Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-08-09 07:33:27
በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ በካራ ቆሬ እና በአካባቢው ለምትኖሩ ወላጆች ሁሉ እንኳን ደስ ያላችሁ !

የረጲ ቃለ ሕይወት አጸደ ሕጻናት እና አንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ - 8ኛ ክፍል) በ2014 ዓ.ም በካራ ቆሬ ከሚገኙ 12 ትምህርት ቤቶች ጋር ተወዳድሮ በወረዳ ት/ቤቶች ጽ/ቤት የዕውቅና ሰርትፊኬት እንደተሰጠው ያውቃሉ ?

እንግዲያውስ ለ2015 ዓ.ም የትምህርት ዓመት ምዝገባ የጀመርን በመሆኑ ልጆዎን ከፍተኛ የማስተማር ልምድ ባካበቱ መምህራን እጅግ ሰፋፊ በሆኑ ክፍሎች ምቹ አና ሰፊ በሆነ ግቢ ለማስተማር ለተማሪዎች ያለን ውስን ቦታ ሳያልቅቦ ፈጥነው ልጆን ያስመዝግቡ ። ልጅዎን በዕውቀት፣ በሥነ-ምግባር ፣ በአካል ብቃት እንቅስቃሴ የታነጸ ለቤተሰብ፣ ላደገበት ሕብረተሰብ እና ለሐገር የሚጠቅም ዜጋ አድርገን እንደምንቀርጽልዎ በተግባር ያያሉ !!!
27 views04:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:26:05
111 views17:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-07 20:25:58 ከዘላለም ፍርድና ሞት የሚያድንህ ከአቤል ደም ይልቅ የሚሻለውን የሚናገርው የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ብቻ ነው!

" የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።"(ዕብራ 12:24)

በቀራንዮ የፈሰሰዉ የክርስቶስ ደም፣ ከአቤል ደም ይልቅ የተሻለዉን የሚናገር ነዉ ! የአቤል ደም አትፈርድልኝም ወይ ብሎ የሚጣራና እግዚአብሔርን ለቁጣ የሚጋብዝ ደም ሲሆን የክርስቶስ ደም ግን የእግዚአብሔርን ቁጣ ያበረደና እዉነትንና ምህረትን፣ ፍርድንና ፍቅርን በማስታረቅ ሰላም ያወረደ ደም ነዉ።

እግዚአብሔር በመስቀል በክርስቶስ ላይ ቁጣዉን አፍስሶ ጨርሷል! እያደረ የሚያስታዉሰዉ ኃጢአት፣ የሚፈርደዉ ፍርድ፣ የሚቆጣዉ ቁጣ የለም ሁሉን ክርስቶስ ወስዶ ጨርሶታልና። "እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ" (ዕብራ 10 :-12)

ዓለም ከተፈጠረ ጊዜ ጀምሮ ዛሬም ድረስ ምትክ ያልተገኘለት የነፍሳችን ቤዛ፣ የድኅነታችን ዋስትና የጽድቃችን ማረጋገጫ፣ እግዚአብሔርን ያየንበት፣ እኛም ዕለት ዕለት በእግዚአብሔር ዓይን የምንታይበት የዕርቅ ማህተማችን የክርስቶስ ደም ነው። እንደ በግና እንደ ጊደር ደም ዕለት ዕለት መፍሰስ ሳያስፈልገው አንድ ጊዜ ፈሶ ለዘለዓለም ሲያድን የሚኖር ብቸኛው የጽድቅ መስዋዕት የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ደም ብቻ ነው።

የክርስቶስ ውበቱ እስከሞት ድረስ የወደደህ እውነተኛው አፍቃሪ ወዳጅህ መሆኑ ነው ። የዓለምን ውበት ከንቱ ያደረገው ይህ በቅዱስ ደም ውስጥ የጎረፈው ፍቅርና ሕይወት ነው። ሕዝብና አሕዛብን፣ ጠቢባንና ኃያላንን በፍቅር ያንበረከከው በክርስቶስ መስቀል ላይ የፈሰሰው የደም ጅረት ነው። ይህ ደም በፍቅር ኃይል ስቦ ወደ ጸጋው ዙፋን የማቅረብ ኃይል አለው።ከዚህ ደም ጋር ሕያው ፍቅር አብሮ ሲፈስ ታይቷል ፣የምህረትና የርኅራኄ ድምጽ ከደሙ ውስጥ ሲጮኽ ተሰምቷል፤ላመኑበትና ለተቀበሉት ሁሉ በዚህ የዘለዓለም የኪዳን ደም የኃጢአት ሥርየት፣ ይቅርታና ሰላም ይሆንላቸዋል ።

የሁላችንን ልብ በፍቅር የማረከ ትጥቅ አስፈትቶ ከመስቀሉ ሥር ያንበረከከን የትኛውም የጦር ኃይል ሳይሆን፤ ደም የተረጨ ፊቱ ፣በጅራፍ የተተለተለ ሰውነቱ ፣በመከራ የደቀቀ ማንነቱ፣በችንካር የቆሰሉ የእጁ መዳፋ እና እግሮቹ ፣በጦር የተዋጋ አካሉ ነው።እርሱ ስለ መተላለፋችን ቆሰለ፣ስለ በደላችን ደቀቀ፣የሁላችንን ነውር እርሱ ተሸከመ ፣ተሰቃየ፣ደከመ፣ከአመፀኞችም ጋር ተቆጠረ፣ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፣በሸላቾቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ በገመድ ተጎተተ፣በኃይል አሰሩት በፍቅር ተከተላቸው፣በግፍ ሰቀሉት በምሕረት ተመለከታቸው፣ ከብዙ ዕንባ ጋር ጸሎትና ምልጃንም አቀረበ ልጅ ስለ መሆኑም ተሰማለት።በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን።ያ ትኩስ ደም ዛሬም ስለ እኛ በአብ ፊት ይጮኻል።አንድ ጊዜ የፈሰሰው ደም ለዘለዓለም ሲያድን ይኖራል።

ስለዚህ ከደሙም የተነሳ ምህረትና ይቅርታ ከልዑል ዙፋን ላመኑትና ለተቀበሉት ሁሉ ይፈሳል።ወገኖቼ ክርስቶስ ጠጥቶ ያስቀረላችሁ የፍርድና የቁጣ ጽዋ የለም! በክርስቶስ በማመን አዲስ ፍጥረት የሆንከዉ ክርስቶስ በመስቀል የጨረሰዉን ለመድገም ሳይሆን ዉጤቱን ለመኖር ነዉ። ስለዚህ ወገኔ ፈጥነህ ሳታመነታ ማድረግ የሚገባህን ልንገርህ :-

1ኛ, ነገ የሚሆነውን አታውቅምና ጌታን ኢየሱስ
ክርስቶን ተቀበል! “ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤”
— ዮሐንስ 1፥12

2ኛ, ለመዳን ቀጠሮ የለም አሁኑኑ ንሰሐ ግባ የመዳን ቀን
ዛሬ ነውና “በተወደደ ሰዓት ሰማሁህ በመዳንም ቀን ረዳሁህ ይላልና፤ እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 6፥2

3ኛ,ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር መዳን በማንም እንደሌለ እወቅ “መዳንም በሌላ በማንም የለም፤ እንድንበት ዘንድ የሚገባን ለሰዎች የተሰጠ ስም ከሰማይ በታች ሌላ የለምና።”
— ሐዋርያት 4፥12

4ኛ, ብቸኛው መዳኛ እውነት መንገድ ሕይወት ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው “ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6

5ኛ, ከኃጢያትህ ፈጽም ሊያነጻህ የሚችል ብቸኛው ደም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ብቻ ነው ! “....የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።”
— 1ኛ ዮሐንስ 1፥7
51 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 00:17:33
24 Waaqayyo yommus aadnaa isaanii dhaga'ee, kakuu Abrahaamii fi Yisihaqiif, Yaaqoobiifis kakate in yaadate;
25 Waaqayyo akka Israa'eloonni itti jiran beekee, isaan in ilaale.
(Seera Ba'uu 2:-24-25)

Ebba kana ameen jedhiiti fudhadhu

+Waaqayyo kakuu siif keenee haa yaadatuu
+Waaqayyo Akataa atii itti jirtuu haa beekuu
+Waaqayyo si haa ilaaluu
+Waaqayyo si haa jaallatu
+mirgasaa siif haa laatu
+kan siEebba argu si haa jaallatu
+kan si dhagahu si haa simatu
+kan ati facaafte siif haa biqilu
+kan ati tuqxe haa lalisu
+firrikee sin miidhin
+kan si dhahe dabalee sin dhahin
+dhalli kee hin du'in
+gaafattee miti gafatamtee gaariin siif haa godhamu
+karaankee dhadhaan siif haa dhiqamu +barrikee, harkikee, hojiin kee kankee kan tahe hundi haa ebbifamu.
239 views21:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 07:40:40 ያለንበት የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም ተፈትኖአል !

ብዙ ጊዜ ያለንበት የመንፈሳዊ እድገት ደረጃ እንዲታይ እንዲመዘን እንዲመረመር እንዲፈተን አንፈልግም ። ምክንያቱም ያለንበትን የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም በእጃችንም በአፋችንም ሆኖ ቀረበው የቃሉ መስታወት ይታያል ።

1ኛ, ያለንበት የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም የሚለካው በቅዱስ ቃሉ ነው ! የተፈተነው ንጹህ ቃል ይፈትንሃል ፣ ይመረምርሃል ፣ ይገርዝሃል ፣ ያስተካክልሃል ።
“በምድር ላይ እንደ ተፈተነ ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ ብር የእግዚአብሔር ቃላት የነጹ ቃላት ናቸው።”
— መዝሙር 12፥6

2ኛ,ያለንበት የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም የሚመዘነው በመታዘዝ ነው ። እግዚአብሔርን እንድንወድ የታዘዝነው ከራሳችንም ከባልንጀራችንም በላይ ነው ።

" ከእነዚህም ነገሮች በኋላ እግዚአብሔር አብርሃምን ፈተነው፥ እንዲህም አለው፦ አብርሃም ሆይ። አብርሃምም፦ እነሆ፥ አለሁ አለ።የምትወደውን አንድ ልጅህን ይስሐቅን ይዘህ ወደ ሞሪያም ምድር ሂድ፤ እኔም በምነግርህ በአንድ ተራራ ላይ በዚያ መሥዋዕት አድርገህ ሠዋው አለ።" (ዘፍጥረት 22:-1 - 2)

3ኛ,ያለንበት የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም የሚመዘነው ለባልንጀራችን በሚኖረን ፍቅር ነው ።

" ባልንጀራህን ውደድ ጠላትህንም ጥላ እንደ ተባለ ሰምታችኋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የሚወዱአችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?"(ማቴዎስ 5:-43 - 46)

የጠሉንን መውድ ቀርቶ ለወደዱን እራሱ ያለን ፍቅር የማስመሰል የሽንገላ ነው ። “ማንም፦ እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥20

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደነገረን በምድር ላይ የገጠመንን የመከራ የስቃይ ውርጀብኝ አምላችንን አስከብረን ማለፍ የምንችለው ከሞት በኃላ ያለውን ዘላለማዊ ሕይወት አሻግሮ በማየት ነው ። ብድራትን ትኩር ብሎ በማየት ።

በመሆኑም ያለንበት የመንፈሳዊ እድገት አቋም ሲመዘን እምነታችን በቃሉ የተሰጠንን የከበረ ተስፋ ላይ አልተመሰረተም ይልቁንም የሚታየውን የተጨበጠውን ነው የምናምነው ።

አሁንም ያለው ስለአይን አይን ስለ ጥርስም ጥርስ በሚል የበቀል ስሜት ነው የሚነቀንቀን ። እስቲ በቃሉ መስታወት ራሳችንን እንመልከት ።ያዕቆብ 1

"ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው ይመስላል፤ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ ይረሳል።" (ያዕቆብ 1:-23-24)

ፍቅር የወንጌል ጉልበት ነው ። ክርስትና ከጌታ ፍቅር የመነጨ ሕይወት ነው ። እሰቲ እራሳችንን እንመርምር ። ጌታ ብዙዎችን ከሰይጣን እስራት አመጽ እና ክፋት ያስተፋው ።
“ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት።”
— ሉቃስ 23፥34

የሚገሉት እዳይሞቱ የሕይወት አዋጅ ፣ የሚያሰቃዩት እንዳይሰቃዩ የዕረፍት አዋጅ ፣ የሚያስሩት እንዳይታሰሩ የመፈታት አዋጅ ...ወዘተርፈ ከጀርባ የሚሰራውን የክፉ መንፈስ ተሸነፈ ስልጣኑንም ሻረ፣ የሞትን መውጊያ ሰበረ ...!

እስቲ የጥሞና ጊዜ እንውሰድ በቃሉ መስታወት ሕይወታችንን እንፈትሽ !

1ኛ, በፖለቲካ ፣ በኢኮኖሚው ፣ በዘረኝነቱ....ወዘተርፈ ሰይጣን ምን ያህል ካለንበት የመንፈሳዊ ሕይወት አቋም እንደለየን አስተውለዋልን ?

2ኛ, ጥላቻ በመስቀሉ ተገድሎ ፍቅር በቀለ የመንፈሳዊ ሰው ህይወቱ ጉልበቱ ፍቅር እና ፍቅር ብቻ አይደለምን ?

3ኛ, እግዚአብሔርን መውደዳችን እንዲገለጥ የምንወደውን ነገር ለእግዚአብሔር ለመሰዋት ምን ያህል ዝግጁ ነን ?

4ኛ, ከበቀል ከቂም ከጥላቻ ከአመጽ የነጻ ሕይወት ይዘን ምን ያህል በጸሎት እየተጋን ነው ?
6 views04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 03:57:04 የመጽሐፍ ቅዱስን ስነ - አፈታትን መረዳት(ለጥያቄ የተሰጠ ምላሽ)።

*ለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስን በግሎ ያነባሉ? ???
*የግልዎ የፅሞና ጊዜ አለዎትን ???
*ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የተቆራኘ ሕይወት እንዲኖሮት ይፈልጋሉ ???
*በቅዱሳን ሕብረት የቃሉ አገልጋይ መሆን ይፈልጋሉን ???

" የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ። በጥበብ ሁሉ እርስ በርሳችሁ አስተምሩና ገሥጹ። በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ በጸጋው በልባችሁ ለእግዚአብሔር ዘምሩ።"(ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3፥16)



የመጽሐፍ ቅዱስ ስነ - አፈታት / ስነ - ትርጓሜ / ዘዴ

1ኛ, መመልከት /Observation /

በዚህ ውስጥ
መቼ ተፃፈ? - የጊዜ አመልካች
ማን ፃፈው? - ጸሐፊውን አመልካች
ለማን ተፃፈ ?- ተደራሲያንን አመልካች
የት ተፃፈ ? - የቦታ አመልካች
እንዴት ተፃፈ? - ሁኔታን አመልካች
ለምን ተፃፈ? - ምክንያትን አመልካች
*ማን? ተናጋሪው ማነው? የሚነገርለትስ?
*ምን? ርዕሱ ምንድነው ቅደም ተከተሉስ?
*የት? ድርጊቱ እየተከናወነ ያለው የት ነው?
*መቼ? ድርጊቱ የተፈፀመው መቼ ነው?
* እንዴት? የተደረሲያን ምላሽ እንዴት ነበር?



2ኛ, መተርጎም / Interpretation /

*በምልከታው ያገኘነውን ሙሉ መረጃ መሠረት በማድረግ ወደ ትርጉም እንገባለን ። የመተርጎም ዓላማ በዘመኑ ለተጻፈላቸው ተደራሲያን ሊተላለፍ የተፈለገውን ትክክለኛ መልዕክት ማግኘት ነው። በመሆኑም በመተርጎም ሒደት የምንጠይቃቸው ቁልፍ ጥያቄዎች :-
* በምልከታው ቁልፍ ጥያቄዎች የተረዳሁት ምንድነው?
* ያነበብኩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ስለምንድነው የሚናገረው?
*በክፍሉ ትኩረት የተሰጠው ነገር ምንድነው?
*በዘመኑ የተጻፈላቸው ሰዎች ያሉበት ሁኔታ ምን ይመሥላል?
*የተላለፈላቸው መልዕክት እንዴት ተቀበሉት?
*ተደራሲያኑ ለመልዕክቱ የሰጡት ምላሽ ምን ነበር?
*በመታዘዛቸው ያገኛቸው በረከት ምንድነው?
* ባለመታዘዛቸውስ ምን አጋጠማቸው?
*ይህ ክፍል የተጻፈበት ዓላማ ወይም ምክንያት ምንድነው?
*በክፍሉ እግዚአብሔር ለተደራሲያኑ ሊናገር የፈለገው ዋና መልዕክት ምንድነው?



3ኛ,ማዛመድ /Application /

* በትርጉም ውስጥ ያገኘነውን መልዕክት በመያዝ በማዛመድ ሒደት ልንጠይቃቸው የሚገቡንን ቁልፍ ጥያቄዎች ።
*መልዕክቱ ከህይወቴ ጋር ምን ግኑኝነት አለው?
* መልዕክቱ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ያዘኛል?
* በመልዕክቱ የተሰጠኝ ተስፋ ምንድነው?
*መልዕክቱ አሁን ካለሁበት ሁኔታ አንጻር ለኔ ምን መልዕክት አለው?
* በክፍሉ ልርቀው ወይም ልከተለው የሚገባኝ ምሳሌ ምንድነው?
* በክፍሉ የተሰጠኝ የተስፋ ቃል የሚጠይቀው ቅድመ ሁኔታ አለ ወይ?
* በክፍሉ መታዘዝ/አለመታዘዝ/በሕይወቴ ሊያስከትለው የሚችለው ውጤት ምንድነው?
*መንፈስ ቅዱስ በተረዳሁት መልዕክት መሠረት የሚሰጠኝ አመራር ምንድነው?
*ያነበብኩት የመጽሐፍ ክፍል የተረዳሁት መልዕክ ከግል ህይወቴ ከቤተሠብ ከቤተ ክርስርስቲያን ከአገር አንጻር ምን የሚሰጠኝ መልዕክት አለ? እንዴትስ ሊዛመድ ይችላል?



በዘመኑ ካለው ስህት ለመጠበቅ አውዳዊ እና ትክክለኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ አተረጓጎም ይማሩ ያኔ አሳውን ሰው እያጠመደ ከሚያበላዎ ለራስዎ አጥምደው መብላት ይጀምራሉ !!!
16 views00:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 03:39:59 “በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፥ በማለዳ በፊትህ እቆማለሁ፥ እጠብቃለሁም።” መዝ 5፥3

1. ማለዳ ጸሎትን ሰምቶ በሚመልሰው አባታችን እና አምላካችን ፊት በመቅረብ የሰጠን ቀን እርሱ በአመራሩ እንዲረከብ ያእርሱ ምንም መሆንም ማድረግም እንደማችል እኛ በእርሱ ላይ ጥገኞች መሆናችንን የምንገልጽበት ጊዜ ነው።

2. ማለዳ በአብዛኛው ተኝተን (አርፈን) በታደሰ አእምሮና ጉልበት የምንነሳበት የቀኑ የመጀመሪያ ክፍል ነው። ስለዚህም ማለዳ አእምሮአችን በዕለቱ የሕይወት ውጣ ውረድ እና ትግል ውስጥ ከመግባቱ በፊት ለእግዚአብሔር የጊዜዓችንን በኩራት የምናቀርብበት ስለ ተጨመረልን እድሜ የምናመሰግንበት ጊዜ ነው።

3. ማለዳ እያንዳንዱ ቀን የየራሱ ክፋት ፣ ትግል እና ፈተና አለውና ሊመጣ ያለውን ፈተና የምናሸንፍበትን ለቀኑ የሚያስፈልገንን ጸጋ ከእግዚአብሔር የምንጠይቅበት ብቃት ጠይቀን የምንታጠቅበት ጊዜ ነው።

4. ማለዳ ከመጽሐፍ ቅዱስ ሕያው ገበታ የቃሉን ቁርስ የምንቆርስበት /የምናነብበት/ ጊዜ ነው ።

አቤቱ እንድናስተውል እርዳን!!
17 views00:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:13:07
እግዚአብሔር ሆይ በምህረትህ አስበን !
47 views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 11:06:55
46 views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 07:25:16
207 views04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ