2023-06-11 11:04:29
ሻለቃ ሰፈር መለስ፣ ሻለቃ ምሬ ወዳጆ፣ ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሃባውን ጨምሮ 51 በሚሆኑ በአማራ ፋኖዎች፣ምሁራን፣ ጋዜጠኞች፣ የማህበረሰብ አንቂዎች እና በሌሎችም ላይ ክስ መመስረቱ ታውቋል።
አማራ ሚዲያ ማዕከል (አሚማ) ከምንጮች ለማጣራት እንደቻለው የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የስራ አስፈጻሚው እና የም/ቤቱ ዋና ሰብሳቢ ሻለቃ ሰፈር መለስ፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ ዋና አዛዥ ሻለቃ ምህረት (ምሬ) ወዳጆ፣ ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሃባውን ጨምሮ በ51 ሰዎች ላይ በዐቃቢ ህግ ክስ ተመስርቶባቸዋል።
ዐቃቤ ህግ ብዛታቸው 51 የሚሆኑ የአማራ ፋኖ አመራሮችና አባላትን፣ ምሁራንን፣ 5 ጋዜጠኞችን፣ የማህበረሰብ አንቂዎችን፣ የጉልበት ሰራተኞችን እና ሌሎችንም በአንድ መዝገብ በማካተት ነው ክስ የመሰረተው።
ከተከሰሱት መካከልም ዶ/ር ወንዶሰን አሰፋ፣ ዶ/ር መሰረት ቀለመ ወርቅ፣ ፕ/ር መዓረጉ ቢያበይን፣ ረዳት ፕ/ር ሲሳይ አውግቸው፣ ፋኖ መንበር አለሙ እና በ20 ሽህ ብር ዋስትና ተፈቶ የነበረው ጠበቃ እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ አለልኝ ምህረቱ እንዲሁም ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ይገኙበታል።
ከመካከላቸውም 24ቱ ባሉበት፤ ቀሪዎቹ 27 የሚሆኑት ደግሞ በሌሉበት ክስ የመሰረተባቸው መሆኑን አሚማ ለመረዳት ችሏል።
ሰኔ 1/2015 በነበረው ቀጠሮ ዐቃቢ ህግ አሟልቶ መቅረብ አለበት በመባሉ ለሰኔ 5/2015 ከሰዓት በኋላ እንዲቀርቡ በሚል የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት በሰጠው ተለዋጭ ቀጠሮ መሰረት ለተከሳሾች ክሱ እንዲነበብና እንዲደርስ ይደረጋል ተብሏል።
ባሉበት እና በሌሉበት ክስ የቀረበባቸው የአማራ ልጆችም፡-
1) ዶ/ር ወንድወሰን አሰፋ ሀ/ማርያም፣
2) ጋዜጠኛ እና መምህርት መስከረም አበራ አየለ፣
3) ዶ/ር መሰረት ቀለመወርቅ፣
4) ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣
5) ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣
6) መምህር ሄኖክ አዲሴ መኮንን፣
7) ጠበቃ አለልኝ ምህረቱ አድነው፣
8 ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው ጥላሁን፣
9) ጋዜጠኛ ገነት አስማማው አያሌው፣
10) ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ዘገዬ፣
11) ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር (በሌሉበት)
12) መንበር አለሙ ተከተል፣
13) ዶ/ር ገብረአብ አለሙ ዘሪሁን፣
14) ዮርዳኖስ አለሜ ከበደ፣
15) ተስፋዬ መኩሪያ አበባው፣
16) ታደሰ ወዳጅነው ተሰማ፣
17) ሀብታሙ ዳኜ አለማየሁ፣
18) ቢሰጥ ተረፈ ካሴ፣
19) ዳዊት እባቡ ቢተው፣
20) ማስረሻ እንየው ታረቀ፣
21) ቴዎድሮስ ተሾመ አየነው፣
22) ሞላልኝ ሲሳይ ጌትነት፣
23) አብርሀም ጌትነት ዘገየ እና
24) አንደበት ተሽከር ታደሰ፣
25) ጌታቸው በየነ (በሌለበት)፣
26) ሰፈር መለስ (በሌለበት)፣
27) ምህረት ወዳጆ (በሌለበት)፣
28) እሸቱ ጌትነት (በሌለበት)፣
29) ታደለ ፍቅሬ (በሌለበት)፣
30) ተፈሪ መኮንን (በሌለበት)፣
31) ረዳ ውበቱ (በሌለበት)፣
32) ኮሎኔል ፈንታሁን ሙሃባው (በሌለበት)፣
33) ሲሳይ መልካሙ (በሌለበት)፣
34) በለጠ አቤ (በሌለበት)፣
35) አለባቸው ያስር (በሌለበት)፣
36) በላይሁን ኃይለ ማርያም (በሌለበት)፣
37) አብ አግማስ (በሌለበት)፣
38) አብርሃም ፈንታ (በሌለበት)፣
39) እዘዝ ሞላ (በሌለበት)፣
40) መታደል ጓዴ (በሌለበት)፣
41) ኤፍሬም ጎበዜ (በሌለበት)፣
42) የአብሰራ ደስታ (በሌለበት)፣
43) መለስ ባበይ (በሌለበት)፣
44) ሀብታሙ አንለይ (በሌለበት)፣
45) አባትነህ ለወዬ (በሌለበት)፣
46) ይኼነው ታደሰ (በሌለበት)፣
47) አርጋው ታደለ (በሌለበት)፣
48) ታደለ ስመኝ (በሌለበት)፣
49) ዮናስ ተሾመ (በሌለበት)፣
50) ሀይለ ሚካኤል ባየ (በሌለበት) እና
51) ቴዎድሮስ ጌታቸው (በሌለበት) መሆናቸው ታውቋል።
ዘገባው የአማራ ሚዲያ ማዕከል ነው።
Via አንድ አማራ
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
2.6K views08:04