰው ልጅ ከክብሩ ወደቀ፣ ለኃጢያት ባርነት፣ ለመንፈሳዊ እስራት፣ ለመንፈሳዊ ሞት እና ፍርድ ተጋለጠ።

ሰው ይህንን ጦርነት ማሸነፍ ስላልቻል የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ወርዶ ተዋጋለት ሰይጣንንም አሸነፈው። ከዚያም ጌታ ለሚያምኑት ቅዱሳኑ ሥልጣንን ሰጣቸው ፣የድሉን ክብር፣ ምርኮን ይሰበስቡ ዘንድ በተሸነፈው ዓለም ላይ ገለጣቸው።

ሰይጣንን ጸንተው እንዲቃወሙ ሁሉ እንደተሸነፈ ስልጣንንም እንደሰጣቸው ነግሮአቸው ወደ አብ አባቱ ተመልሶ በቀኙ ተቀመጠ።“በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።”(ገላትያ 5፥1)

ስለዚህም እውነተኛ ክርስቲያኖች በማያቋርጥ ጦርነት ውስጥ ናቸው። ምክንያቱም ሰይጣን ሁል ጊዜ ክርስቲያኖች ወደ ታሰበላቸው ግብ፣ወደ ተዘጋጀላቸው በረከትና ክብር፣ ወደ ከበረው አሸናፊና የድል ሕይወት እንዲገቡ አይፈልግም በመሆኑም በየሰከንዱ፣ በየደቂቃው፣ በየሰዓቱ፣ በየቀኑ ወደ ክርስቲያን የሚላኩ እርኩሳን መናፍስቶች እንዳሉ ማወቅ ይኖርብናል።
“መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።”
( ኤፌሶን 6፥12)

ለዚህ ነው ቅዱሱ ቃል ዘወተር ወታደራዊ የሆነ ዝግጅት እንዲኖረን የሚነግረን ። "... የዲያብሎስን ሽንገላ ትቃወሙ ዘንድ እንዲቻላችሁ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ ልበሱ ። መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና ፣ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ ..." (ኤፌሶን 6:11-20)

የእምነት አባቶች በምድር በኖሩበት የሕይወት ምዕራፍ የተፋለሙ የክፋት የእርኩሰት መናፍስትን ተቃውሞ ፣ ተግዳሮት፣ጦርነት ነው።በመሆኑም በዕብራውያን 11 እንደተገለጸ መንፈሳዊውን ጦርነት ገጥመው መልካሙን የእምነት ገድል ተጋድለው ድል ነስተው አለፉ።

እኛስ ይህ እውነት ገብቶናል ወይ ?ሰይጣን በመንፈሳዊው ጦርነት ድል ለመንሳት ከዘመኑ ጋር የሚዘምንበት ፣ ከቴክኖሎጂው ጋር የሚራቀቅበት፣ ከዕውቀቱ ጋር የሚጠበብበት የራሱ አካሔድ አለው። በዘመኑ ስልጣኔ ትውልዱን በደረሰበት የዕውቀት ደረጃ በምኞቱ በፍላጎቱ በመሻቱ የሚያጠምድበት የራሱ ዘዴ ፣ ብለሃትና ብልጠት አለው። ሰይጣን የዘመኑን ሥልጣኔ ተጠቅሞና በእርሱ ውስጥ መሽጎ ትግሉን እጅግ በረቀቀ መንገድ እያካሄደ ይገኛል።ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊውን ጦርነት ማስቀጠል ይቅርና እራሷም እውነቸኞችን በማሳደድ ፣ የወንጌል እንቅፋት የሚሆኑትን በማስተናገድ በማመቻመች በመመሳሰል በሽንገል ላይ የምትገኝ ይመሥላል። ምክንያቱም የመንፈሳዊው ዓለም ጦርነት ዋጋ ያስከፍላል፣ ለመሰዋዕትነት ይዳርጋል ፣ ምቾት ይነሳል፣ ላያስማማ ይችላል። “በእውነትም በክርስቶስ ኢየሱስ እግዚአብሔርን እየመሰሉ ሊኖሩ የሚወዱ ሁሉ ይሰደዳሉ።”( 2ኛ ጢሞቴዎስ 3፥12)

ሰይጣን በይሁዳ ከኢየሱስ ጋር አንደተጋፈጠ በምትወደው በምትቀርበው ሰው ሊጠቀም ይችላል። በጴጥሮስ ሆኖ ከአላማው ሊያስተው እንደታገለ በማታስበው አቅጣጫ ሊመጣ ይችላለ።

ባለንበት ዘመን ሰይጣን የወንጌልን ተልዕኮ አስጥሎ ለቤተክርስቲያን የሰጣት ብዙ የቤት ሥራ አለ ። ከነዚህም በጥቂቱ መከፋፈል ፣ መገፋፋት ፣ ዘረኝነት ፣ መጠቃቀም ፣ ቡድናዊነት ፣ የቤ/ክ ውስጠ ንግድ....ወዘተርፈ ።

እግዚአብሔር ሁሉን ያያል እንመለስ ንሰሐ እንግባ ወደ መንፈሳዊው የጦርነት አውድማ እንግባ ቅድስናን ታጥቀን እርኩሰትን እንዋጋ ፣ እውነትን ታጥቀን ሐሰትን እንቃወም ፣በረከትን እርግማንን እናፍርስ ፣ አፍቃሪዎች በመሆን ጥላቻን እናስወግድ .......።

ኧረ እስቲ ልጠይቅህ ቆም በል ስማኝ እግዚአብሔር በምልልስህ በአካሔድህ በአኗኗርህ ደስ ይሰኛልን ? ስለ እግዚአብሔር ሁሉን ጥለው የወጡትን እውነተኞች እያሳደድክ ይሆን ? ወይስ የእግዚአብሔርን ሐሳብ ጥለህ ሰው ለማስደሰት እየሮጥክ ይሆን ? ከሰይጣን ከዓለም ጋር ተወዳጅተህ ልኑርበት ተውኝ ብለህ እያመቻመችክ ፣ እየተመሳሰልክ ፣ በመቻቻል ልኑር ብለህ እውነትን ደብቀህ ቀብረህ ይሆን? .......
4 viewsedited  02:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 15:13:34 እንኳን አደረሳችሁ !
" ዛሬ ... መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" (ሉቃ 2:10-11)

የእግዚአብሔር ድንቅ ስጦታ ልጁ ነው ! ስጦታው ከመሆኑም በፊት ያልነበረ ከሆነም በኃላ ያልተደገመ የከበረ ስጦታ ነው። እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ይባላል። ይህም ስጦታ ለዘላለማዊ ደህንነታችሁ አስተማማኝ ዋስትናችሁ ነው።ስጦታውን ተቀበሉ በርሱም እመኑ ዘላለማዊ ደህንነታችሁን ትጎናጸፋላችሁ !

“በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።”
— ዮሐንስ 3፥16

አሌክስ እና ቤተሰቡ
14 views12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ