Get Mystery Box with random crypto!

የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )

የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የቴሌግራም ቻናል አርማ alexkhc — የእግዚአብሔር ቃል በሙላት ይኑርባችሁ (pastor Alemayehu Abebe )
የሰርጥ አድራሻ: @alexkhc
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 184

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-10-14 05:04:51 https://www.facebook.com/100064101580250/videos/1265764847598547/
93 views02:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-14 04:30:58 በመንፈሳዊው ጦርነት አሸንፈሃል !

እኛ በመንፈሳዊው ጦርነት የእግዚአብሔር ጦርነት የምንዋጋው ለማሸነፍ ሳይሆን በክርስቶስ የመስቀል ላይ ስራ ከተሸነፈው ጠላት ምርኮ ለመበዝበዝ ነው ። ጠላት ዲያቢሎስ በጌታ በኢየሱስ የመስቀል ስራ ሙሉ በሙሉ ድል የተደረገ በመሆኑ የተያያዝነው መንፈሳዊ ውጊያ የተሰጠንን ድል የምናስቀጥልበት ነው።

1ኛ, የዲያብሎስ ሥራ ፈርሶአል !
“ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። ”
— 1ኛ ዮሐንስ 3፥9
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያላጠናቀቀው መንፈሳዊ ጦርነት የለም ። ሰይጣን ተሸንፎአል ።

2ኛ,ጉልበት ሁሉ ለጌታ ይንበረከካል

“እኔ ሕያው ነኝ፥ ይላል ጌታ፥ ጉልበት ሁሉ ለእኔ ይንበረከካል መላስም ሁሉ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ተብሎ ተጽፎአልና።”
— ሮሜ 14፥11
በተሸነፈ በተዋረደ ጠላት ላይ ገልጦኃል ። በድል ነሺው ስም እንድታዘው እንድታስረው የያዘውን ሁሉ እንድታስለቅቅ ተልከሃል ።

3ኛ, በመናፍስት ሁሉ ላይ ስልጣን ተሰጥቶአችኃል!

“እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም።”
— ሉቃስ 10፥19
ሥልጣን የተሰጠህ ጠላት ሰይጠንን እንዳይነሳ አድርጎ ከዙፋኑ በገለበጠው ጌታ ነው ። በመናፍስት ኃይላት ላይ ሁሉ ሙሉ ስልጣን አለህ ። አንተ እኮ የእግዚአብሔ ልጅ ነህ።

4ኛ, ባንተ ካለው እና ሰይጣንን ዓለምን የኃጢያትን ኃይል እሸንፎ ከሰጠህ ጌታ የተነሳ አሸንፈሐል !

“ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።”
— 1ኛ ዮሐንስ 4፥4
እንኳን የክብሩን እና የመለኮቱን ኃይል ለብሰህ ቆመህ ዝለህም ፣ወድቀህም፣ ደክመህም ፣ አሸናፊ ተደርገሃል።
ሞት ተሸንፎአል መውጊያው ተሰብሯል ፣አለም ተሸንፎአል ፣ ኃጢያት ተሸንፎአል ።
28 views01:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 03:49:58
15 views00:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 03:18:09 በእስራኤላውያን ዘንድ ሐገራቸው በገባችበት ጉዳይ የመጀመሪያውን ኃላፊነት የሚወጡት መንፈሳዊ አባቶች ካህናት መሪዎች ናቸው::ሐገር ወደ ጦርነት ስትገባ፣ ችግር ሲያጋጥማቸው፣ ሀገራቸው እረሀብና ቸነፈር ሲያጥማት… ወዘተርፈ ታቦቱ አና ካህናቱ ፊት ለፊት ይቀድሙ ነበር :: ይህ በእግዚአብሔር ኃይል የመጣባቸውን አስቸጋሪ ነገር ሁሉ ተጋፍጦ ድል መንሳት ያስችላቸው ነበር :: (ዘጸአት14:-13,ኢያሱ3::-15) ከዚያም ጠላት በባህር ሰጠመ !እስራኤል በደረቅ ምድር ተሻገሩ ! እየተባለ ይዘመራል። እንግዲህ ወገኔ ሆይ የነህሚያም አምላክ ያንተም አምላክ ነውና። ከፖለለቲካው ይልቅ ወደ ከበረው ዘላለማዊ አውነት፣ ከዘረኝነቱ ይልቅ ወደ የሰው ልጆች ሁሉ ሰላም፣ ከተራ አሉባልታ ከአክቲቪስቱ ወሬ ይልቅ ወደ ቅዱስ ቃሉ ፊታችሁን መልሱ ለኢትዮጵያ እና ለሕዝቧ ሁሉ ሰላም ይሁን ! ተባረኩልኝ !
15 views00:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 03:18:09 ከራስሕ በላይ ለሆነ ዓላማ ኑር !

“ይህንም ቃል በሰማሁ ጊዜ ተቀምጬ አለቀስሁ፥ አያሌ ቀንም አዝን ነበር፤ በሰማይም አምላክ ፊት እጾምና እጸልይ ነበር፥”
— ነሀምያ 1፥4

" በንጉሡ በአርጤክስስ በሀያኛው ዓመት በኒሳን ወር የወይን ጠጅ በፊቱ በነበረ ጊዜ ጠጁን አንሥቼ ለንጉሡ ሰጠሁት። ቀድሞ ግን በፊቱ ያለ ኃዘን እኖር ነበር። ንጉሡም። ሳትታመም ፊትህ ለምን አዘነ? ይህ የልብ ኅዘን ነው እንጂ ሌላ ነገር አይደለም አለኝ። እጅግም ብዙ አድርጌ ፈራሁ።"( ነህምያ 2:-1-2)

ነህሚያ በምዕራፍ አንድ እንደ ተመለከትነው የኢየሩሳሌምን ቅጥር መፍረስ ፣ የበሮቿን መቃጠል፣ የሕዝቡን የጠላት መሳለቂያ መሆን፣ ሰምቶ ተቀምጦ ማልቀሱ ፣ ክፉኛ ማዘኑ የአባቶችን የመሪዎችን ኃጢያት እየተናዘዘ ንሰሐ መግባቱ ፣ መጾሙ መጸለዩ አልበቃውም::
ስለሐገሩ ፣ስለ ህዝቡ ፣ስለ እግዚአብሔር መቅደስ ፣ የመቅደሱ ቅጥር መፍረሱ እና ሕዝቡና መቅደሱ ለጠላት መሳለቂያ መሆኑን እየሰማ ያለው ውስጣዊ የልብ ሸክም ለራሱ ምንም በቤተመንግስት፣ በተድላና በምቾት እየኖረ ያለ ቢሆንም ሰላም እረፍት ምቾት ሊኖረው አልቻለም።

በርሱ ያለው መለኮታዊ ጥሪ እና ሸክም ምቾት ሊሠጠው አልቻለም:: በጣም ተጨንቀ ፣ ተበሳጨ ነገሩ እረፍት ነስቶት ነበር።ከቀን ወደ ቀን ሥለ ምድሩ ያለው ቅናትና ሸክም የውስጥ ሐዘን ነጸብራቁ ከውስጥ ወደ ውጭ ወጥቶ በፊቱ ላይ ተገልጦ ለሁሉ እስኪታይ ደረሰ ሆነ :: ይህንን እውነት ነህሚያን ያየ ሁሉ ሊረዳው ይችላል ::

የኢሩሳሌም የቅጥር ግንብ መፍረስና ስለ የበሮቿ መቃጠል ከሰማበት ጊዚ ይልቅ የበለጠ ከኅዘኑ፣ከጾም፣ ጸሎቱ፣ ከለቅሶው
አልፎ ለዚህ ጉዳይ እራሱን ለመስጠት አስወሰነው :: ነህሚያ ከንጉሱ ፊት መሰወር የማያስችለው ሥራ ስለነበረው ከንጉሱ ሊሸሽግ ወደማይችልበት ሁኔታ ውስጥ ገባ:: ይህም ሆኖ አገልግሎቱን አለቋረጠም ። ነገር ግን ያለበት ሁኔታ ከወትሮው በተለየ መልኩ ፊቱ አዝኖ፣ ጠቁሮ ስለነበር ንጉሱ የነህሚያ ሁኔታ ያልተለመደና ሁሌ የሚያውቀውን ፈገግታ ደስታ ከነህሚያ ፊት ላይ በማጣቱ "ሳትታመም ፊትህ ለምን አዘነ?"ብሎ የነህሚያን የውስጥ ሀዘን በቀጥታ ወደ ውጭ አውጥቶ ላዘነበተ ጉዳይ ለስብራቱ ምክንያት ጠየቀው :: እርሱም መልሶ:-" ንጉሡንም። ንጉሡ ሺህ ዓመት ይንገሥ፤ የአባቶቼ መቃብር ያለባት ከተማ ተፈትታለችና፥ በሮችዋም በእሳት ተቃጥለዋልና ፊቴ ስለ ምን አይዘን? አልሁት።"ይለናል ( ነህምያ 2:3)

ታድያ የነህሚያ በሀገሩና በሕዝቡ ጉዳይ እንዲህ መሆኑና ከንጉሱ መልስ ያገኝበት ዋናው ምክንያት ከእየሩሳሊም የመጡ ሰዎች የሀገሩንና የህዝቡን ሁኔታ ሲጠይቃቸው:-
ሕዝቡ በታላቅ መከራና ስድብ አሉ !
የእየሩሳሊምም ቅጥር ፈርሶአል !
በሮችም በእሳት ተቃጥለዋል !
የሚለውን ሲሰማ የወሰደው እርምጃ በቀጥታ በእግዚአብሔር ፊት እራሱን ማዋረድ ነበር እርሱ እንደተናገረ " ይህንም ቃል በሰማሁ ጊዜ ተቀምጬ አለቀስሁ፥ አያሌ ቀንም አዝን ነበር፤ በሰማይም አምላክ ፊት እጾምና እጸልይ ነበር፥"( ነህምያ 1:4)

እንዴት ያስደንቃል ወገኖቼ ነህሚያ በስደት በነበረበት ሀገር የሀገሩና የሕዝቡ ጉዳይ አይቶ ሳይሆን ሰምቶ የራሱን የንጉስ ቤት ኑሮ ጠልቶ በልቡ ካለው ውስጣዊ ሸክም የሀገሩንና ህዝቡን ለመታደግ ፣ጭንቀታቸውና ሊጨነቅ፣ መከራቸውን ሊካፈል፣ሐዘናቸውን ሊያዝን፣ እራሱን ለሐገሩ፣ለሕዝቡ፣ ለእግዚአብሔር ክብር አሳልፎ ሰጠ !

ለምን ዓላማ ቢባል ንቀት ስድብና መከራን ከሕዝቡ ሊያርቅ የፈረሰውን ሊገነባ ራሱን አሳልፎ ሰጠ ። መታገስ አልቻለም በሀሳቡ በገንዘቡ ብቻ ሳይሆን በአካልም ማንነቱን አሳልፎ ሰጠ :: " ንጉሡንም። ንጉሡን ደስ ቢያሰኝህ፥ ባሪያህም በፊትህ ሞገስ ቢያገኝ፥ እሠራው ዘንድ ወደ ይሁዳ ወደ አባቶቼ መቃብር ከተማ ስደደኝ አልሁት። "አለ( ነህምያ 2:5) ነህሚያ ከራሱ
ይልቅ የምድሩ የሕዝቡ የእግዚአብሔር መቅደስ ያለባት ከተማ ጉዳይ የሚገደው ሰው ነው። ነህሚያ በእግዚአብሔር ትልቅ እምነትና ተስፋ ይዞ ወደ እግዚአብሔር ያደረገው ፀሎትና ፆም ሀገሩንና ህዝቡን ለመታደግ አብቅቶታል።

በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም የምትኖሩ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች ሆይ ስለ ኢትዮጵያ ስለ ሕዝባችሁ ስለ እግዚአብሔር ቤት :-
ስለምድራችሁ የምታስቡት ምንድነው ?
ወገኖቼ ሆይ ከነህሚያ ሕይወትስ ምን ትማራላችሁ?
እግዚአብሔር ከአንድ ሀገር ሕዝብ ሲፈጥርህ ዓላማ አለው የዛ ሀገር ችግር የመፍትሄ ምክንያት ሊያደርግህ አይደለምን ?

ነህሚያ ከራሱ ባለፈ የሚኖርበት ዓላማ እንዳለው የተገነዘበ ሰው ነው::ለራሱማ በምርኮ አገር ያለ እስራኤላዊና በንጉስ ቤት በምቾት እና በተድላ የሚኖር ሰው ነው:: ነገር ግን ነህሚያ ወገኑ እየተራበ የራሱን ጥጋብ ፣ወገኑ እየተዋረ የራሱን ክብር ፣ወገኑ የጠላት መሳለቂያ እየሆነ የራሱን ምቾት፣ ወገኑ እየተሰቃየ የራሱን ተድላ ወዘተርፈ አልፈለገም ::

ሀገሩና ህዝቡን የእግዚአብሔር መቅደስ ከተማ የሆነችውን ኢየሩሳሌምን በልቡ ትሸክሞ በአምላኩ ፊት ወደቀ:: ከምንም በላይ በእግዚአብሔር ቃል ስለሀገሩ የተነገረውን የተስፋ ቃል ጠንቅቆ የሚያውቅ ስለነበር በሀገሩ ላይ በደረሰው ሁኔታ እንደ ተስፋው ቃል ወደ አምላኩ በመጮኸ ለሀገሩ የቃተተ እና መፍትሄ ያመጣ ሰው ነው።
ለኛስ እግዚአብሔር ስለሐገራችን ኢትዮጵያ የሰጠን የተስፋ ቃል ምንድነው? እግዚአብሔር የኢትዮጵያን ጉዳይ በኔና ባንተ እጅ ላይ አላስቀመጠምን ? የሰው ልጅ ሲሞት ሲጎዳ ፣ሲራብ፣ ሲጠማ ፣ሲሰቃይ ፣ሲፈናቀል ዝም ልንል ይገባልን ?
ከማስለቀስ ይልቅ እንባ አባሽ እንድንሆን ስለፍትህ ስለእውነት ስለጽድቅ አትሟገትምን ?
ስለ ሰላሟ ስለአንድነቷ አትጾምም አትጸልይምን ?
በእግዚአብሔር መልክና አምሳል የተፈጠረውን የሰው ልጅ ሁሉ በፍቅር እንድንከባከብ፣ ካለን እንድናካፍል ፣
ለኛ እንዲሆንልን የምንፈልገውን ሁሉ እንድናደርግለት አይገባንምን ?
ከነህምያ ሕይወት እና አገልግሎት የምንማረው ምንድነው ?
እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን ሁሉ ማድረግ ይኖርብናል በዚህ ምድር እርሱ ደስ የሚሰኝበትን እውነት ከማከናወን ያለፈ አገልግሎት ምን አለ ?

የእግዚአብሔር ፈቃድ ሕያው ድምጹ ቅዱስ ቃሉ ነው። ነህሚያ ወደ እግዚአብሔር የፀለየው እንደ ቃሉ ነበር እግዚአብሔር በሰጠው የተስፋ ቃል ላይ በመመስረት በእግዚአብሔር ፊት ስለሕዝቡ ስለምድሩ አጥብቆ ጸለየ እግዚአብሔርም ሰማው ።
1ኛ, ወገኖቼ ስለምድራችን በእውነተኛ ልባዊ ሸክም እንጹም እንጸልይ !
2ኛ, ነህምያ አገሩን እንደ አንድ ሐገር ሕዝቡንም እንደ አንድ ሕዝብ ለእግዚአብሔር አሳልፎ እንደሰጠ ከዘረኝነት በመውጣት አገራችንን ለእግዚአብሔር አሳልፈን እንስጥ ።
3ኛ, ለአገራችን ሰላም የራሳችንን ድርሻ እንወጣ ያኔ እግዚአብሔርን በቃሉና በፈቃዱ ላይ እናገናኘዋለን።

እንግዲህ እውነቱ በውጭ ሆነ በአገር ውስጥ ያለ ኢትዮጵያዊ፣ዲያስፖራው፣ ፓትሪያሪኩ፣ ፓስተሩ ፣ ሽማግሌው፣ነብዮ፣ ካህኑ፣ ቄሱ፣ ቢሾፑ ፣ አስተማሪው ፣ ወንጌላዊው፣ ሐዋሪያው በዚህ ጊዜ በምድሪቱ ላይ ከሚሆነው ነገር ኃላፊነት መሸሽ አይችሉም:: የእግዚአብሔርን ፈቃድ የማድረጉን የመጀመሪያ ኃላፊነት መውሰድ ይኖርባቸዋልና::
15 views00:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-30 07:02:02 ከቂመኛነት እና ከበቀለኛነት አርነት የወጣ ሕይወት አምልኮ !

"እንግዲህ መባህን በመሠዊያው ላይ ብታቀርብ፥ በዚያም ወንድምህ አንዳች በአንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፥
በዚያ በመሠዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፥ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።"(ማቴዎስ 5:-23 -24)

ብዙ ሰዎች የተደረገባቸውን መቁጠር ፣ በደልን መቁጠር ማቄም ዛቻ ለጎዳቸው ሰው የሚመልሱትን የበቀል መጠን ማሰብ ፣ የስብራታቸውን መጠን ለሰው ማሳየት ቂም መያዝ ሌት ተቀን ስለዛ ማሰብ ማውጣት ማውረድ መብታቸው እንደሆነ በማሰብ ቀኑን ይጠብቅ እያሉ ሒሳብ የሚያወራርዱበትን ጊዜ እና ሰዓት ወስነው ይጠባበቃሉ ።

በዚህ ጊዜ የቂም በቀል እሳት ነው በውስጣቸው የሚነደው
ለበቀል ጊዜያቸውን ፣ ጉልበታቸውን ፣ አዕምሮአቸውን ፣ ሁለንተናቸውን አሳልፈው በመስጠት ቀኑን ይጠብቅ ፣ እሰራለታለሁ እኔ ወንድ አይደለሁማ እያሉ ሲዝቱ ሲፎክሩ ማየት የተለመደ ነው ። ጉዳታቸውን በማሰብ ቂም ለመያዝ ለበቀል መብት እንዳላቸው ያስባሉ።ቃሉ ግን “አትበቀልም፥ በሕዝብህም ልጆች ቂም አትያዝ፥ ነገር ግን ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ፤ እኔ እግዚአብሔር ነኝ።”( ዘሌ 19፥18)
ይለናል ።

የሚገርመው ነገር ግን በእግዚአብሔር ቃል እንደተገለጠውም ሆነ በሳይንስ እንደተረጋገጠው ቂም ከተያዘበት ሰው ይልቅ ቂመኛው ሰው ራሱን ለመንፈሳዊ ወድቀት ፣ ለሞራል ድቀት ተጋልጦ እረፍት በማጣት በመቅበዝበዝ በስቃይ የሚኖር ይሆናል ።ለዚህ ነው ዳዊት “ወደ ደም እንዳልሄድ፥ በእጄም በቀል እንዳላደርግ ዛሬ የከለከለኝ አእምሮሽ የተመሰገነ ይሁን፥ አንቺም የተመሰገንሽ ሁኚ።” ( 1ኛ ሳሙኤል 25፥33)

የእግዚአብሔር ቃል እንድንበቀል አይፈቅድም ለዚህ ነው
“ተወዳጆች ሆይ፥ ራሳችሁ አትበቀሉ፥ ለቍጣው ፈንታ ስጡ እንጂ፤ በቀል የእኔ ነው፥ እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ ይላል ጌታ ተብሎ ተጽፎአልና።” (ሮሜ 12፥19)

ለፈውሳችን ፣ለሰላማችን ፣ለደስታ ፣ለእርካታችን፣ ለተሳካ መንፈሳዊ ሕይወት አና ጉዞ በይቅርታ ልብ ልንሞላ ይገባል ። “ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት።”
( ሉቃስ 23፥34)

ሰው ሰውን የሚበድለው በተለያየ ምክንያት ነው :-
ባለማወቅ፣ አውቆም ፣ የተሻለ ሕይወት ሊኖር እንደሚችል በማሰብ ወዘተርፈ ሰው የሰራውን በደል በምንም መንገድ ይስራው እኛ ግን የይቅርታ ልብ ሊኖረን ይገባል ። ጥሪያችንም ክፉን በክፉ ማሸነፍ ሳይሆን ክፉን በመልካም ማሸነፍ ነውና ።

1ኛ, ይቅርታ ማድረግ አለመቻል በትናንት ቂም በቀል ታስሮ ዛሬን እንዳንኖር ለኛ ወደተወሰነው የበረከት ሕይወት እንዳንዘረጋ ያደርጋል።"...በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ ..."(ፊልጵ 3፥13 )

2ኛ, ይቅርታ አለማለት ከእግዚአብሔር የሚለይ፣ አምልኮን የሚከለክል፣ እኛም ከእግዚአብሔር ምህረት አንዳናገኝ በር የሚዘጋ ነው።“እኛም ደግሞ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን፤”( ማቴ 6፥12)

3ኛ, ይቅር አለማለት እግዚአብሔር በቀላችንን እዳይበቀል መከልከል ነው ።"...በቀል የእኔ ነው፥..."(ሮሜ 12:19)

4ኛ, ይቅር ባይ ስትሆን አምልኮህ ፣ መባህ ፣ ለእግዚአብሔር ክብር የምታደርገው ሁሉ በርሱ ፊት ተቀባይነት
ይኖረዋል። መልካም የመዓዛ ሽታ ያለው መሰዋዕት ይሆናል ።

"እንግዲህ መባህን በመሠዊያው ላይ ብታቀርብ፥ በዚያም ወንድምህ አንዳች በአንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፥
በዚያ በመሠዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፥ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።"(ማቴዎስ 5:-23 -24)
25 viewsedited  04:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-29 04:47:13 በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻ አውጥቶናል !

“በነጻነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻነት አወጣን፤ እንግዲህ ጸንታችሁ ቁሙ እንደ ገናም በባርነት ቀንበር አትያዙ።”
— ገላትያ 5፥1
ነጻ የወጣነው ቀድሞ ከተያዝንበት የኃጢያት ባርነት ፣ ከዘር ተወራርሶ ከመጣው ክፉ የመንፈስ አሰራር ቀንበር ፣ አውቀንም ሳናውቅም ከተጫነብን እርግማን ቀነበርም ነው ።

በመናፍስቱ ዓለም አርነት በወጣንበት በክርስቶስ የነጻነት መንፈስ እንድንመላለስ ጠላት አይፈልግም። በቀድሞው አለማዊ ልምምድ እና መንፈሳዊ አሰራር የታሰረ ሰው ደግሞ በእግዚአብሔር ወደተዘረጋለት የከበረ መንፈሳዊ ደረጃ መድረስ አይችልም ። በፊቱ ወዳለው ክብር እንዳይዘረጋ አዕምሮው ሙሉ በሙሉ በቀድሞው ጉዳይ ጠላት ሰይጣን የቀድሞውን ቂም፣ በቀል ፣ጉዳት፣ መገፋት፣ ስቃዩን...ወዘተ በማሰብ ታስሮ እንዲኖር እና የይቅርታ፣ የእርቅ ፣የፍቅር፣ የመተው ሕይወት እንዳይኖረው በማድረግ በበደል ቆጣሪነት ታሥሮ እንዲኖር ያደርገዋል።

ከዚህ የተነሳ በክርስቶስ ያገኘውን የነጻነት ሕይወት እንዳይለማመድ ፣ በመዳኑ ሐሴት እንዳያደርግ ፣ በምሬት እና በማጉረምረም እንዲኖር ያደርገዋል። ስለዚህ ሰዎች በክርስቶስ ባገኙት አርነት ለመገኘት ከመናፍስት አሰራር ፣ ከዓለማዊነት ፣ ከክፉ ሰዎች ተጽኖ ፣ ከኃጢያት እስራት ፣ ከቀድሞ ክፉ ሥራቸው ወቀሳ ...ወዘተ ነጻ መውጣት እና መፈታት ይኖርባቸዋል።

ይህ ደግሞ ቀድሞ ከተሰራው በደልእና ኃጢያት በንሰሐ ፣ ከተጣሉት ሰው ጋር በይቅርታ ፣ የሚጠሉት ያ ሰው ምንም ያህል የበደላቸው፣ ያሰቃያቸው ፣ያንገላታቸው ቢሆን ለዛ ሰው ቀርቦ መልካም በማድረግ እና በተግባር ፍቅርን በስጦታ በመግለጽ የአዕምሮን ጠባሳ መሻር ይገባል ።

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚገሉት ሕይወትን ፣ ለሚጥሉት መነሳትን፣ ለሚያስሩት መፈታትን ፣ ለሚያቆስሉት መፈወስን ፣ ለሚያሰቃዩት እረፍትን ፣ ለነፍሰ ገዳዮች ምህረት ማግኘት ማለደ እኛም የተጠራነው ለዚሁ ነው ። “የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።”
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥21

እንዲህ ብለን አንጸልይ እግዚአብሔር ሆይ አሁን ባለኝ እና ወደፊትም በሚኖረኝ የሕይወት ላይ የክፉ መንፈስ አሰራር በምንም መልኩ እድል ፈንታ እና ተጽኖ እንዲኖረው አልሻም ። ያለፈው የበደል እስራት የእርግማን ቀንበር መጥፎ አሳዛኝ ትዝታ ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተቆረጠ ይሁን ።ጌታ ሆይ የጠሉኝን ልወ፣ የጣሉኝን ላነሳ፣ የገፉኝን ላቀርብ፣ የተጣሉኝን ልታረቅ፣ የበደል እስራትን ልፈታ፣ የረገሙኝን ልመርቅ እና ያሳደዱኝን ልቀበል....ወዘተርፈ ቃል እገባሁ አቤቱ የሚረዳኝ ጸጋ ይሰጠኝ ! በበረከትና በነጻነት እንዳልኖር ከቀድሞ ዘመን ተከትሎኝ የመጣ ምንም ነገር በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተቆረጠ ይሁን ! አሜን! አሜን! አሜን !

1ኛ, ወደ ታቀደላችሁ የነጻነት ክብር ለመዘርጋት ወስኑ ።
2ኛ, ተከታትሎ የመጣውን ቂም ጥላቻ በተግባራዊ ምላሽ
በእርቅ በይቅርታ ፍቱ ።
3ኛ,የክፉ መናፍስትን ተጽኖ የቀድሞውን ቀንበር ስበሩት ።
የጠላት ዓላማ በእግዚአብሔር ወደ ተዘጋጀላችሁ ክብር
እንዳትሻገሩ መያዣው ነውና ።
4ኛ, በክርስቶስ የተገኘውን ነጻነት በሕይወታችሁ ፣
በኑሮአችሁ በአገልግሎታችሁ በትውልዳችሁ
ላይ አውጁት ።
3 views01:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-28 09:20:25 አንድ ሊባል የሚገባው ጉዳይ !

¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
"በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር።ወዮ ለዓለም ስለ ማሰናከያ፤ ማሰናከያ ሳይመጣ አይቀርምና፥ ነገር ግን በእርሱ ጠንቅ ማሰናከያ ለሚመጣበት #ለዚያ #ሰው #ወዮለት።"(ማቴዎስ 18:- 6-7)

ቤተ ክርስቲያንን በቃሉ መርህ መሠረት መምራት ተገቢ ነው ። መሪዎች የመሪነትን ኃላፊነት የሚቀበሉት ከተጠያቂነት ጋር ነው ። “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
— ሐዋርያት 20፥28

እየሳቱ ለሚያስቱ በአብያተ ክርስቲያንም ሆነ በካውንስሉ እየተሰጠ ያለ ማስጠንቀቂያ፣ ውግዘት፣ተግሳጽ ፣ ከመንጋው መካከል ለይቶ የማስወጣት ሥራ አይታይም ። ከዚህ የተነሳ ብዙ ነብያት ነን ባዮች ፣ ፓስተሮች ነን ባዮች፣ ሐዋርያ ነን ባዮች......ወዘተርፈ መንጋውን ሲያንላቱ ያልሆነ አስተምለህሮ ሲያሰራጩ ምንም የሚሰማው ፣የሚገስጽ ፣የሚመክር፣ ሸክም የሚሰማው መሪ አለመኖሩ በእጅጉ አሳዛኝ ነገር ነው ።
ሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን እንድትጠበቅ አዘዋል። ምክንያቱንም ሲገልጹ :-“....ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ።”
— ሐዋርያት 20፥29-30
ከእውነት ርቆ የራስ ጎራ ፈጥሮ አንድ የሆነውን የክርስቶስ አካል (ቤተ ክርስቲያን) በሰው ብለሃት በተፈጠረ ተረት ከፋፍሎ ሲጓዙ እየታየ ዝም መባሉ ለምን ይሆን? በእግዚአብሔር በቤተክርስቲያን በትምህርት ላይ የፈለጉትን ሲያደርጉ ዝም መባሉስ ለምን የሚለው ጥያቄ የሁሉም ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ አዕማድ ሆኖ የሚታየውን ኬፋን (ጴጥሮስን ) ፊት ለፊት ተቃወምኩት ያለው ከወንጌል እውነት አፈንግጦ ስላገኘው ነው ።

በየሚዲያው በእግዚአብሔር ላይ ፣ በቤተክርስቲያን ላይ ... በአስተምሮዋ ላይ የሚታየውን ዘመቻ አደብ ማስያዝ የሚችል ወሳኝ አካል መኖር አለበት ። እንደፈለጉ የሚፋንኑ አንድ ሊባሉ ይገባል።አብያተ ክርስቲያንም ሆነ ካውንስሉ የወንጌልን እውነት ተጠብቆ ቤ/ክ ጤናማ አስተምህሮ ይዛ እንድትጓዝ በማድረግ ከውጪ የሚመጣባትን የሐሰት ትምህርቶችና ልምምዶች ለመቋቋም ጥረት ካላደረገ በየአመት በአላት በየመድረኩ ብቻ ብቅ ብሎ ንግግር ለማድረግ ብቻ የተቀመጠ ከሆነ ልዩነቱ ምንድነው ?

በየሚዲያው የአብያተክርስቲያን አካል ነኝ በሚሉ ግለሰቦች የእግዚአብሔር ስም ሲነካ ፣ አስተምህሮው ሲያዛባ ፣ ስተው ሲያስቱ ዝም ሊባሉ ይገባል ብዬም አላምንም ። ሁላችንም ከቃሉ ድንበር ባላፈነገጠ እውነት መታቀፍ ይኖርብናል ።
ቤተክርስቲያንን መጠበቅ (የተዋጀውን መንጋ መጠበቅ) ፣መንፈሳዊ አንድነትን መጠበቅ የቃሉን መርህ ጠብቆ መጓዝ ይገባል።

እግዚአብሔርን የሚወዱ እውነተኛ ቅዱሳን የሆናችሁ ሁሉ ለእውነተኛው የወንጌል እውነት በመቆም በአንድ ልብ ሆነን ስተው የሚያስቱትን፣ ተሰናክለው የሚያሰናክሉትን የወንጌልን እውነት ለመበረዝ የሚሯሯጡትን አንድ ልንላቸው ይገባል ። ወዳሻቸው ሊነዱን ሊያስቱን ለሚሹ ቆም በሉ ልንላቸው ይገባል ።

ብዙ አሳፋሪ አሳዛኝ ነገር እያየን ነው በፈውስ ጸሎት ስም ገንዘብ መሰብሰብ “ድውዮችን ፈውሱ፤ ሙታንን አስነሡ፤ ለምጻሞችን አንጹ፤ አጋንንትን አውጡ፤ በከንቱ ተቀበላችሁ፥ በከንቱ ስጡ።”(ማቴዎስ 10፥8) ከእግዚአብሔር ጋር መቧቀስ ፣ ታቦቱ በኢትዮጵያ ነው የተቀጣነው እርሱን ባለማክበራችን ነው ፣ ማርያም ታማልዳለች ከሞት ተነስታለች የሚለው ፓስተር ሌላም ሌላም ወዘተርፈ ሊወገዙ ሊገሰጹ ይገባል ብዬ አምናለው ። ነገ በሌለው አገር እንደምናየው መንጋውን ሳር የሚያስበላ ፣ አገልጋዩን በሸክም የሚያጓጉዝ ፣ አገልጋዩ መሬት እንዳይነካው በምዕመን ላይ እየተረማመደ እንዲሄ የሆነበት ሁኔታ እዚህም ላለመከሰቱ ዋስትና የለንም።

የጽሁፌ ዓላማ
1ኛ, በፍጹም ትህትና እግዚአብሔር ሸክምና ኃላፊነት ሰጥቶ
ያስቀመጣቸው መሪዎች እንዲነቁ ለማሳሰብ !

2ኛ, ጫፍ የረገጡ ከቃሉ ያፈነገጡ አገልጋዮችና ልምምዶች
ሃይ እንዲባሉ አና ቅዱሳን ሊሰናከሉ ከሚችሉበት ሁኔታ
እንዲጠበቁ !

3ኛ, ስተው የሚያስቱትን ከማውገዝ አንጻር ቅዱሳን ሁሉ
አንድ ልብ እንዲኖራቸው ለማበረታታት ነው ።
ተባረኩልኝ !
16 views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-27 17:38:53
15 views14:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-26 13:42:58 ፍለጋችን መስቀሉን ይሁን ወይስ ስለ እኛ የተሰቀለው ኢየሱስ ክርስቶስ ?

“እርሱ ግን፦ አትደንግጡ፤ #የተሰቀለውን #የናዝሬቱን #ኢየሱስን #ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል፥ በዚህ የለም፤ እነሆ እርሱን ያኖሩበት ስፍራ።”(ማርቆስ 16፥6)
የመስቀል ሚስጥር ሲገባን እንደፈለግን ሳይሆን መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለን መኖር በቃሉ መመራት እንጀምራለን።

እስኪ በጥያቄ ልጀምር መስቀሉ ወይስ የመስቀሉ ቃል በየትኛው ነው የዳንከው ?
የመስቀሉ ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ።
የመስቀሉ ቃል የኃይል ምንጭ ነው
የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት። ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር። ኃይል ነው(1ቆሮ1:18)

መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ መስቀል ምንድነው ?
የኃጢአታችን እዳ የተከፈለበት የወንጀለኛ መስቀያ ነው!
የኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ ክቡር ደሙን ያፈሰሰበት በገዳዮቹ የተዘጋጀ መስቀያ እንጨት ነው !
ስለዚህ የሰው ልጅ ደህንነት ሚስጥር ያለው በመስቀያ እንጨቱ ላይ ሳይሆን ስለ ሁላችን ደሙን ባፈሰሰው በመስቀሉ ቃል በኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
ከተሰቀለበት እንጨት የተሰቀለልን ኢየሱስ ይበልጣል በፍጹም አይወዳደርም አይነጻጸርም !
“እናንተ #በእንጨት ላይ ሰቅላችሁ የገደላችሁትን ኢየሱስን የአባቶቻችን አምላክ አስነሣው፤”(ሐዋርያት 5፥30)
“እኛም በአይሁድ አገርና በኢየሩሳሌም ባደረገው ነገር ሁሉ ምስክሮች ነን፤ እርሱንም #በእንጨት ላይ ሰቅለው ገደሉት።”(ሐዋርያት 10፥39)
“#በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤”
(ገላትያ 3፥13)

በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው።
ኢየሱስ ስለ እኔና ስለናንተ በዚህ በተረገመ እንጨት ላይ ሲሰቀል
እሱ ጻድቅ ኃጢያት የሌለበት ነውር ያልተገኘበት ፍጹም አምላክ ነው።
ነገር ግን ስለእኔ እና እናንተ እርግማን ሆኖ #በእንጨት ላይ ተሰቀለ። በመስቀል ላይ ክቡር ደሙን አፍስሶ ሞተ ተቀበረ በሦስተኛውም ቀን ሲኦልን ድል ነስቶ የሞትን ጣር አጥፍቶ ተነሳ ።

ስለዚህ መስቀል የወንጀለኛ የሚቀጣበት ነው። የኢሱስን መገለጥና መገኘት አዘናግቶ የመስቀሉን መገኘት ማወጅ ከተሰጠን ተልዕኮ ውጭ የሆነ ክህደት ነው ።

ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ህይወቱን ሰጠን። መዳናችንን ያወጅን ሁላችን ሰርተን አልዳንም በመስቀል ላይ ተሰርቶልን እንጂ። ኢየሱስ ክርስቶስ ፍርዳችንን የኃጢያት ዕዳችንን ተሸክሞ ሞታችንን በመስቀል ላይ ሞቶ አዳነን ። በመስቀል ላይ ስለ እኛ ሞተ ። ለመዳን ማመን ያለብን በመስቀል ላይ ሥራችንን ሰርቶ ጨርሶ ያዳነንን ጌታ እንጂ መስቀሉን አይደለም።የዳነው በእርሱ በተሰራልንን በተፈጸመልንን ሥራ ነው።

ጤናማው የመስቀል ሚስጥር መልዕክቱ ሲገባን ጨለማው ሊጋርደን አይችልም። ቤተክርስቲያን ተልዕኮን ይዛ ስራን የጀመረችው ከመስቀሉ ሞት ከዛም ከትንሳኤው በኋላ ነው።በክርስቶስ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የተሰራልን ሥራ አልገባንም ማለት የእግዚአብሔር የማዳን ዓላማው እንዲገባን የሚያስችለንን እምነት የለንም ማለት ነው።

መስቀል ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጅን ቅጣት ለመቀበል የምትክነት ስራ ያከናወነበት የወጀለኛ መቅጫ ነው።
“ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን #በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።”(1ኛ ጴጥ 2፥24)

እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን እንጂ የተሰቀለበትን አንሰብክም ለትውልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ ነው መሰብክ ያለበት።ቢሆን እንኳ መስቀል መታወስ ያለበት የስቅለት መታሰቢያ በዓል ላይ በፋሲካ ነበር( ዮሐ19:17-18) የመስቀሉ መልዕክት የተሰቀለበትን የሰማይና የምድር ፈጣሪ ኢየሱስ ክርስቶስን የመስቀል ላይ የማዳን የፍቅር ስራ ነው መግለጥ ያለበት።ምክንያቱም በመስቀሉ ላይ የተሰራው ሥራ ለሰው ልጅ ሁሉ የደህንነትን፣ የምሕረት፣ የሰላምና የእርፍት አስደናቂ የመለኮት አጀንዳ ያለበት ነው ።
“እኛ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን፤ ይህም ለአይሁድ ማሰናከያ ለአሕዛብም ሞኝነት ነው፥”
(1ኛ ቆሮንቶስ 1፥23)

መስቀሉ፡-እግዚአብሔር ወልድ ሥልጣን እያለው ጌታ ሆኖ እያለ፣ በሰው አፍና እጅ በመዋረድ፣ በመሰደብ፣ በጥፊና መመታት፣ በጅራፍ በመገረፍ፣ መስቀል ተሸክሞ በመንገላታት፣የእሾህ አክሊል በመድፋት፣ በምስማር በመቸንከር ፣ እንዲሁም በጦር መወጋት ፣በመስቀል ላይ መጠማት፣ መዘባበቻ በመሆን በስቃይ በመሞት ስለ ሰው ልጆች ሁሉ ኃጢያት ምትክ ሆኖ የሞትን ፍርድ በመስቀል ላይ በመቀበል ከዘላለም ፍርድ ያዳነበት ነው።

እርሱ ግን "ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም፣ መከራንም ሲቀበል አልዛተም፡፡ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ"(1 ጴጥ 2፡23)
እንዲያውም "አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው"ለገዳዮቹ ለሰቃዮቹ ማለደላቸው(ሉቃ 23፡34)፡፡
በአዲስ ኪዳን፣ የብሉይ መሥዋዕቶች በክርስቶስ ተተክተዋል፡፡ ሁሉንም የመሥዋዕትነት ዓላማ ያሟላ ፍጹም መሥዋዕት ሆኖ ክርስቶስ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ቀርቦልናል፡፡

ለእግዚአብሔርም የመልካም መዓዛ ሽታ፣ ለእኛ ደግሞ የኃጢአታችን ማስተስሪያ በመሆን መሥዋዕትም፣ መሥዋዕት አቅራቢም ሆኖ የድነትን ሥራ ሰርቶ ፈጽሞልናል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በመሥዋዕትነቱ ደም የበደላችንን ይቅርታ አስገኘልን፡፡ በእርሱም ሞት ምክንያት የሞት ዕዳችን ተሻረ፡፡ ቅጣታችንንና የእግዚአብሔርን ቁጣ ከላያችን አነሣልን ማለት ነው፡፡ ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ለአምልኮ የምንገባበትንም በር ከፈተልን፡፡ድነትን ሰላምና እረፍትንም ሰጠን፡፡ ይህ ሁሉ የሆነው በክርስቶስ ክቡር መሥዋዕትነት ነው፡፡

እግዚአብሔርም የዘላለምን ህይወት እንደ ሰጠን ይህም ህይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው "ልጁ ያለው ህይወት አለው የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ህይወት የለውም " (1ዮሐ 5÷12)

“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”( ዮሐንስ 14፥6) ስለዚህ ጌታ እኔን ፈልጉ እንጂ መስቀል ፈልጉ አላለም ።ጌታ በመስቀል ላይ ለመዳናችን የመሆነውን ሰርቶ ጨርሶታል።

1ኛ.መስቀሉ በክርስቶስ የተሰራልን የድነት ሥራ የተከናወነበት እንጨት ነው። በታረደው በግ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ታርቀን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ታላቁ ሊቀ ካሕናታችን በመሆን እና መሥዋዕት በመሆን ወደ እግዚአብሔር አብ የጸጋው ዙፋን አቀረበን፣ አዳነን ፣ አበቃን (ዕብ 10፡1-10 ዕብ 2፡ 17-18)፡፡

2.መስቀሉ በክርስቶስ በተሰራልን የድነት ሥራ በእኛ ሕይወት የተፈጸመውንም ታላቅ ነገር ይገልጣል - አሮጌው ሰዋችን ከክርስቶስ ጋር እንደተሰቀለ (ሮሜ 6፡ 6፤11)፣ ለኃጢአትም ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር መደረጋችንን ይነግረናል። (1ጴጥ 2፡24)፡፡ በመሆኑም፣ በእኛ በአማኞች ሕይወት ውስጥ የተፈጸመና ሊታይም የሚችል ታላቅ ለውጥ ተሰርቷል አዲስ ፍጥረት ሆነናል፡፡ በአዲስ ሕይወት ለመመላለስ ለአሮጌው ሞተናልና፡፡ (ገላ 2:-20)

ክብር ሁሉ በቀራኒዮ ሥቃይ በደሙ ለዋጀን፣ ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ፣ ከዘላለም እስከ ዘላለም ድረስ ይሁን፡፡ አሜን !
22 views10:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ