Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ነገር መረጃ

የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_news — አዲስ ነገር መረጃ
የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_news — አዲስ ነገር መረጃ
የሰርጥ አድራሻ: @addis_news
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 76.16K
የሰርጥ መግለጫ

አዲስ ነገር መረጃዎች
መረጃዎች በትኩሱ ና ሳይዉሉ እንዲሁም ሳያድሩ በቻናሉ በኩል ይደርሳሉ
ለአስተያየት እና ለማስታወቂያ ስራዎች 👇👇
@Addisnegermereja_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 270

2022-07-13 21:05:49
ሰበር_መረጃ

በአዲስ አበባ ሰሞኑን የወጣው የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውደቅ ተደረገ
!!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሐምሌ 1 ቀን 2014 ያወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ዕጣ ውድቅ አደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ ባሳለፍነው ሐምሌ 1 ቀን 2014 የወጣው የ20/80 እና 40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕጣ ውድቅ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ከእጣ ማውጣቱ ጋር በተያያዘ እርምጃ የተወሰደባቸው አመራሮችና ሰራተኞች ስም ዝርዝር ይፋ ሆነ።

ከ14ኛ ዙር የ20/80 እንዲሁም ከ40/60 3ኛ ዙር እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮና የቤቶች ቢሮ የተለያየ እርምጃ የተወሰደባቸው አመራሮችና ሰራተኞች ስም ዝርዝር

1ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሃብቱ ቢሮ ሃላፊ ከሃላፊነቱ የተነሳ

በቁጥጥር ስር የዋሉ፡-

1ኛ. አብርሀም ሰርሞሎ የዘርፉ ምክትል ቢሮ ሃላፊ
2 ኛ . መብራቱ ወልደኪዳን :_ዳይሬክተር
3ኛ. ሀብታሙ ከበደ :_ሶፍትዌር ባለሙያ
4ኛ. ዬሴፍ ሙላት :_ሶፍትዌር ባለሙያ
5ኛ. ጌታቸው በሪሁን :_ሶፍትዌር ባለሙያ
6ኛ. ቃሲም ከድር :_ሶፍትዌር ባለሙያ
7ኛ. ስጦታው ግዛቸው :_ሶፍትዌሩን ያለማ
8.ኛ. ባየልኝ እረታ ፡_ሶፍትዌር ተቆጣጣሪ
9ኛ. ሚኪያስ ቶሌራ ፡_የቤቶች ኢንፎሜሽን ና ቴክኖሎጂ ባለሙያ
10ኛ .ኩምሳ ቶላ ፡_ የቤቶች ኢንፎርሜሽንና ቴክኖሎጂ ዳሬክተር መሆናቸውን የከተማ አስተዳደሩ አሳውቋል።

@Addis_News
@Addis_News
10.5K views18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:58:38 ደቡብ ክልል ከሲዳማ ክልል ጋር ቀደም ሲል የደረሰበትን ስምምነት በመተው በቅርቡ ከከተማዋ እንደሚለቅ ተገለፀ

ደቡብ ክልል በሀዋሳ ከተማ ለ10 ዓመታት ለመቆየት ከሲዳማ ክልል ጋር ቀደም ሲል የደረሰበትን ስምምነት በመተው በቅርቡ ከከተማዋ እንደሚለቅ ዋዜማ ዘግባለች። በደቡብ፣ ሲዳማ እና ደቡብ ምዕራብ ክልሎች መካከል የተጀመረው የሃብት ክፍፍል ገና መቋጫ አላገኘም።

ሦስቱ ክልሎች መንግሥታዊ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ለመከፋፈል ቀደም ሲል የጋራ ኮሚቴ አቋቁመዋል። ሲዳማ ክልልም በከተማዋ ከሚገኙ መንግሥታዊ ሃብቶች 23 በመቶውን እንዲወስድ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ሲዳማ እስካሁን የተረከበው ግን ሦስት ሕንጻዎችንና ተሽከርካሪዎችን እንደሆነ ዋዜማ ዘግባለች።
@Addis_News
@Addis_News
9.1K views17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:31:09
የጋራ መኖሪያ ቤት ላይ የወጣው እጣ ውድቅ ተደረገ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ20/80 እና የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤት እጣ ውድቅ አደረገ።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለ25 ሺሕ 491 ያወጣው የ20/80 እና 40/6 ላይ እጣ የወጣበት ሲስተም ላይ የተአማኒነት ጉድለት እንደነበር በመረጋገጡ ነው የወጣውን ዕጣ ውድቅ ያደረገው፡፡

ከጋራ መኖሪያ ቤቶች ከዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ጥቆማዎች በመቅረባቸው የኦዲት ሥራ የጀመረው ከተማ አስተዳደሩ በባንክ የተላከውና ለእጣ እንዲውል ወደ ኮምፒዩተር የተጫነው ዳታ ልዩነቶች መገኘታቸውን መግለጹ ይታወሳል::

[Walta]

@Addis_News
@Addis_News
9.3K views17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 20:18:55 #ችሎት!

የአሻራ እና የንስር ብሮድ ካስት ሚዲያ ጋዜጠኞችና ቲና በላይ በተጨማሪ 20 ሽህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ተወሰነ!

የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የአሻራ ሚዲያ እና ንስር ብሮድካስት ጋዜጠኞችን እንዲሁም ቲና በላይን በድጋሚ የ20 ሺህ ብር ዋስትና ጠይቋል።

ባለጉዳዮቹ በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ቀርበው የ20 ሺህ ብር ዋስትና ተጠይቆባቸው ገንዘቡ ከተከፈለ በኋላ በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ወደ አዲስ አበባ ተወስደዋል።

የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዛሬ ባዋለው ችሎት ደግሞ ጋዜጠኞችና ቲና በላይ በድጋሚ በ20 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።

በአንድ ጉዳይ ሰዎችን እያፈኑና ከቦታ ቦታ እያዘዋወሩ በወር ገቢ የሚተዳደሩ ተቀጣሪዎችን ማንገላታትና ገንዘባቸውን በዋስትና ስም መዝረፍ የመንግስት የሰርክ ስራ ሆኗል።

ኢትዮጵያን አስተዳድራለሁ ብሎ የተቀመጠው ኦህዴድ መራሹ የብልፅግና መንግስት በህዝቡ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ መልኩን እየቀያየረ ቀጥሏል ሲል አሻራ ሚዲያ ዘግቧል።

@Addis_News
@Addis_News
8.8K views17:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 16:29:52
በመጠንም ሆነ በስርጭት ብዙ አካባቢዎችን የሚሸፍን እርጥበት እንደሚኖር እና በአንዳንድ አካባቢዎች ቅጽበታዊ ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከባድ ዝናብ ሊኖር ስለሚችል ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ብሔራዊ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስጠነቀቀ፡፡

ባለፉት ቀናት በተከታታይ ዝናብ እያገኙ ያሉና ውሃ የመሸከም አቅማቸው ከፍተኛ የሆነ የአፈር አይነት ያላቸው አካባቢዎች የአፈር ውስጥ እርጥበት መብዛት እንዲሁም ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ ቦታዎች ከአፈር መሸርሸርም ሆነ ከመሬት መንሸራተት ጋር የተያያዙ ችግሮች ሊከሰቱ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል፡፡

ከእርጥበት መብዛት ጋር ተያይዞ የአረም መጨመር ሊከሰት ስለሚችል አርሶ አደሩ አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርግም ተጠይቋል፡፡

በአንጻሩ በአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች የሚጠበቀው እርጥበት በተለይም ባሳለፍናቸው ቀናት አካባቢዎቹ ካገኙት የተሻለ እርጥበት ጋር ተዳምሮ የመጠጥ ውሀ አቅርቦትና የግጦሽ ሳር ልምላሜ ከማሻሻል አንጻር ጥሩ ጎን እንደሚኖረው የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያመላክታል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ በትንበያው ላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች በአብዛኛው ከመደበኛና ከመደበኛ በላይ የሆነ ዝናብ የሚያገኙ ሲሆን ይህም የአፈር ውስጥ እርጥበትን ከማሻሻል አንፃር አስቀድመው የተዘሩና በተለያየ የዕድገት ደረጃ ላይ ለሚገኙ የበልግም ሆነ የመኸር ሰብሎች እንዲሁም ለተለያዩ የቋሚ ተክሎችና የጓሮ አትክልቶች የውሀ ፍላጎታቸውን ከማሟላት አንፃር ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል ነው ያለው፡፡

[FBC]

@Addis_News
@Addis_News
9.2K viewsedited  13:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 16:06:04
#NewsAlert

አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ። 

ኮሚሽነሩ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው ዛሬ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በፌደራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው እንደገለጹት፥ ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኤልሻዳይ ከተሰኘ በጎ አድራጎት ማህበር ባለቤት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በሚል በመጠርጠራቸው ነው። 

ይህ ኤልሻዳይ የተሰኘ ድርጅት በአዋሽ፣ በአዳማ፣ በሐዋሳ፣ በእንጅባራ በመሳሰሉ አካባቢዎች ተፈናቃዮች በሌሉበት ተፈናቃዮች አሉ በማለት በተደጋጋሚ ጊዜ የእርዳታ እህልና አልባሳት በመረከብ ሽጦ ለተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት መግዛቱ በምርምራ መረጋገጡን ነው ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ የተናገሩት።

ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ ሰፊ ክትትል ሲያደርግ እንደነበረም ረዳት ኮሚሽነሩ ማብራራታቸውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።

@Addis_News
@Addis_News
8.7K views13:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 14:32:23
ዩሮ እና የአሜሪካ ዶላር ለመጀመሪያ ጊዜ እኩል ሆኑ

ዩሮ እና የአሜሪካ ዶላር በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ እኩል እንደሆነና ከዚህ ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ ዩሮ 12 በመቶ መቀነሱ ተገለጸ።

በከፍተኛ የዋጋ ግሽበት እና የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት በተፈጠረው የኃይል አቅርቦት አለመመጣጠን የተነሳ አውሮፓ የኢኮኖሚ ውድቀት እንዳጋጠማት ሲ ኤን ኤን ዘግቧል።

ከጦርነቱ በፊት 40 በመቶ የሚሆነውን ጋዝ በሩሲያ የቧንቧ መስመር ያገኝ የነበረው የአውሮፓ ኅብረት ከጦርነቱ በኋላ በሩሲያ ዘይት እና ጋዝ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለመቀነስ ሲሞክር ሩሲያ በበኩሏ ለአንዳንድ የአውሮፓ ኅብረት ሀገራት የጋዝ አቅርቦትን አቋርጣለች።

የኢነርጂ ቀውሱ የኢኮኖሚ መቀዛቀዝ ያስከተለ ሲሆን የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ የዋጋ ግሽበትን ለማውረድ ፖሊሲውን በበቂ ሁኔታ ማጥበቅ ስለመቻሉ ጥርጣሬን ፈጥሯል ነው የተባለው።

በዚህም የዩሮ ዋጋ ከዶላር እኩል በመሆኑ የወርቅ ግብይት ላይ አሉታዊ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የዩሮ ዞን የዋጋ ግሽበት በ8 ነጥብ 6 መቶ ላይ በመቀመጡ ከአውሮፓዊያኑ 2011 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ወር የወለድ ምጣኔን እንደሚያሳድግ የአውሮፓ ማዕከላዊ ባንክ አስታውቋል።

@Addis_News
9.1K viewsedited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 13:09:44
የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ኮሚሽነሩ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው ዛሬ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉት።

በፌደራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ ሀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው ለኢቲቪ እንዳሉት ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኤልሻዳይ ከተሰኘ በጎ አድራጎት ማህበር ባለቤት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጅል ፈፅመዋል በሚል በመጠርጠራቸው ነው።

ይህ ኤልሻዳይ የተሰኘ ድርጅት በአዋሽ፣ በአዳማ፣ በሀዋሳ፣ በእንጅባራ በመሳሰሉ አካባቢዎች ተፈናቃዮች በሌሉበት ተፈናቃዮች አሉ በማለት በተደጋጋሚ ጊዜ የእርዳታ እህልና አልባሳት በመረከብ ሽጦ ለተጠርጣሪው መኖሪያ ቤት መግዛቱ በምርምራ መረጋገጡን ነው ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ የተናገሩት።

ፖሊስ በተጠርጣሪው ላይ ሰፊ ክትትል ሲያደርግ እንደነበረም ረዳት ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።

Via EBC

@Addis_News
@Addis_News
9.0K viewsedited  10:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ