2023-05-12 16:04:07
#አባ_አርፈዋል
መላከ ምህረት ቀሲስ ሀብተወልድ ተምትሜ ከአባታቸው ከደብተራ ተምትሜ አስፈሪ ከእናታቸት ከወ/ሮ እህትማርያም በጋሻው ህዳር 29,1917 ዓ.ም በእመጓ ቆላ ልዩ ስሙ ሾላ ፊት ተብሎ በሚጠራ ቦታ ተወለዱ ::
ከዚያም ከአባት እና እናታቸው ጋር ካደጉ በኋላ በአባታቸው አማካኝነት ውዳሴ ማርያምን ንባብ ተምረው ተጨማሪ እውቀትን ለማግኘት ወደ የህይጣ በመሄድ በአለቃ ደስታ መምህነት የውዳሴ ማርያም ዜማ መስተጋብዕ እና አቋቋም ተምረው ወደ ትውልድ ቦታቸው በመመለስ በአቡነ ቄርሎስ አማካኝነት በ1936 ዓ.ም ድቁናን ተቀብለው በማገልገል እንዳሉ ከወ/ሮ ጥሩወርቅ ተከተለው ጋር በህገ አብረሃም በ1941 ዓ.ም ተጋብተው እና ኑሮ መስረተው ልጆችም አፍርተዋል::
በመሆኑም የግብርና ሥራቸውን ከክህነት አገልግሎት ጋር በማጣጣም እየሠሩ ለ 5 ዓመታት ከቆዩ በኃላ 1947 ዓ.ም በአቡነ ባስሊዮስ አማካኝነት ቅስናቸውን ተቀበሉ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ከ እመጓ ዑራኤል ፣ ቀጭን አንባ ማርያም ፣ አረጋይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጭምር ከድቁና እስከ ቅስና ባላቸው ሙያ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ሠፊ አገልግሎት ሲያበረክቱ ቆይተው በ1988 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ ሐገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነበሩት በአቡነ ኤፍሬም እዚሁ ቦታ በመምጣት ደብሩን ደብረ ምህረት ቅዱስ ዑራኤል እሳቸውን ደግሞ መላከ ምህረት ቀሲስ ሀብተወልድ በማለት ልቅናን ሠጥተው የደብሩ አስተዳደሪ እንዲሆኑ የሾሙአቸው ሲሆን የእመጓ ዑራኤል እና ቀጭን አንባ ማርያም ቤተክረስቲያን እንዲሠራ አድርገዋል::
ከዚህም በተጨማሪ ለረጅም አመታት የእግዚአብሔር አብ ገዳም በአዛዥ የገዳም አገልግሎት ሢሰጥ ቆይቶ 1972 ዓ.ም መሬት ሲደለደል የተወሰደበት በመሆኑ ወደ ቀጭን አንባ ማሪያም የተደረበውን የእግዚአብሔር አብ ፅላት በዚሁ ልዩ ስሙ ሳሎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በ 2012 ዓ.ም በእሳቸው አማካኝነት የእግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን መስራች በመሆን አገልግሎት እንዲሰጥ አድርገዋል ::
አባታችን ሀላፊነት የተቀበሉት በአመጓ ይሁን እንጂ የሚሠጡት አገልግሎት ወሰን ና ቦታ ገደብ ሳይኖራቸው ወደ አዲስ አበባ በመሄድ በጐ አድራጊዎችን በማሠባሰብ ለ 118 ቤተክርስቲያን የሚሆኑ ረድተዋል ፡፡
የአባታችን የመላከ ምህረት ተግባር በዚህ አጭር ጊዜ ፅፎ ማቅረብ አዳጋች ነው....... አባታችን በተጨማሪም ለሀገር አለኝታ ለእመጓ ተስፋ በመሆን መንፈሳዊ ስራዎችን በመስራት የቆዪ ሲሆን ህመማቸው
ሣይቆይባቸው ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም
በተወለዱ በ 98 አመታቸው ከዚህ አለም አርፈዋል::
የእርሳቸዉ የህይወት ታሪክ በርካታ እና ተፅፎ የማያልቅ ነዉ
አብዛኞቻችሁም ስለምታዉቋቸዉ ሙሉ ታሪካቸዉን በቀጣይ እንፅፍላቸዋለን!!
የአባታችን በረከትና ረድኤታቸው አይለየን።
Aki Man Z Menz
85 viewsAki_man , 13:04