Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የሰርጥ አድራሻ: @addiszeybe
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.27K
የሰርጥ መግለጫ

ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ
Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC
ስልክ 251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-04-24 10:59:22
የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ተማሪዎቹ በስልክ ሪፖርት እንዲያደርጉ አሳሰበ

በሰሜኑ ጦርነት ውድመት የደረሰበትና ከ35 ሺ በላይ ተማሪዎችን በማስተማር ላይ የነበረው መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ከጦርነቱ በኋላ ስራ ለማስጀመር እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።

በፌደራል መንግስት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል በነበረው ጦርነት ሳቢያ ለዓመታት የመማር ማስተማር ስራውን ያቋረጠው መቀሌ ዩኒቨርሲቲ አሁን የጥገና እና የመረጃ ማጣራት ስራዎችን እየሰራሁ ነው ብሏል።

በጥር ወር 2013 ዓ.ም መከላከያ ሰራዊት መቀሌ መግባቱን ተከትሎ በጊዜያዊ አስተዳደር አማካኝነት መደበኛ ትምህርት ማስተማር ጀምሮ የነበረው ዩኒቨርሲቲው የጦርነቱን ማገርሸት ተክትሎ የመማር ማስተማር ሂደቱ እንዲቋረጥ የግድ ሆኗል።

የዩኒቨርሲቲው የትምህርት ክፍል ምክትል ኃላፊ ሳሙኤል ክፋሌ (ዶ/ር) ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የጥገና፣ የበጀት ማስተካከል እና የአእምሮ ማነቃቂያ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ለአዲስ ዘይቤ ገልፀዋል።

ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/mekelle/current-affairs-am/mekele-university-urged-its-former-students-to-report-by-phone
867 views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 09:45:51
የፌደራል መንግስት እና በአሸባሪነት የተፈረጀው የሸኔ ቡድን በዚህ ሳምንት በታንዛኒያ ይገናኛሉ

ሚያዚያ 16፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፣ አዲስ አበባ) የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ ሸኔ እኩለ-ለሊት ላይ በድረ ገፁ እንዳስታወቀው ሶስተኛ ወገን ባለበት ከመንግስት ጋር ለመደራደር ተስማምቷል።

ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ዶ/ር) "ከኦነግ ሸኔ ጋር የሚደረገው ድርድር ከነገ ወዲያ በታንዛኒያ ይጀመራል" ማለታቸውን ተከትሎ ማምሻውን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ምላሽ ሲጠበቅ ቆይቷል።

ኦ ኤም ኤን ሚዲያ የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራር አማካሪ አቶ ጂሬኛ ጉደታ ገለፁልኝ እንዳለው "የታንዛኒያው ቀጠሮ  የመድረክ ማበጀት ሂደት እንጂ የፍሬ ነገር ወይይት አለመሆኑን" ገልፀዋል።

ድርድሩን በዋነኛነት የማመቻቸት ድርሻ እየተወጡ የሚገኙት ሀገራትም ኬንያ እና ኖርዌይ ቢሆኑም የኦነግ አማካሪ ለኦ ኤም ኤን እንደገለፁት ከአሜሪካ እና አውሮፓ ህብረትም ፍላጎት ነበረ።

"ጠቅላይ ሚንስተር አብይ አህመድ ድርድር ይጀምራል በሚል የገለጹበት መንገድ ሂደቱ ካለበት አንጻር ትንሽ የቸኮለ ይመስላል" ሲሉም አቶ ጂሬኛ ጉደታ አክለዋል። በመግለጫው  በጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ላይ "ኦነግ ሸኔ" በሚል የተጠቀሰው አጠራርንም ክፉኛ ኮንኖታል።

በመግለጫውም "የድርጅታችን ስም የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ሲሆን ሌላ ማንኛውም ስያሜ የተሳሳተ እና ማንነታችንን እና አላማችንን ለማሳሳት የሚደረግ ሙከራ ነው" በማለት ስያሜውን አውግዟል።

በኦሮሚያ የተለያዩ ዞኖች የሚንቀሳቀሰውን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት  ኦነግ ሸኔ በሚል በሽብርተኝነት መፈረጁ ይታወሳል። በዚህ ወቅት የትግራይ ህዝቦች ነጻነት ግንባር (ትህነግ) በሽብርተኝነት የተፈረጀ ቢሆንም የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ከሽብርተኝነት መዝገብ መሰረዙ ይታወቃል።
906 views06:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 22:25:55 የኢትዮጵያ ወይስ የኦሮምያ ጠቅላይ ሚኒስትር? - ያማረ ዱካ

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

1.3K views19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 16:37:26 አሜሪካ በዶላር ሰበብ እጅ መጠምዘዝ የምታቆምበት ጊዜ ቅርብ ነው!!!
ዲ-ዶላራይዜሽን - ፈራንካ

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ

662 views13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 14:16:51
በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙበት የሱዳን አል-ሁዳ ወህኒ ቤት ተሰበረ 

እስር ቤቱ የወንጀለኛ ቡድን መሪዎችና እጽ አዘዋዋሪዎች የሚገኙበት ሲሆን በፖሊሶች ሲያዙ የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውያንም የታሰሩበት ነበር 

ሚያዚያ 14፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤አዲስ አበባ) ከካርቱም በስተምስራቅ የሚገኙ አካባቢዎች በጀነራል አህመድ ሃምዳን ዳጋሎ ቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ ትልቁ የአል-ሁዳ ወህኒ ቤት መሰበሩ ተሰምቷል።

እስር ቤቱ ብዙ ኢትየጵየዊያን በሱዳን የፀጥታ ኃይሎች የሚታሰሩበት ሲሆን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እስረኞቹ እንዲለቀቁ ማድረጉን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ተናግረዋል።

ከካርቱም 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በኦምዱሩማን መንገድ የሚገኝና የወንጀለኛ ቡድን መሪዎች፣ አደንዛዥ እፅ አዘዋዋሪዎች እና ከመኖሪያ ፈቃድ ጋር በተገናኘ ብዙ ኢትዮጵያውያን የሚታሰሩበት እንደነበረ ምንጮቻችን ተናግረዋል።

የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ እስረኞቹን ማስለቀቁን ተከትሎ ሃሳባቸውን የሰጡ ምንጮች ታስረው ለነበሩት ኢትዮጵያውያን መፈታት በጎ ቢሆንም በከባድ ወንጀል የታሰሩ ሰዎችም መፈታታቸው ስጋት ፈጥሯል።

ግጭቱ ከተጀመረ ጀምሮ 15 የሚደርሱ ኢትዮጵያዊያን በጦርነቱ መገደላቸው የተገለፀ ሲሆንሲሆን በካርቱም የኢትዮጵያ ኤምባሲ በቂ መረጃ እየሰጠ ባለመሆኑና ስለተገደሉት ዜጎች ጉዳይ መንግስት ያለው ነገር አለመኖሩ በኢትዮጵያውያኑ ዘንድ ትችቶች እንዲሰነዘሩ አድርጓል።

በግጭቱ መባባስ ምክንያት ሀገራት ዜጎቻቸውን ከሀገሪቱ አእያስወጡ ሲሆንአሁን የኢትዮጵያ መንግስትም ዜጎቹን ለመታደግ ሀገራዊ ግብረ ሀይል ማቋቋሙን ይፋ አድርጓል።
844 views11:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 11:36:30 በሱዳን በተነሳው ግጭት የኢትዮጵያ ጣልቃ ገብነት የለም- የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

በሱዳን የኢትዮጵያውያ ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ግብረ ሀይል ተቋቁሟል

ሚያዝያ 14 ፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ አዲስ አበባ) እስካሁን ከ300 በላይ ሱዳናውያን እንዲሁም ከአምስት የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን የሞቱበት ግጭት ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ አልገባሁም አለ።

በሱዳን ግጭት የኢትዮጵያና ኤርትራ እጅ አለበት የሚል መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ በሱዳን የሚኖሩ የሀገራቱ ዜጎች የጥቃት ሥጋት ውስጥ መግባታቸውን ለአዲስ ዘይቤ ገልፀው ነበር።

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር “በሀገሪቱ ለተፈጠረው ችግር የኢትዮጵያ ጣልቃገብነት እንዳለ የተሠራጨው መረጃ ሀሰተኛ ነው” ብሏል። መረጃውን የሚያሰራጩ አካላትም “በሱዳን የተፈጠረውን ችግር አካባቢያዊ የማድረግ ፍላጎት አላቸው” ሲል የኢትዮጵያ መንግስት ወቅሷል።

ኢትዮጵያና ሱዳን ፅኑ ወዳጅነት አላቸው ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም፣ ችግሩ እንዲፈታ ኢትዮጵያ በየትኛውም ሁኔታ ከሱዳናዊያን ጎን ናት ብለዋል።

በሌላ በኩል የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ከተለያዩ መስሪያ ቤቶችና አጎራባች ክልሎችን በአባልነት ያቀፈ ግብረ ኃይል  መቋቋሙን ቃል አቀባዩ መናገራቸውን ኢዘኤ ዘግቧል። ስለተገደሉትና ስለቆሰሉት ኢትዮጵያውያን ቃል አቀባዩ በዘገባው ያሉት ነገር የለም።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሱዳን ተቀናቃኝ ሃይሎች ተኩስ አቁመው ወደ ሰላም ስምምነት እንዲመጡ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወቃል።

አዲስ ዘይቤ በሱዳን የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን በተሰራጨው መረጃ ዙሪያ ያንጋገረችበት ዘገባ - https://am.addiszeybe.com/featured/addis-ababa/current-affairs-am/Ethiopians-are-afraid-of-being-attacked-in-the-Sudanese-conflict
901 views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 11:36:26
848 views08:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 10:45:16
አሜሪካ በዶላር ሰበብ እጅ መጠምዘዝ የምታቆምበት ጊዜ ቅርብ ነው!!!
ዲ-ዶላራይዜሽን - ፈራንካ

በአዲስ ዘይቤ ዩ-ትዩብ ቻናል ይጠብቁን
https://www.youtube.com/@AddisZeybe/videosd
924 views07:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 12:25:40
Addis Alemayehou has become a household name in Ethiopia’s entrepreneurship landscape. The founder and chairman of Kanzana Group is well known for supporting and mentoring startups making him one of the biggest cheerleaders for Ethiopia’s recent tech ecosystem.

Here is a tribute from one of the founders of a startup that he helped establish,
Watch the full video of Startup Corner -

702 views09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 07:08:27 ከባህር ዳር ወደ ጎንደር ተጓዦች ከታሪፍ በላይ በመክፈላቸው እየተማረሩ ነው

ከባህር ዳር ወደ ጎንደር የሚጓዙ መንገደኞች ከታሪፍ በላይ እየከፈሉ በመሆኑ ቢያማርሩም አሽከርካሪዎች ግን ተሳፋሪዎች ራሳቸው ለመክፈል ተባባሪ ስለመሆናቸው ይገልጻሉ።

አዲስ ዘይቤ በባህር ዳር መናኸሪያ ተገኝታ ያነጋገረቻቸው መንገደኞች እንደሚሉት አጫጫኝ ደላሎች እና ረዳት የስምሪት ባለሞያ ወይም የትራፊክ ፖሊስ “መንገድ ላይ ከጠየቋችሁ 165 ብር መክፈላችሁን ተናገሩ” በማለት ያስጠነቅቋቸዋል፡፡

ይሁን እንጅ ከታሪፍ በላይ እስከ 200 ብር እየከፈሉ ይሳፈራሉ በሚል አሽከርካሪዎች እና የስምሪት ባለሞያዎች ተሳፋሪዎችም ተባባሪ ናቸው በማለት ይጠቁማሉ።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/bahir-dar/%E1%8B%9C%E1%8A%93/current-affairs-am/economy-am/Travelers-from-Bahir-Dar-to-Gondar-are-complaining-about-paying-more-than-the-fare
315 views04:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ