Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የሰርጥ አድራሻ: @addiszeybe
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.27K
የሰርጥ መግለጫ

ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ
Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC
ስልክ 251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-04-20 20:31:38
Samson Teklemichael's family filed a complaint against the Ethiopian Prime Minister's Office and the Ministry of Foreign Affairs over his abduction in Kenya in 2021. Samson was kidnapped by individuals in Kenyan police uniform in Nairobi 18 months ago and has not been found since.
Read more - https://addiszeybe.com/featured/politics/economy/news/currentaffairs/ethiopian-government-sued-over-its-abducted-citizen-in-kenya
772 views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 20:06:19
783 views17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 14:02:20
በኬንያ የታገተው ኢትዮጵያዊ ቤተሰቦች በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ክስ መሰረቱ

ከአንድ ዓመት ከስድስት ወር በፊት ኬንያ ውስጥ “የፖሊስ ደንብ ልብስ” በለብሱ ሰዎች ተወስዶ እስካሁን ያለበት አልታወቀም የተባለው የአቶ ሳምሶን ተክለሚካኤል ቤተሰቦች የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ላይ ክስ መሰረቱ።

የመንግስት አካላቱ ላይ የተከፈተውን ክስ በተመለከተ በዛሬው እለት የአቶ ሳምሶን ባለቤት ወ/ሮ ሚለን ሀለፎም እንዲሁም በፌደራል እና በኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች ጠበቃ የሆኑት አቶ ዳባ ጩፋ (ዶ/ር) በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

ወ/ሮ ሚለን ሀለፎም እንደተናገሩት ከባለቤታቸው መሰወር በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት የተወሰኑ ጥረቶች ቢያደርግም አንድ ዜጋ በውጭ ሀገር መብቱ ሲጣስ ማድረግ ከሚገባውው አንፃር በቂ ባለመሆኑ ክስ መክፈቱ አስፈላጊ ሆኗል ብለዋል።

ጉዳዩን የያዙት የህግ ባለሞያ አቶ ዳባ ጩፋ በበኩላቸው “ጉዳዩ ወደ ፍርድ ቤት የመጣበት ምክንያት እነዚህ የተከሰሱ አካላት ግዴታቸውን ባለመወጣታቸው ነው። ፍርድ ቤት በህግ አግባብ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ማስገደድ የሚችል በመሆኑ እንደሚያስገድዳቸው እንጠብቃለን” ሲሉ ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/addis-ababa/%E1%8B%9C%E1%8A%93/politics-am/current-affairs-am/business-am/the-families-of-the-ethiopian-kidnapped-in-kenya-filed-a-lawsuit-against-the-ethiopian-government
1.1K views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 11:18:52
የውጭ ጣልቃ ገብነት ያለበት የሱዳን ግጭት እንዲሁም የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዜጎች በሱዳን ጉዳይ - ያማረ ዱካ

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

182 views08:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 09:33:37 In celebration of this year’s “Fiche-Chambalala”, here is a piece from Addis Zeybe about Sidama’s unique calendar.
https://addiszeybe.com/fiche-chambalala-a-look-into-sidama-s-unique-calendar
377 views06:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 20:32:20
በሀዲያ ዞን በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ

በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ከጀመሩ ሁለተኛ ቀናቸውን አስቆጥረዋል፡፡

በዞኑ ባደዋቾ ወረዳ እና ሾኔ ከተማ ከ ሰባት ሰዓት በላይ በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አበባን ከአርባ ምንጭ  የሚያገናኘዉ መንገድ ዝግ ሆኖ ሲውል ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ ሰልፈኞችን ለመበተን በዞኑ ፓሊሶች ተኩስ መከፈቱን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ገልጸዋል።

በሾኔ ከተማ ሰልፉን ለመበተን በተወሰደዉ እርምጃ አንድ የፓሊስ አባል በእራሱ ተኩሶ ጉዳት ሲደርስበት ሶስት ሰዎች ድብደባ ተፈፅሞባቸዉ በከተማዋ ወደሚገኘዉ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መወሰዳቸዉን ምንጮቻን ተናግረዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/hawassa/current-affairs-am/It-was-heard-that-people-were-injured-in-the-action-taken-by-the-security-forces-in-Hadiya-Zone
846 views17:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 17:33:37 የምሽት እግር ኳስ ጨዋታዎች በድሬደዋ ከተማ የበርካቶችን ቀልብ ስቧል

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ገናና በሆነችው ድሬዳዋ ከተማ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የእግር ኳስ እየተዘወተረ መምጣቱ የበርካቶችን ቀልብ ስቧል። ሰው ሰራሽ ሳር የተነጠፈባቸው ሜዳዎች ለአንድ ሰዓት 900 ብር ይከፈልባቸዋል።

የከተማዋ የአየር ጠባይ ሙቀታማ በሆነው ድሬዳዋ ባልተለመደ መልኩ የምሽት እግር ኳስ ጨዋታዎች እየተለመዱ ሲሆን የከተማዋን ነዋሪዎችን ቀልብም እየሳበ ስለመሆኑ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ ገልፀዋል።

በወጣቶች ዘንድ ተወዳጅ እየሆነ የመጣው የምሽት ጨዋታ ከእግር ኳስ ሜዳ የራቀውን ስፖርት አፍቃሪ ወደ ሜዳ በመመለስ እና የድሬዳዋን በስፖርት ስመ ጥር መሆን ያድሳል ተብለው ተስፋ ተጥሎባቸዋል ሲሉ ነዋሪዎቹ ጨምረው ይናገራሉ።

አዲስ ዘይቤ በድሬደዋ ከተማ ተዘዋውራ የተመለከተቻቸው በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ 6 የሰው ሰራሽ ሳር የለበሱ የእግር ኳስ መጫዋቻ ሜዳዎች በአንድ ጨዋታ ማለትም ለአንድ ሰዓት እስከ 900 ብር እየተከፈለባቸው በኪራይ ያጫውታሉ።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/dire-dawa/%E1%8B%9C%E1%8A%93/lifestyle-am/current-affairs-am/night-football-games-have-attracted-the-attention-of-many-people
909 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 15:04:34 አዲስ አበባ ውስጥ ሲ.ኤም.ሲ ወይም ሳሪስ ወይም 4ኪሎ ወይም የትኛውም ቦታ ቤት መከራየት ከፈለጉ በቀላሉ መተግበሪያውን ከፍተው ቤቶቹን ማግኘት ፣ ዋጋ ማነፃፀር ከዛም በተጨማሪ በቅርቡ እቃዎትን የሚጭኑ እና የሚያደርሱ አገልግሎቶችን ማግኘት ይችላሉ ይለናል ወጣቱ ስራ ፈጣሪ ኑርሁሴን መሀመድ - Startup Corner

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ


433 viewsedited  12:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 14:17:47 የውጭ ጣልቃ ገብነት ያለበት የሱዳን ግጭት እንዲሁም የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዜጎች በሱዳን ጉዳይ - ያማረ ዱካ

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

530 views11:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 13:26:12 አንዷለም አራጌ እና ኢዜማ ተለያዩ

ታዋቂው ፖለቲከኛ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ(ኢዜማ) አመራር የነበሩት አቶ አንዷለም አራጌ ከፓርቲያቸው መለይየታቸውን ለፓርቲው ባስገቡት ደብዳቤ አስታውቀዋል፡፡ አቶ አንዷለም “ አይነግቡ እና ዘመን ተሻጋሪ ለማድረግ” የያዙት ህልም እውን ስለማይሆን ከፓርቲው ጋር መቀጠል አለመቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

አቶ አንዷለም አራጌ ለፓርቲው ባስገቡት እና በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ባሰራጩት የመልቀቂያ ደብዳቤ ላይ “ኢትዮጵያ በየትኛውም የታሪክ ድርሳን ላይ ከሰፈረው መከራዋ ሁሉ የከፋውን በምታስተናግድበት በዚህ ዘመን” ለሀገሪቱ እና ለዜጎቿ መድህን ይሆናል የተባለው ፓርቲው “የተሳከረ ሚና” እየተጫወተ ነው ብለዋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/addis-ababa/politics-am/current-affairs-am/arage-and-izema-parted-ways
615 views10:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ