በሀዲያ ዞን በፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ በሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን የሚገኙ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች ካለፈው ጥር ወር ጀምሮ ደመወዝ አልተከፈለንም በሚል ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ከጀመሩ ሁለተኛ ቀናቸውን አስቆጥረዋል፡፡ በዞኑ ባደዋቾ ወረዳ እና ሾኔ ከተማ ከ ሰባት ሰዓት በላይ በተደረገዉ ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አበባን ከአርባ ምንጭ የሚያገናኘዉ መንገድ ዝግ ሆኖ ሲውል ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ ሰልፈኞችን ለመበተን በዞኑ ፓሊሶች ተኩስ መከፈቱን የአዲስ ዘይቤ ምንጮች ገልጸዋል። በሾኔ ከተማ ሰልፉን ለመበተን በተወሰደዉ እርምጃ አንድ የፓሊስ አባል በእራሱ ተኩሶ ጉዳት ሲደርስበት ሶስት ሰዎች ድብደባ ተፈፅሞባቸዉ በከተማዋ ወደሚገኘዉ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል መወሰዳቸዉን ምንጮቻን ተናግረዋል። ዝርዝሩን ያንብቡ - https://am.addiszeybe.com/featured/hawassa/current-affairs-am/It-was-heard-that-people-were-injured-in-the-action-taken-by-the-security-forces-in-Hadiya-Zone 846 views17:32