ከባህር ዳር ወደ ጎንደር ተጓዦች ከታሪፍ በላይ በመክፈላቸው እየተማረሩ ነው ከባህር ዳር ወደ ጎንደር የሚጓዙ መንገደኞች ከታሪፍ በላይ እየከፈሉ በመሆኑ ቢያማርሩም አሽከርካሪዎች ግን ተሳፋሪዎች ራሳቸው ለመክፈል ተባባሪ ስለመሆናቸው ይገልጻሉ። አዲስ ዘይቤ በባህር ዳር መናኸሪያ ተገኝታ ያነጋገረቻቸው መንገደኞች እንደሚሉት አጫጫኝ ደላሎች እና ረዳት የስምሪት ባለሞያ ወይም የትራፊክ ፖሊስ “መንገድ ላይ ከጠየቋችሁ 165 ብር መክፈላችሁን ተናገሩ” በማለት ያስጠነቅቋቸዋል፡፡ ይሁን እንጅ ከታሪፍ በላይ እስከ 200 ብር እየከፈሉ ይሳፈራሉ በሚል አሽከርካሪዎች እና የስምሪት ባለሞያዎች ተሳፋሪዎችም ተባባሪ ናቸው በማለት ይጠቁማሉ። ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/bahir-dar/%E1%8B%9C%E1%8A%93/current-affairs-am/economy-am/Travelers-from-Bahir-Dar-to-Gondar-are-complaining-about-paying-more-than-the-fare 315 views04:08