Get Mystery Box with random crypto!

የምሽት እግር ኳስ ጨዋታዎች በድሬደዋ ከተማ የበርካቶችን ቀልብ ስቧል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ | አዲስ ዘይቤ ~ Addis Zeybe

የምሽት እግር ኳስ ጨዋታዎች በድሬደዋ ከተማ የበርካቶችን ቀልብ ስቧል

በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ገናና በሆነችው ድሬዳዋ ከተማ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ የእግር ኳስ እየተዘወተረ መምጣቱ የበርካቶችን ቀልብ ስቧል። ሰው ሰራሽ ሳር የተነጠፈባቸው ሜዳዎች ለአንድ ሰዓት 900 ብር ይከፈልባቸዋል።

የከተማዋ የአየር ጠባይ ሙቀታማ በሆነው ድሬዳዋ ባልተለመደ መልኩ የምሽት እግር ኳስ ጨዋታዎች እየተለመዱ ሲሆን የከተማዋን ነዋሪዎችን ቀልብም እየሳበ ስለመሆኑ ያነጋገርናቸው ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ ገልፀዋል።

በወጣቶች ዘንድ ተወዳጅ እየሆነ የመጣው የምሽት ጨዋታ ከእግር ኳስ ሜዳ የራቀውን ስፖርት አፍቃሪ ወደ ሜዳ በመመለስ እና የድሬዳዋን በስፖርት ስመ ጥር መሆን ያድሳል ተብለው ተስፋ ተጥሎባቸዋል ሲሉ ነዋሪዎቹ ጨምረው ይናገራሉ።

አዲስ ዘይቤ በድሬደዋ ከተማ ተዘዋውራ የተመለከተቻቸው በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ 6 የሰው ሰራሽ ሳር የለበሱ የእግር ኳስ መጫዋቻ ሜዳዎች በአንድ ጨዋታ ማለትም ለአንድ ሰዓት እስከ 900 ብር እየተከፈለባቸው በኪራይ ያጫውታሉ።
ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/dire-dawa/%E1%8B%9C%E1%8A%93/lifestyle-am/current-affairs-am/night-football-games-have-attracted-the-attention-of-many-people