Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የቴሌግራም ቻናል አርማ addiszeybe — አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe
የሰርጥ አድራሻ: @addiszeybe
ምድቦች: የልጅ እንክብካቤ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 11.27K
የሰርጥ መግለጫ

ለፈጣን መረጃዎች አዲስ ዘይቤ
Twitter : https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook : https://bit.ly/2SeU3Ev
Website : https://addiszeybe.com/
YouTube : https://youtube.com/c/AddisZeybe
Instagram : https://bit.ly/3D1tEwC
ስልክ 251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-11 10:28:54
የባህር ዳር ከተማ ሁሉም መንገዶች በአሁኑ ሰዓት ተዘግተዋል
ሚያዝያ 3፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ ባህር ዳር) በአማራ ክልል ከልዩ ኃይል አባላት ወደ ፌደራል የፀጥታ መዋቅር መግባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ውጥረት ቀጥሏል።

በዛሬው እለት የክልል መስተዳደሩ መቀመጫ በሆነችው ባህር ዳር ከተማ ሁሉም መንገዶች መዘጋታቸውን አዲስ ዘይቤ ተመልክታለች። በተጨማሪም የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ የተቋረጠ ሲሆን የንግድ ድርጅቶች እና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ዝግ ሆነዋል።
በተቀጣጠለ ጎማ የተዘጉ መንገዶችን የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪ እያጠፋም ይገኛል።

ወቅታዊ መረጃዎችን ከቦታው በፍጥነት ከፈለጉ አዲስ ዘይቤ ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ።
Telegram - https://t.me/AddisZeybe
1.2K views07:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-11 09:13:29
በአማራ ክልል መራዊ ከተማ ትላንት አንድ ግለሰብ በፀጥታ ኃይሎች ሲገደል ሁለት ሰዎች ቆስለዋል ተባለ
ሚያዝያ 2፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ ባህር ዳር) በትላንትናው እለት ከጃዊ አካባቢ ወደ ባህር ዳር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የመከላከያ ሠራዊት አባላትን አታልፉም ብለው በከለከሉ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል ግጭት ተፈጥሮ አንድ ሰው መገደሉን አዲስ ዘይቤ ከስፍራው አረጋግጣለች።

አባተ መስፍን የተባለው ግለሰብ የአምስት ልጆች አባት ሲሆን የመራዊ ከተማ ነዋሪ ነበር። በትላንትናው እለት ከሰዓት የቤቱ በር አካባቢ በቆመበት በፌድራል መንግስት የፀጥታ ሀይሎች መገደሉን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ከስፍራው ማረጋገጥ ችለዋል።

በተጨማሪም ሁለት ሰዎች ላይ የመቁሰል ጉዳት ደርሷል ሲሉ ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ከፈለጉ አዲስ አበባን ጨምሮ ከ13 በላይ የኢትዮጵያ ከተማዎች ዘገባዎችን የምታቀርበውን አዲስ ዘይቤን ይወዳጁ ::
Telegram - https://t.me/AddisZeybe
Twitter - https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook - https://bit.ly/2SeU3Ev
Website - https://addiszeybe.com/
ስልክ +251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com
1.2K views06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 15:05:37
ዛሬ በእንጅባራ ከተማ ከተደረገ ሰልፍ የተወሰዱ ምስሎች ::
868 views12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 14:31:39
በጎንደር ከተማ የእንቅስቃሴ እገዳ ተጥሏል ::
929 views11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 12:29:36 በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ ከቁጥጥር ውጭ ነው ተባለ

ሙሉ ዘገባውን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/gonder/%E1%8B%9C%E1%8A%93/%E1%89%B1%E1%88%AA%E1%8B%9D%E1%88%9D/current-affairs-am/economy-am/the-fire-in-the-northern-mountains-national-park-is-said-to-be-out-of-control
1.0K views09:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 12:07:14 በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የተነሳው የእሳት ቃጠሎ ከቁጥጥር ውጭ ነው ተባለ

ከ600 በላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ እሳቱን ማጥፋት እንዳልተቻለ ኃላፊው ተናግረዋል

ሚያዝያ 02፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ ጎንደር) በሰሜን ጎንደር ዞን በሚገኘው የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ውስጥ ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ሰደድ እሳት መነሳቱን የፓርኩ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አዛናው ከፍያለው ለአዲስ ዘይቤ ገለፁ።

መጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ከ ቀኑ 9 ሰዓት መነሻው ባልታወቀ ምክንያት ሰደድ እሳቱ የተነሳ ሲሆን እሳቱን ለማጥፋት የአካባቢው ማህበረሰብ ቢሞክርም መቆጣጠር አልቻሉም። በተጨማሪም ከ600 በላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን ይህ ዘገባ እስከወጣበት ሰዓት ድረስ እሳቱን ማጥፋት እንዳልተቻለ ኃላፊው ተናግረዋል።

የቦታ አቀማመጡ ገደላማ መሆኑ እሳቱን ለመቆጣጠር ፈተና ሆኖብናል የሚሉት ሃላፊው አቶ አዛናው፣ እሳቱ ግጭ ተብሎ በሚጠራው ቦታ በኩል እንደተነሳ ገልፀው እስከ ዛሬ ሚያዚያ 02 ቀን 2015 ድረስ ከቁጥጥር ውጭ እንደሆነ ገልፀዋል።

በአማራ ክልል ከጎንደር ከተማ በሰሜን ምስራቅ አቅጣጫ 120 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኘውና 412 ኪሎ ሜትር ስኩዌር ስፋት ያለው የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ የኢትዮጵያ ረጅሙን ተራራ ራስ ደጀንን ይዟል።

በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ እንደ ጭላዳ ዝንጀሮ፣ ዋልያ አይቤክስ፣ የምኒልክ ድኩላ፣ ቀይ ቀበሮ እና ሌሎችም ብርቅዬ እንስሳት በብሔራዊ የሚገኙ ሲሆን ከ1 ሺህ 200 በላይ የተለያዩ የዕፅዋት ዝርያዎችም በፓርኩ ዉስጥ እንዳሉ ተገልጿል።

የሰሜን ብሔራዊ ፓርክን መጠለያ ካደረጉት እና ከ200 የሚበልጡት አዕዋፍ ዝርያዎች መካከል 5ቱ በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ሲሆን የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) እ.ኤ.አ. በ1978 ዓ.ም በዓለም ቅርስነት መዝግቦታል።

ስለሆነም በፓርኩ የተነሳውን ሰደድ እሳት ለመቆጣጠር የሚመለከተው አካል አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ የፓርኩ ፅህፈት ቤት ጥሪ አቅርቧል።
992 views09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-10 12:06:59
935 views09:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:46:43
በዛሬው እለት ከጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ቆቦ አካባቢዎች የአዲስ ዘይቤ ዘጋቢዎች ያሰባሰቧቸው ምስሎች ::

ወቅታዊ መረጃዎችን በፍጥነት ከፈለጉ አዲስ አበባን ጨምሮ ከ13 በላይ የኢትዮጵያ ከተማዎች ዘገባዎችን የምታቀርበውን አዲስ ዘይቤን ይወዳጁ ::

Telegram - https://t.me/AddisZeybe
Twitter - https://twitter.com/AddisZeybe
Facebook - https://bit.ly/2SeU3Ev
Website - https://addiszeybe.com/


ስልክ +251954903850
ኢሜይል info@addiszeybe.com
537 views11:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 14:12:45
#አሁን
ከደብረ ብርሃን ወደ ሸኖ የሚወስደው በተቃውሞ ሰልፈኞች ተዘጋ

ሚያዚያ 1፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ አዲስ አበባ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ከደብረ ብርሃን ከተማ ወደ  ሸኖ ያለው አገር አቋራጭ መንገድ በተቃውሞ ሰልፈኞች ተዘግቷል።

በደብረ ብርሃን የሚገኙ የአዲስ ዘይቤ ምንጮች እንደገለጹት በደብረ ብርሃን ከአማራ ፖሊስ አድማ ብተና ውጪ የልዩ ኃይል በስፍራው አለመኖሩን ገልጸው የተለየ ነገር አልተስተዋለም ብለዋል።

በሸኖ ከተማ በኩል የተዘጋው መንገድ በተደጋጋሚ ጊዜ ከአማራ ክልል የሚመጡ ተጓዦች ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ሲከለከሉ የነበረበት እና ከፍተኛ ቅሬታ የሚነሳበት እንደነበር ይታወሳል።

ዛሬ ረፋድ በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፍ  እየተደረገ ይገኛል።
633 views11:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 13:04:34
በቆቦ ከተማና ዙሪያዋ በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና በፋኖ መካከል የጥይት ተኩስ መከፈቱን ነዋሪዎች ገለፁ

ሚያዝያ 1፤ 2015 ዓ.ም.

(አዲስ ዘይቤ፤ ጎንደር) የራያ ቆቦ ከተማ ነዋሪዎች ዛሬ ሚያዚያ 01 ቀን 2015 ዓ.ም ከ 5 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ የመከላከያ ሰራዊት ከፋኖ እና የአማራ ልዩ ሃይል ጋር ተኩስ መለዋወጣቸውን ለአዲስ ዘይቤ ገለፁ።

በተያያዘ ቆቦና ወልዲያ አካባቢዎች ላይ መንገዶች እየተዘጉ ይገኛሉ።

ከመጋቢት 29 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስከዛሬ ሚያዚያ 01 ቀን ድረስ መንገድ በመዝጋት በከተማዋ ምንም አይነት የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ እንዳይኖር እንደተደረገ ነዋሪዎች አክለዋል።
701 views10:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ