Get Mystery Box with random crypto!

Aki Man Z Menz

የቴሌግራም ቻናል አርማ akiman12345 — Aki Man Z Menz A
የቴሌግራም ቻናል አርማ akiman12345 — Aki Man Z Menz
የሰርጥ አድራሻ: @akiman12345
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 334

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-01-12 11:01:33
123 viewsAki_man , 08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 11:01:29 #አቤቶ_ነጋሲ...!!
አቤቶ ነጋሢ ክርስቶስ!!
ይህንን አንጋፋ ትምህርት ቤት የ75ኛ ዓመት በዓሉን ስናከብር የበረካታ ታሪክ መነሻና መዳረሻ መሆኑን ለማስተዋወቅ እናም በትምህርት ቤቱ ዉስጥ የምናሳካቸዉ ዘርፈ ጉዳዮች አሉን።
ሆኖም አብዛኞቻችን ስለ አቤቶ ነጋሲ ክርስቶስ ወረደ ቃል/ ስለዚህ አንጋፋ ትምህርት ስያሜ ጥያቄ ዉስጥ አሳድሮብናል እናም አጠር ባለ ቋንቋ ታሪካዊ ዳራዉን ለማስቀመጥ እወዳለሁ።
አቤቶ ነጋሲ ክርስቶ የአቤቶ ሁን ያዕቆብ የልጅ ልጅ ልጅ ሲሆኑ በ1633 ዓ.ም መንዝ እመዝዋ ተራራ ላይ ነጋሪት ጎስመዉ የሸዋ ንጉስ መሆናቸዉን ያወጁ የሸዋ ስርዎ መንግስት መስራች ናቸዉ፡፡
በ1688 ዓ.ም የጎንደሩ ንጉስ አጼ ኢያሱ ከጎንደር ደብረሊባኖስ ድረስ መጥተዉ የነጋሲ ክርስቶስን የሸዋ የበላይ መስፍንነታቸዉን እንዳጸኑላቸዉ በታሪክ ተመዝገቦ ይገኛል፡፡
ነጋሲ ክርስቶስም ግዛታቸዉን እያስፋፉ፤ከተሞችን እየከተሙ፤ አብያተክርስቲያናትን እያሰሩ፤ መሬት ሳይቀር ለህዝቡ እያከፋፈሉ ሸዋን ለ27 ዓመት ገዝተዉ በመጨረሻም በጎንደር የነበሩ ወንድሞቻቸዉን ሊተዋወቁ እንዲሁም ማህተም ሊያስቀርጹ እና ግብር ሊያስገቡ ጎንደር ሄደዉ በፈንጣ በሽታ ታመዉ በ1690 ዓ.ም ስለሞቱ እዚያዉ ጎንደር ፊት አቦ እንደተቀበሩ ታሪካቸዉ ያስረዳል፡፡
ነጋሲ ክርስቶስ ያስጀመሩትን የሸዋ ስርወመንግስት የሳቸዉ ልጆች አስቀጥለዉት እስከ ታላቁ ንጉስ እምየ ምኒልክ እና የት/ቤቱ መስራች እስከሆኑት ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ቀጥለዉ የእሳቸዉ እና የአባቶቻቸዉ ህልም የነበረችዉን ኢትዮጵያን እዉን አድርገዋታል፡፡
በ1954 ዓ.ም ት/ቤቱን አቤቶ ነጋሢ ክርስቶስ ወረደ ቃል ብለዉ የሰየሙት መምህር ወልደሐዋርያት ወ/ሚካኤል የሚባሉ ለንጉሰ ነገስቱ ቅርበት የነበራቸዉ መንዜ የቤተክርስቲያን ሊቅ እንደነበሩ አባቶች ይናገራሉ፡፡ ይሄዉም ነጋሲ ክርስቶስ ይጠሩ የነበረዉ በአባታቸዉ ሳይሆን በአያታቸዉ ቀረደ ቃል እንደነበረ ያነሰጥራል፡፡
ለዚያ ነዉ ት/ቤቱ አቤቶ ነጋሲ ክርስቶስ ወረደ ቃል ት/ቤት ተብሎ የተሰየመዉ፡፡ ተቋሙ እስከ 1954 ዓ.ም ድረስ አዳሪ ትምህርት ቤት እንደነበርም ታሪክ ያወሳል፡፡
አሁን ላይ ግን
የአስተዳደር ህንጻ/ አሁን ያለዉ ህንጻ እየፈረሰ ያለ እና በሰራተኞች ህይወት ላይም አደጋ የደቀነ መሆኑ /ሙሉ ለሙሉ መቀየር ያለበት
የመጀመሪያ ደረጃ እርዳታ መስጫ ክፍል አለመኖር
የመምህራን ማረፊያ አለመኖር
የጽዳት ክፍል አለመኖር
ደረጃዉን የጠበቀ የፊዚክስ ቤተ ሙከራ አለመኖር
ደረጃዉን የጠበቀ የባዮሎጅ ቤተሙከራ አለመኖር
የሂሳብ ክፍል አለመኖር
የቴክኒካል ድራዊንግ ክፍል አለመኖር
የአይሲቲ ማዕከል አመኖር
የአይሲቲ ቤተ ሙከራዎች በመማሪያ ክፍል ዉስጥ መሆን
የመሰብሰቢያ አዳራሽ አለመኖር
የትምህርት ማበልጸጊያ /ወርክ ሾፕ አለመኖር
የሰዉነት ማጎልመሻ/ስ/ሳ ክፍል አለመኖር
የትምህርት ክፍል ቢሮዎች አለመኖር
የመምህራን መዝናኛ አለመኖር
በቤተመጽሃፍ የመቀመጫ ወንበር እጥረት
የማንበቢያ ጠረንጴዛ እጥረት
የመጽሃፍት መደርደሪያ እጥረት
የላቦራቶሪ መስሪያ ጠረንጴዛዎች እጥረት
የኩርሲ እጥረት /ላቦራቶሪ
የቁም ሳጥን እጥረት/ላቦራቶሪ
ለየትምህርት ክፍሉ የሚያገለግሉ ቁሳቁሶች እጥረት
ለትምህርት ማበልጸጊያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች አለመኖር
በአይሲቲ ቤተሙከታዎች የኮምፒዉተር እጥረት
የኮምፒዉተር ማስቀመጫ ዴስኮች ችግር
ለአስተዳደር ስራ እና ለተለያዩ የስራ ጅፍሎች የሚያገለግሉ የኮምፒዉተር እጥረት
የፕሪንተር እጥረት
የፎቶ ኮፒ ማሽኖች፤የፋክስ፤እስካነር እንዲሁም ፕሮጀክተር አለመኖር
ለተማሪዎች እና መምህራን መዝናኛ ክፍል የሚሆኑ እቃዎች/ማቴሪያልስ / አለመኖር
የመጀመሪያ እርዳታ መስጫ ቁሳቁሶች አለመኖር ...
ወ.ዘ.ተ ችግሮችን የምንሞላበት ጊዜዉ አሁን ነዉ!
ሁላችንም ታሪኩን በማስረዳት የበኩላችንን ማድረግ ይጠበቅብናል !!
Aki Man Z Menz
106 viewsAki_man , 08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 10:59:36 እንባ፥እና፥ገለባ

ላንቺ ፡ያነባሁት፡ያፈሰስኩት፡እንባ፣
ላንቺ፡ተራ፡ሆኖ፡ ቢቀል፡ከ፡ገለባ፣
እንባ፡ከ፡ገለባ፡ምን፡ቢቀል፡ከፊትሽ፣
ሚዛንሽ፡አጋድሎ፡ቀላል፡ቢከብድብሽ፣
ይማርሽ፡ነው፡እንጂ፡ሌላ፡ምን፡እላለሁ፣
ስሜትሽ፡ከ፡አዕምሮሽ፡ቀድሞ፡አይቻለሁ።
82 viewsAki_man , 07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-12 10:58:56 "ለምን ሞትህ" ቢሉት ...
አልሞትኩም እያለ ፣ ትውልድ ይሟገታል
ድሮስ
ኖሮ የማያውቅ ህዝብ ፣ ምን ሆኖ ይሞታል?!!!
።።።።።
79 viewsAki_man , 07:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 20:16:50 ሰላም ለሁሉም መሠረት ነዉ
@Aki Man Z Menz
97 viewsAki_man , 17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-10 20:16:29
በዛሬው የመቀሌ ጉዞ በጦርነቱ ምክንያት ከቤተሰቦቻቸው የተለያዩትን አትሌቶች ከቤተሰቦቻቸው ከማገናኘት በተጨማሪ ለትግራይ ክልል አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ማቋቋሚያ የሚውል የ2ሚሊዮን ብር ድጋፍ አድርገናል። ከክልሉ አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ ስኬታማና ቤተሰባዊነት የተሞላበት ስኬታማ ጉዞ አድርገን ተመልሰናል። ይህን ቀን እንድናይ ያደረግ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። ሰላም ፍቅር መቻቻል አንድነት ኢትዮጵያዊነት መዳኛ ዕሴቶቻችን ይሁን። ሁላችንም የመጣንበት ብሔር ቢኖርም ኢትዮጵያዊነት ግን አንድ ያደርገናል።እናመሰግናለን ። ሼር በማድረግ ሰላምን እናብስር
97 viewsAki_man , 17:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 09:43:00
8:30 እንገናኝ


#ተጠርታችኋል
#ሁሉም_ኮሚቴ

በዓሉን ለማክበር በሞላሌ ከተማ የከተማችሁ እንግዶች እንዲሁም ይህ ትምህርት  ቤት ይመለከተኛል የምትሉ ሁሉ
ትምህርት ቤታችን በታላላቆቻችን በኩል ጠርቶናል።

የተወደዳችሁ የአቤቶ ነጋሲ ክርስቶስ ወረደ ቃል ትምህርት ቤት ፍሬዎችና የልማት ሀሳቡ ደጋፊዎች ሁሉ በተለይም በአካል መንዝ ምድር በነዋሪነትም ይሁን ለበዓል የተሰባሰባችሁ የማትቀሩበት ክቡር ጥሪ ተጠርታችኋል።

በትልቁ እቅዳችን ጉዞ ላይ እየተማከርን በዓሉን እንጨዋወትበት ሲሉ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ኩራ ድፋባቸውና ታላቁ አባታችን መምህር ወልደሃና ወልደዮሃንስ ተጣርተዋል።
ፕሮግራሙ ነገ ከሰዓት 8:30  በትምህርት  ቤቱ አዳራሽ  ይጀምራል።
ይህ ጥሪ የማይታለፍ የማይዘገይበት ነውና የቻላችሁ ሁሉ ታደሙ።

ይህ በመንዝ ማማ ምድር ወረዳ
በሞላሌ ከተማ አስተዳደር ሞላሌ ከተማ የሚገኝ የ75 ዓመት አንጋፋ ትምህርት ብት ጥሪ ነዉ

ሼር በማድረግ መረጃውን ያድርሱልን።
28 viewsAki_man , 06:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 09:41:53
ከቀኑ 8:30 ዛሬ እንገናኝ

በጠዋቱ
የስብሰባው   አዳራሽ በዚህ መልኩ
ዝግጅቱን አጠናቋል

የእናንተን መንጣት ብቻ ነዉ የሚጠባበቀዉ
45 viewsAki_man , 06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-08 09:40:43
8:30 እንገናኝ


#ተጠርታችኋል
#ሁሉም_ኮሚቴ

በዓሉን ለማክበር በሞላሌ ከተማ የከተማችሁ እንግዶች እንዲሁም ይህ ትምህርት  ቤት ይመለከተኛል የምትሉ ሁሉ
ትምህርት ቤታችን በታላላቆቻችን በኩል ጠርቶናል።

የተወደዳችሁ የአቤቶ ነጋሲ ክርስቶስ ወረደ ቃል ትምህርት ቤት ፍሬዎችና የልማት ሀሳቡ ደጋፊዎች ሁሉ በተለይም በአካል መንዝ ምድር በነዋሪነትም ይሁን ለበዓል የተሰባሰባችሁ የማትቀሩበት ክቡር ጥሪ ተጠርታችኋል።

በትልቁ እቅዳችን ጉዞ ላይ እየተማከርን በዓሉን እንጨዋወትበት ሲሉ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ኩራ ድፋባቸውና ታላቁ አባታችን መምህር ወልደሃና ወልደዮሃንስ ተጣርተዋል።
ፕሮግራሙ ነገ ከሰዓት 8:30  በትምህርት  ቤቱ አዳራሽ  ይጀምራል።
ይህ ጥሪ የማይታለፍ የማይዘገይበት ነውና የቻላችሁ ሁሉ ታደሙ።

ይህ በመንዝ ማማ ምድር ወረዳ
በሞላሌ ከተማ አስተዳደር ሞላሌ ከተማ የሚገኝ የ75 ዓመት አንጋፋ ትምህርት ብት ጥሪ ነዉ

ሼር በማድረግ መረጃውን ያድርሱልን።
725 viewsAki_man , 06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-07 08:16:00 እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ…!

"…ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ? ቃልን ወሰነችው። ልደቱንም ዘር አልቀደመውም። በመወለዱም ድንግልናዋን አልለወጠም። ቃል ከአብ ያለ ድካም ወጣ። ከድንግልም ያለ ህማም ተወለደ። ሰብአሰገል ሰገዱለት። አምላክ ነውና ዕጣን አመጡለት። ንጉሥም ነውና ወርቅ አመጡለት። ስለኛ በፈቃዱ ለተቀበለው መዳኛችን ለሆነው ሞቱም ከርቤ አመጡለት። እርሱ ቸርና ሰውን ወዳጅ የሆነ አንድ እርሱ ብቻ ነው። ቅድስት ሆይ ለምኚልን።

"…ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ፤ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ፤ የተደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች፤ በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ፤ እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም። ለእርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ለዘላለሙ አሜን።

"…በዓለ ጌናን ስናከብር በሀዘን በመከራ፣ በጭንቅ፣ በረሃብና በጥም፣ በሰቀቀን፣ በስደት፣ በወኅኒ ቤት፣ በአልጋ ቁራኛ በደዌ ደኛ፣ በፅኑ ህመም ተይዘው፣ በየቤቱ፣ በየጎዳናው፣ በየሆስፒታሉና በፀበል ስፍራዎች ሁሉ ያሉትን፣ ከሞቀ ቤትና ንብረታቸው ተፈናቅለው በየጥሻው የወደቁትን በማሰብ፣ በመንከባከብ፣ በመጠየቅ፣ በመጎብኘትና ማዕድ በማጋራት ይሁን። ሃገራችን ኢትዮጵያንና ጎረቤቶቿን፣ መላውንም ዓለም ሁሉ ሰላማዊው ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም ያድርግልን። አሜን።

"…እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለአምላካችንና ለፈጣሪያችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን
66 viewsAki_man , 05:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ