2022-09-01 07:34:33
የማይረሱት_የትህነግ ወራሪው ሀይል ግፎች
ክፍል አንድ
ትናንት "ሒሳብ እናወራርዳለን!" ዛሬ "የምናወራርደው ሒሳብ የለም።" እያለ ወረራ የፈጸመው የጌታቸው ረዳው ትህነግ የማይረሳው ግፍ!!
"እናንዬን ድው አደረጋት"
ህጻናት የታቀፉ ወላጆችን በግፍ የረሸነው አሸባሪው የህወሓት ቡድን ህጻን አማን እና ወንድሞቹን ያለወላጅ አስቀርቷል። ህጻን አማን በእናትና አባቱ አስከሬን መካከል በደም ተነክሮ ነው የተገኘው። የእናቱን ሞት በአይኑ አይቷል። የወላጅ እናቱን እና አባቱን አስከሬን ታቅፎ ተገኝቷል። ይህ የጭካኔ ጥግ "ሂሳብ እናወራርዳለን" በሚል የአሸባሪው ቡድን አመራሮች ተናግረው በአማራ ክልል ወረራ ከፈጸሙ በኋላ የፈጸሙት የማይረሳው የሽብር ተግባራቸው ነው።
ጥቅም 24፣ 2013 ዓ.ም ምሽት፤ የወቅቱ የቡድኑ ቃል አቀባይ ሴኮ ቱሬ ባሞካሸው አገላለጽ "መብረቃዊ ጥቃት" በመከላከያ ላይ ክህደት ፈጽሞአል።
በህግ ማስከበር ዘመቻው ወቅት መንግስት የተናጠል ተኩስ አቁም አውጆ ከትግራይ ክልል ከወጣ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ዳግም ወረራ የፈጸመው "ከአማራ ጋር ሒሳብ አወራርዳለሁ!!" በሚል የበቀልና የጥፋት ስሜት ነበር። በዚህ ወረራ በአማራ አፋር ክልሎች ከፍተኛ ግፍ በንጹሃን ህጻናት፡ ሴቶች እና ህዝቡ ላይ ፈጽሞ ተመልሷል።
ትህነግ ዛሬም ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት በዘረፈው ነዳጅና ምግብ ለሶተኛ ዙር ጦርነት ሲጀምር መንግስትና ህዝብ የዘረጉትን የሰላም እጆች እረግጦ እና ለዳግም ግፍ መሆኑ ግልጽ ነው።
ከቀናት በፊት የትህነግ ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ እንዳለው ትናንት ከአማራ ጋር ሒሳብ እናወራርዳለን ያለውን ቀይሮ "ከአማራ ህዝብ ጋር የምናወራርደው ሒሳብ የለም" ሲል ተደምጧል።
የማይረሳው የትህነግ ግፍ ግን ይህ ነው።
ህጻናትን በጦርነት ከመማገድ ጅምሮ ህጻናት እያዩ ወላጆቻቸውን እስከ መረሸን የደረሰ!!
ይህ ንፋስ መውጫ ከተማ ውስጥ የሆነ እውነተኛ ታሪክ ነው።
@Addis_News
@Addis_News
14.5K views04:34